TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አዲስ አበባ⬆️

በአዲስ አበባ #በካርቶን የታሸገ 3 ሚሊዮን 5 መቶ ሺህ የኢትዮጵያ ብር እና 61400 የአሜሪካ #ዶላር በነሐሴ ወር 2010 ዓ/ም #መያዙን የከተማይቱ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የቻይና ዜግነት ያላቸው ሁለት ግለሰቦች ከቻይና ስቴት ኮንስትራክሽን በየቀኑ ማታ ማታ በካርቶን የታሸጉ ብሮች ያወጡ እንደነበር ከአስራ አምስት ቀን በላይ ከፈጀ #ጥብቅ ክትትል በኋላ ፖሊስ ደርሶበታል፡፡

ነሀሴ 28 ቀን 2010 ዓ/ም ምሽት ላይ መነሻዋን ከቦሌ ሻላ ያደረገች ፕራዶ መኪና ወደ ቦሌ ሩዋንዳ ታመራለች፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የክትትልና ኦፕሬሽን ክፍል አባላትም መኪናዋን በቅርብ ርቀት መከታተል ይጀምራሉ፡፡

ፕራዶዋ ቦሌ ሩዋንዳ ከአንድ ሰዋራ ቦታ ትደርስና ከአንዲት ነጭ ዶልፊን መኪና አጠገብ ትቆማለች፡፡

ከዚያም ከፕራዶዋ ውስጥ የነበሩት ተጠርጣሪዎች በካርቶን የታሸጉት የገንዘብ ኖቶችን ወደ ዶልፊነኗ ሲያዛውሩ በክትትል ቡድኑ በቁጥጥር ስር ይውላሉ፡፡

በዕለቱ በቁጥጥር ስር የዋሉት ቀደም ሲል የተጠቀሱትና የቻይና ዜግነት ያላቸው ሁለት ግለሰቦችና አንድ ኢትዮጵያዊ ግብረአበራቸው በድምሩ 3 ተጠርጣሪዎች ናቸው፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በወቅቱ ለክትትል ፖሊስ አባላቱ 2 ሁለት ሚሊየን ብር እንስጣችሁነና ልቀቁን ሲሉ ተማፅነዋቸዉ የነበረ ቢሆንም የፖሊስ አባላቱ ግን ቀጥታ ጉዳዩን ለኃላፊዎቻቸው በመንገር ከእነ ኤግዚቢቱ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ማዋላቸው ተነግሯል፡፡

©ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስመጪዎች እና ማናጀሮች

በተለያዩ ከተሞች የሚስተዋለው የውጭ ሀገራት ገንዘብ ህገወጥ ምንዛሬ በትላልቅ አስመጪዎች እና በባንክ ማናጀሮች ዋነኛ ተዋናይነት የሚመራ መሆኑን የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ገለጸ።

በፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ የፋይናንስ ወንጀሎች ምርመራ ምክትል ዳይሬክተር ኮማንደር ታደሰ አያሌው እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ ውስጥ በህገወጥ የውጭ አገራት ገንዘብ ምንዛሬ ዋነኛ ተዋናዮች አስመጪዎች፣ የተለያዩ ተቋማት ኃላፊዎች በተለይም የባንክ ማናጀሮች ናቸው።

በየአካባቢው የሚገኙት ዶላር መንዛሬዎች ግን ሶስተኛ ወይንም አራተኛ አካላት ናቸው። እንደ ኮማንደር ታደሰ ገለጻ፣ በየአካባቢው የሚገኙት ዶላር መንዛሬዎች ዋነኛ የህገወጥ ተግባሩ ተዋናዮችን በውል የማያውቁ እና ለእነርሱ የሚሰሩ ናቸው።

ህገወጥ ተግባሩ በተዋረድ (በኔትወርክ) የሚከናወን እና በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ያላቸው አስመጪዎች የሚያንቀሳቅሱት ነው። በተጨማሪ የባንክ #ማናጀሮች ዶላር ፈልጎ የመጣን ባለሀብት ቢሮክራሲ በማብዛት ዶላር እንደሌለ አስመስለው ያባርራሉ። በጎን ደግሞ ደላሎችን ልከው ወደ ህገወጥ መንገድ እንዲሄዱ በማመቻቸት ገንዘብ ተቀብለው ይሰጧቸዋል።

