TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ወላይታ ሶዶ🔝

#አለን_ኢትዮጵያ የበጎ-አድራጎት ድርጀት የሰው ልጆች የለውጥ ማዕከል ህጋዊ እውቅና በማግኘት ትላንት በ19/05/01 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ በይፋ ሥራ ጀመረ።

"በጎ ሥራ በመስራት የህሊና እረካታ እናግኝ!!" በሚል መር ቃል አቅም ለሌላቸው አረጋዊያንና ጎዳና ተዳዳሪ ህጻናት ድጋፍ አደረገ፡፡

የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ አቶ ሐንጀሎ ደሴ በመክፈቻው እንደተናገሩት ወላጅ አጥ የሆኑትንና አቅመ ደካማ አረጋዊያንን ማገዝ የዕቅዳችን ዋና ዐላማ ስሆን ይህን መልካም ተግባር በራሳቸው ፍቃድ በመደራጀት እየመሩ አሁን ላለበት ቁመና ያደረሱ ወጣቶችንና ባለድርሻ አካላትን ከልብ እያመሰገንኩ በቀጣይ ይህ ዛሬ በማዕከል ደረጃ አድጎ "አለን ኢትዮጵያ የሰው ልጆች የለውጥ ማዕከል" በምል የበጎ አድራጎት ድርጅት ሆኖ ሥራ መጀመሩን አበስራለው።

የዝህ ድርጅት ዋና ዓላማ በተደራጀ አግባብ ቀጣይነት ባለው መልክ ይህን መልካም ተግባር ለመደገፍ ታስቦ የተቋቋመ ስሆን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆንና በየደረጃው ካሉ አመራሮች ጋር ሆነን ይሄን መዋቅር ለመደገፍ ብሎም ከከተማ አስተዳደር የሚጠበቀውን የትኛውንም ድጋፍ ለማገዝ ቃል እየገባው ይህ መልካም ተግባር በሁሉም ህብረተሰብ ዘንድ ልለመድ ይገባል ስል መልክቱን አስተላልፈዋል።

አቅመ ደካማ የሆኑ አረጋዊያንና ህፃናትን በየአካባቢው ህብረተሰቡ ሊደግፏቸውና ሊንከባከቧቸው እንደሚገባ ብሎም ሁሉም የህብረተሰብ አካል የዝህ ድርጅት አባል በመሆን የዜግነት ድርሻውን እንድወጣ የድርጅቱ ኃላፍ ወጣት ዘገየ ወርቁ ተናግረዋል፡፡

ምንጭ፦ ተስፋማርያም(አለን ኢትዮጵያ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 20/2011 ዓ.ም.

የጀርመን ፌዴራል ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ዶ/ር #ፍራንክ_ዋልተር_ሽቴይንሜይር በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት እያደረጉ ይገኛሉ።
.
.
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀድሞ አፈ ጉባኤ አቶ #ዳዊት_ዮሃንስ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል።
.
.
ቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል #የደም_ስር_መጥበብ ችግር ላለባቸው ታካሚዎች ከዛሬ ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት የፒሲአይ የነጻ ህክምና አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
.
.
ጠ/ሚር #ዐቢይ_አሕመድ ኢትዮጵያን እየጎበኙ ካሉት ከጀርመን ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ፍራንክ ዋልተር ስታይንማየር ልዑካቸውን ተቀብለው አነጋግረዋል።
.
.
ለኢፌድሪ ፕረዝዳንት ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ታከለ ኡማ(ኢ/ር) የEuropean Tourism Academy Membership ሽልማት ሊሠጥ እንደሆነ ተሰምቷል።
.
.
የኢትዮጵያ ክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ በ2011 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት 4 ሚሊየን 234 ሺህ 856 መቶ ተሸከርካሪዎች በማስተናገድ በአጠቃላይ ብር 124 ሚሊየን 578 ሺህ 594 መቶ ብር መሰብሰብ መቻሉ ተሰምቷል።
.
.
#አለን_ኢትዮጵያ የበጎ-አድራጎት ድርጀት የሰው ልጆች የለውጥ ማዕከል ህጋዊ እውቅና በማግኘት ትላንት በ19/05/01 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ በይፋ ሥራ ጀምሯል።
.
.
በአንድ ፒካፕ ተሽከርካሪ ላይ በተደረገ ፍተሻ ከባህርዳር ወደ አዲስ አበባ ሲጓጓዙ የነበረ ሦስት መትረየስ፣ 1924 የስታር እና 1856 የማካሮቭ ሽጉጥ ጥይቶች ከ37 የጥይት መያዥ ጋር #መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
.
.
የጀርመኑ ግዙፍ የመኪና አምራች ኩባንያ ቮልስዋገን ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርሟል።
.
.
የሚድሮክ ግሩፕ የሼክ ሙሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲንን ከእስር #መፈታትን ምክንያት በማድረግ ሠራተኞቹን #አንበሻብሿል
.
.
ከፍተኛው ፍርድ ቤት ለሙስና ተጠርጣሪው የጄኔራል ክንፈ ዳኘው ወንድም #ኢሳያስ_ዳኘው ፈቅዶት የነበረውን የዋስትና መብት ዛሬ ጠቅላይ ፍርድ ቤት እንደሻረው ካፒታል ዘግቧል፡፡
.
.
ጠ/ሚር ዶክተር #ዐቢይ_አሕመድ ዛሬ ምሽት #በብሄራዊ_ቴአትር በየሶስት ወሩ የሚካሄደውን የኪነ ጥበብና የባህል ምሽት ተካፍለዋል።
.
.
ሚድሮክ ኢትዮጵያ የሼክ ሞሃመድ አላሙዲን መፈታት አስመልክቶ፦ የሚድሮክ ንብረት በሆነው #ዩኒቲ_ዩኒቨርስቲ የሚማሩ ተማሪዎች ላንድ ወሰነ ትምህርት(1 ሴሚስተር) #በነጻ እንዲማሩ ፈቅዶላቸዋል፡፡
.
.
ምንጭ፦ ዋልታ፣ ፋና፣ ኢ.ፕ.ድ.፣ ዋዜማ ሬድዮ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት
.
.
ሰላም እደሩ!!
የነገ ሰው ይበለን!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቡሌ ሆራ👆

#አለን_ኢትዮጵያ_የሰው_ልጆች_የለውጥ_ማዕከል ቡሌ ሆራ ቅርንጫፍ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በማዕከሉ ለሚያሰለጥናቸው ሰልጣኞች የምሣ ግብዣ በማድረግ በአሉን በጋር አክብሯል።

Via www.alenethiopia.org

@tsegabwolde @tikvahethiopia