TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA #ETHIOPIA በኢትዮጵያ የአሜሪካ ጉዳይ ፈፃሚ አምባሳደር ትሬሲ አን ጃኮብሰን ከኢትዮጵያ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል። ከአሜሪካ ኤምባሲ በኩል ይፋ በሆነ መረጃ ውይይቱ ፥ በአሜሪካ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነቶች ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ እንዲሁም በሀገራቱ መካከል ስላለው ወሳኝ ኢኮኖሚያዊ እና የንግድ ግንኙነት ላይ ትኩረት ያደረገ…
#US

በኢትዮጵያ የአሜሪካ ጉዳይ አስፈፃሚ ትሬሲ አን ጃኮብሰን ከሰሞኑ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነርና ምክትል ዋና ኮሚሽነር ጋር ተገናኝተው መወያየታቸው ይታወሳል።

በኃላም ከገንዘብ ሚኒስትር ጋር በኢትዮጵያ እና አሜሪካ የሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ መክረው ነበር።

ትላንት ከኢትዮጵያ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ ጋር በገለልተኛ የዳኝነት ስርዓት እንዲሁም የሰብአዊ መብት አያያዝ አስፈላጊነት ላይ ተወያይተዋል።

በዛሬው ዕለት ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ጋር ተገናኝተዋል።

ሰላም እና እርቅ እንዲፈጠር እንዲሁም ለተቸገሩ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እርዳታ እንዲደርስ ያላቸውን ተስፋ መጋራታቸውን ከአሜሪካ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ፅ/ቤት ባገኘነው መረጃ ደግሞ ፥ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የአሜሪካን ተጠባባቂ አምባሳደር ጃኮብሰንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ማነጋገራቸውን ይገልፃል።

አምባሳደር ኣን ጃኮብሰን ፤ ከቅዱስነታቸው ቡራኬ ለመቀበል እና ይፋዊ የሥራ ትውውቅ ለማድረግ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ የተገኙ መሆናቸውን መረጃው ይገልፃል።

ቅዱስነታቸው ከአምባሳደሯ ጋር በነበራቸው ቆይታ የእንኳን ደህና መጡ መልዕክት በማስተላለፍ በኢትዮጵያ የሚቆዩበት ጊዜ ውጤታማ ተግባራትን ማከናወን የሚችሉበት ይሆን ዘንድ አባታዊ ተምኔታቸውን ገልጸው በቡራኬ ሸኝተዋቸዋል።

@tikvahethiopia
#US_VISA

አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በስቴት ዲፓርትመንት በተቀመጡና ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች መሰረት Diversity Visa (ዲቪ) ን ጨምሮ ሁሉንም የስደተኛ እና ስደተኛ ያልሆኑ የቪዛ ሂደት ማስቀጠል መጀመሩ ዛሬ አሳውቋል።

እስካሁን በትዕግሥት ለጠበቁም " ትዕግስታችሁን እናደንቃለን " ብሏል።

የአሜሪካ ኤምባሲ ፤ ቀጠሮ ለመያዝ ጊዜው ሲደርስ አመልካቾች መረጃ በኢሜል ይላክላቸዋል ያለ ሲሆን ጥያቄ ካላችሁ ይህንን ድረገፅ ጎብኙ ብሏል ፦ https://et.usembassy.gov/visas/

የአገልግሎቱ ፈላጊዎች " የግል ጉዳዮቻቸውን " በተመለከተ ጥያቄያቸውን በፌስቡክ ወይም በሜሴንጀር በኩል ቢያነሱ ለጥያቄያቸው መልስ መስጠት እንደማይችል የገለፀው የአሜሪካ ኤምባሲ " የግል መረጃችሁን በፌስቡክ ገፁ ላይ አታጋሩ " ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#US_VISA አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በስቴት ዲፓርትመንት በተቀመጡና ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች መሰረት Diversity Visa (ዲቪ) ን ጨምሮ ሁሉንም የስደተኛ እና ስደተኛ ያልሆኑ የቪዛ ሂደት ማስቀጠል መጀመሩ ዛሬ አሳውቋል። እስካሁን በትዕግሥት ለጠበቁም " ትዕግስታችሁን እናደንቃለን " ብሏል። የአሜሪካ ኤምባሲ ፤ ቀጠሮ ለመያዝ ጊዜው ሲደርስ አመልካቾች መረጃ በኢሜል ይላክላቸዋል…
#US_VISA

የአሜሪካ ኤምባሲ ፤ የ Diversity Visa (ዲቪ) ን ጨምሮ ሁሉንም የስደተኛ እና ስደተኛ ያልሆኑ የቪዛ ሂደቶች እያስቀጠለ መሆኑን ገልጿል።

ኤምባሲው አገልግሎቱን እየተጠባበቁ ያሉ ሁሉ ፤ በዓለም አቀፉ ወረርሽኝ ኮቪድ-19 እና በኢትዮጵያ ታውጆ በነበረው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወደኃላ የቀሩ ስራዎችን ለመስራት በሚደረገው ሂደት በትዕግስት እንዲጠብቁ መልዕክቱ አስተላልፏል።