ኮማንደር ታደሰ እንደተናገሩት፤ በአንድ የአሜሪካን #ዶላር ከ10 ብር እስከ አስራ አራት ብር ትርፍ በመውሰድም #ከደላሎች እና በየደረጃው ካሉ ህገወጦች ጋር ይከፋፈላሉ። በተለይ በሶማሌ ክልል #ቶጎ_ውጫሌ የሚገሹ 16ቱም ባንኮች በህገወጥ የዶላር ምንዛሬ ውስጥ እንደሚሳተፉ መረጃ አለ። በሶማሌ ላንድ ጠረፍ ከተማዋ የሚገኙ እና በተለያዩ ከተሞች የሚሰሩ የባንክ ማናጀሮች በዚህ ህገወጥ ተግባር እንደሚሳተፉ የፌዴራል ፖሊስ መረጃው አለው። በሌላ በኩል በህገወጥ መንገድ ከአገር የዘረፉትን ገንዘብ በህጋዊ መንገድ ለማንቀሳቀስ የሚፈልጉ ሰዎች ሀብታቸውን ወደ ዶላር መንዝረው ከአገር ለማስወጣት ይጠቀሙበታል።

በዚህ ዓመት በመርካቶ እንደተደረገው ድንገተኛ ፍተሻ አሁንም በቀጣይ እንደሚደረግ የገለጹት ኮማንደር ታደሰ፤ ይሁንና ዋነኞቹ የምንዛሬው ተዋናዮችን ለመያዝ መረጃ ሳይሆን ማስረጃ እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል። እንደ እርሳቸው ገለጻ፤ ለዚህ ደግሞ ህብረተሰቡ ተሳታፊ መሆን አለበት። ህብረተሰቡ ደግሞ መረጃ ቢያቀብልም መስካሪ ሆኖ የችግሩን አመንጪዎች ለመከላከል ፍላጎት አያሳይም። ፖሊስ ግን ገንዘብ የያዘን ሁሉ አስሮ መቅጣት ስለማይችል የህብረተሰቡ የማጋለጥ እና የመመስከር ልምድ መጠናከር አለበት። ፌዴራል ፖሊስም ማስረጃ ባጠናቀረ ወቅት ህገወጦችን ለመቅጣት የሚያስችል ስራ ማከናወኑ አይቀርም ብለዋል።

Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሩብል📉

የምዕራባውያን ማዕቀብ እጅጉን የበረታባት ሩስያ የመገበያያ ገንዘቧ የሆነው #ሩብል ከአሜሪካ #ዶላር አንፃር በእጅጉ ቀንሷል።

አሁን ላይ 1 የሩስያ ሩብል $0.0085 ከ1 የአሜሪካ ሳንቲም በታች ወይም አንድ የአሜሪካ ዶላር በ117.18 የሩስያ ሩብል እየተመነዘረ ነው።

አንድ የአሜሪካ ዶላር በሩስያ ሩብል ሲመነዘር ፦

• ከአንድ ወር በፊት : 76.2 ሩብል
• ከአንድ ሳምንት በፊት : 81.4 ሩብል
• ከአንድ ቀን በፊት : 108.5 ሩብል
• አሁን : 117.18 ሩብል

ምዕራባውያን አንዳንድ የሩሲያ ባንኮች #ስዊፍት የተሰኘውን ዓለም አቀፍ የገንዘብ ማዘዋወሪያ ስርዓትን እንዳይጠቀሙ አግደዋቸዋል።

እገዳውን ተከትሎ ነው የሩሲያው ሩብል በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ደረጃ ዋጋው የወረደው።

ምዕራባውያን በሩስያ ባንኮች ላይ ጠንካራ የሆኑ ማዕቀቦችን ጥለዋል ፤ የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክም 630 ቢሊዮን ዶላር ከማንቀሳቀስ ታግዷል።

አሁንም የምዕራባውያኑ ሀገራት በሩስያ ላይ እየጣሉት ያለው ጠንካራ ማዕቀብ የሩስያን ኢኮኖሚ እንደሚያሽመደምደው እና ከዓለም አቀፉ ስርዓት እንደሚገፋው ተንታኞች እየተናገሩ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሩብል📉 የምዕራባውያን ማዕቀብ እጅጉን የበረታባት ሩስያ የመገበያያ ገንዘቧ የሆነው #ሩብል ከአሜሪካ #ዶላር አንፃር በእጅጉ ቀንሷል። አሁን ላይ 1 የሩስያ ሩብል $0.0085 ከ1 የአሜሪካ ሳንቲም በታች ወይም አንድ የአሜሪካ ዶላር በ117.18 የሩስያ ሩብል እየተመነዘረ ነው። አንድ የአሜሪካ ዶላር በሩስያ ሩብል ሲመነዘር ፦ • ከአንድ ወር በፊት : 76.2 ሩብል • ከአንድ ሳምንት በፊት : 81.4…
#Rubel

ከዩክሬን ጦርነት ጋር በተያያዘ በምዕራባውያን ብርቱ የሆነ ማዕቀብ ምክንያት የሩስያ የመገበያያ ገንዘቧ የሆነው #ሩብል ከአሜሪካ #ዶላር አንፃር በእጅጉ ቀንሶ እንደነበር ይታወሳል።

ከሳምንታት በፊት በተለዋወጥነው መረጃ 1 የአሜሪካ ዶላር በ117.18 የሩስያ ሩብል እስከመመንዘር ደርሶ ነበር።

ይህም ፥ የሩሲያው ሩብል በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ደረጃ ዋጋው እንዲወርድ አድርጎት ነበር።

አሁን ላይ ግን በሩብል እና የአሜሪካ ዶላር ያለው ልዩነት በእጅጉ ጠቧል።

ከሳምንታት በፊት በ117.18 ሩብል ሲመነዘር የነበረው የአሜሪካ ዶላር ዛሬ በ80.25 ሩብል እየተመዘረ ይገኛል።

👉 የካቲት 24 ቀን 2014 ዓ/ም - አንድ የአሜሪካ ዶላር 117.18 ሩብል ፤

👉 ዛሬ ሚያዚያ 2 ቀን 2014 ዓ/ም - አንድ የአሜሪካ ዶላር 80.25 ሩብል ፤

የምዕራባውያን ጠንካራ ማዕቀቦችን ተከትሎ የኢኮኖሚ ተንታኞች የሩስያ ኢኮኖሚ በአጭር ጊዜ ሊሽመደመድ እንደሚችል እና የከፋ ችግር ላይ እንደምትወድቅ መግለፃቸው ፤ ሩስያ በበኩሏ እየተጣሉባት ያሉት ማዕቀቦች ይበልጥ ነፃና ጠንካራ ሀገር እንደሚያደርጋት መግለጿ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የፌዴራሉ መንግሥት የ2017 ጠቅላላ የወጪ በጀት 971.2 ቢሊዮን ብር ሆኖ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቧል። ለክልል መንግሥታት የበጀት ድጋፍ የተመደበው 236.7 ቢሊዮን  ብር ነው። አጠቃላይ የ2017 በጀት (971.2 ቢሊዮን) በ2016 በጀት ዓመት ከጸደቀው የወጪ በጀት አንጻር የ21.1 በመቶ እድገት እንዳለው  ተገልጿል። ዛሬ ከሰዓት የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ምክር…
#ብር #ዶላር

የፌዴራል መንግሥት #የ2017_በጀት ሲዘጋጅ ብርን ከዶላር አኳያ ያለውን የምንዛሬ ተመን #የሚያዳክም ውሳኔ ተግባራዊ ይደረጋል በሚል ታሳቢነት እንዳልሆነ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ለተወካዮች ም/ ቤት ተናግረዋል።

በኢ-መደበኛው እና በባንኮች በሚደረግ ይፋዊ ምንዛሬ (official exchange) መካከል ያለውን ልዩነት የሚያጠብ እርምጃን አስመልክቶ  " ምንም የቀረበ ነገር የለም "  ብለዋል።

አቶ አህመድ ፥ የፌዴራል መንግሥት በጀት የተዘጋጀው " የነበረው አካሄድ #እንደሚቀጥል ታሳቢ ተደርጎ " ሲሉ ገልጸዋል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ " ዘንድሮ የነበረውን ይፋዊ የውጭ ምንዛሬ መጠን (official exchnage rate) ታሳቢ አድርጎ ነው በጀቱ የቀረበው " ሲሉም አጽንኦት ሰጥተዋል።

ይህን ማብራሪያ የሰጡት በም/ቤቱ የኢዜማ ተወካይ ዶ/ር አብርሃም በርታ ፥  " ህጋዊውን እና ኢ-መደበኛውን የውጭ ምንዛሬ ገበያ እኩል ለማድረግ የሚደረጉ ሙከራዎች እንዳሉ ከአንዳንድ ወገኖች እየሰማን ነው ፤ ... የውጭ መንግስታት #በብድር_ምክንያት በኢትዮጵያ ላይ ጫና በመፍጠር ይህንኑ ለማስፈጸም እንደሚንቀሳቀሱ የሚገልጹ መረጃዎችም አሉ ፤ እንዲህ አይነቱ እርምጃ የማንወጣው ችግር ውስጥ ይከተናል የሚል የባለሙያዎች ትንታኔ አለ " በማለት ላነሱት ሀሳብ ነው።

#EthiopianInsider #HoPR #TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ለነገ አርብ የውጭ ምንዛሬ ዋጋ ጨምሯል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የነገ አርብ ምንዛሬ ዋጋን ዛሬ ምሽት ይፋ አድርጓል። በዚህም አንዱ የአሜሪካን ዶላር መግዣው 83 ብር ከ9413 ሳንቲም ፤ መሸጫው 85 ብር ከ6201 ሳንቲም እንዲሆን ቆርጧል። ፓውንድ ስተርሊንግም በእጅጉ ጨምሯል። መግዣው 101 ብር ከ9101 ሳንቲም ፤ መሸጫው 103 ብር ከ9483 ሆኖ ይውላል ብሏል። ዩሮም ጨምሯል።…
#ዶላር

ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 25/2016 ዓ/ም የነበረውን እና ነገ ሐምሌ 26/2016 ዓ/ም የሚኖረውን ልዩነት ይመልከቱ !

➡️ ዛሬ የዋለበት ፦ አንድ የአሜሪካ
ዶላር 80 ብር ከ0203 ሳንቲም መግዣ ፤ 81 ብር ከ6207 ሳንቲም መሸጫ

➡️ ለነገ የተቆረጠው ፦ አንድ የአሜሪካ
ዶላር 83 ብር ከ9413 ሳንቲም መግዣ ፤ 85 ብር ከ6201 ሳንቲም መሸጫ

ይህ የምንዛሬ ዋጋ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ነው።


#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዕለታዊ ዛሬ ንግድ ባንክ የዶላር መግዣ ላይ ጭማሪ በማድረግ ወደ 108 ብር ከ0728 ሳንቲም አስገብቷል። መሸጫው 119 ብር ከ9608 ሳንቲም ነው። በአቢሲኒያ ባንክ አንዱ ዶላር 108 ብር ከ0729 ሳንቲም መግዣ ፤ 121 ብር ከ0416 ሳንቲም መሸጫ ተቆርጦላታል። በወጋገን ባንክ የዶላር መግዣው 115 ብር ከ0121 ሳንቲም ነው። አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ደግሞ አንዱን የአሜሪካ ዶላር በ107…
#ዶላር

የዶላር ምንዛሬ ዋጋ ከፍ ያለ ጭማሪ አሳይቷል።

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለ7 ቀናት ጭማሪ ያልታየበት ወጥ የምንዛሬ ዋጋ ነበር።

ባንኩ ዛሬ ሲያገበያይበት የነበረው የምንዛሬ ዋጋ ከፍ ያለ ጭማሪ የታየበት ነበር።

አንዱ የአሜሪካ ዶላር መግዣው ወደ 112 ብር ከ3957 ሳንቲም ደርሷል።

የመጫው ዋጋም 124 ብር ከ7592 ሳንቲም ገብቷል።

በፓውንድ ላይም ጭማሪ ተመዝግቧል።

አንዱ ፓውንድ መግዣው 141 ብር ከ6314 ሳንቲም ተቆርጦለት ውሏል። መሸጫው 157 ብር ከ9487 ሳንቲም ነበር።

ዩሮ መግዣው 125 ብር ከ0177 ሳንቲም መሸጫው 138 ብር ከ7697 ሳንቲም ሆኖ ውሏል።

የUAE ድርሃም መግዣው 30 ብር ከ6030 ሳንቲም መሸጫው 33 ብር ከ9693 ሳንቲም ገብቷል።

#Ethiopia

@tikvahethiopia