የቪዛ ቃለመጠይቆች ሂደት ሚከናወነው በስቴት ዲፓርትመንት ቅድሚያ በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ በመመስረት መሆኑን የገለፀው ኤምባሲው ፤ አሜሪካውያንና ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች በሁሉም የቪዛ መደቦች ላይ በተቻለ መጠን ብዙ ቃለ መጠይቆችን ለማድረግ በማቀድ በትጋት ስራቸውን እያከናወኑ ነው ብሏል።

በዚህም ሂደት ላይ ፤ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ሁሉንም አስፈላጊ ሰነዶች ይዘው ለቃለ መጠይቅ ዝግጁ ሆኖ በመምጣት የሁሉንም ሰው የጥበቃ ጊዜ እንዲቀንስ ለማድረግ ማገዝ ይችላሉ ሲል መልዕክቱን አስተላልፏል።

@tikvahethiopia
#US

የአሜሪካው ፕሬዜዳንት በሀገራቸው ለሚታየው የዋጋ ግሽበት የሩስያን መሪ ቭላድሚር ፑቲንና የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ተጠያቂ አደረጉ።

ትላንት ጆ ባይደን ለሀገራቸው ህዝብ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ሁኔታ ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በዚህ ማብራሪያቸው ለዋጋ ግሽበት የኮቪድ-19 ወረርሽኝንና ሩስያን ተጠያቂ አድርገዋል።

"ዛሬ እያየን ያለነው የዋጋ ንረት ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች አሉ" ያሉት ባይደን አንደኛው አስከፊው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መሆኑን አስተዋል።

ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ "ፑቲን በዩክሬን ላይ የከፈተው ጦርነት ነው" ሲሉ ተደምጠዋል፤ ባይደን በመጋቢት ወር ከተመዘገበው የዋጋ ግሽበት 60% የሚሆነው ከነዳጅ የዋጋ ጭማሪ ጋር በተያያዘ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ባይደን ዩክሬንና ሩስያ በስንዴና በቆሎ ምርታቸው ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዙ በማስረዳት "የፑቲን ጦርነት የምግብ ዋጋ እንዲጨምር አድርጓል" ሲሉ የሩስያውን መሪያ ተጠያቂ አድርገዋል።

ከሪፖርተሮች በአሜሪካ ለሚታየው የዋጋ ግሽበት አስተዳደራቸው ኃላፊነት ይወስድ እንደሆነ ሲጠየቁ "ፖሊሲዎቻችን የሚያግዙ እንጂ የሚጎዱ አይመስለኝም" ሲሉ መልሰዋል።

ባይደን በሀገራቸው የሚታየው የዋጋ ግሽበት ሊፍታ የሚገበው ከፍተኛ ችግር መሆኑን በማንሳት ችግሩን ለመፍታት ልዩ ትኩረት አድርገው እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

ፕሬዜዳንቱ በትላንት ማብራሪያቸው "በእርግጥ የተወሳሰበ ነው። የአሜሪካ ዜጎች ሊረዱት እንደማይችሉ ግን እየጠቆምኩ አይደለም። እነሱ ይረዱታል፤ ጠረጴዛቸው ላይ ምግብ እንዲኖር ለማድረግ በቀን 8፣ 10 ሰዓታት እየሰሩ ነው" ብለዋል።

መቼ የምርቶች ዋጋ ይቀንሳል ለሚለው ባይደን ለመተንበይ ፍቃደኛ ሳይሆኑ የቀሩ ሲሆን የዋጋ ግሽበቱን ለመቆጣጠር ምን መስራት እንዳለብን እናውቃለን ብለዋል telegra.ph/US-05-11-2

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA መሳሪያ በታጠቁ ሰዎች በርካቶች በሚገደሉባት ሀገረ አሜሪካ ከሰሞኑን ተፈፅመው በነበሩ ጥቃቶች ሰዎች ተገድለዋል ፤ ቆስለዋል። ሰሞኑን በኒው ዮርክ ግዛት በፋሎ ከተማ አንድ ነጭ ታጣቂ ጥቁሮች የሚበረክቱበት መገበያያ ሥፍራ ገብቶ ጥቃት ፈፅሞ 10 ሰዎችን ገድሏል። ይኸው ተጠርጣሪ 18 ዓመቱ ሱሆን ፔይተን ጌንድሮን ይባላል ጥቃቱን 320 ኪሎ ሜትር ተጉዞ መጥቶ መፈፀሙን ፖሊስ ገልጿል። አሜሪካዊው…
#US

በየጊዜው በርካቶች በታጣቁ ሰዎች በሚከፈት ተኩስ የሚገደሉባት ሀገረ አሜሪካ ትላንትም እጅግ በጣም ዘግናኝ የሚባል ጥቃት ተፈፅሞ 2 አዋቂዎችን ጨምሮ 19 ሕጻናት ተገድለዋል።

በአሜሪካ ቴክሳስ ግዛት አንድ የ18 ዓመት ወጣት በከፈተው የተኩስ እሩምታ 2 አዋቂዎችን ጨምሮ 19 ሕጻናት መገደላቸውን ተዘግቧል።

ድርጊቱ የተፈፀመው በደቡብ ቴክሳስ ግዛት፣ ዩቫልዲ ከተማ ሮብ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ነው አንድ ወጣት ድንገተኛ ተኩስ ከፍቶ ነው 19 ህፃናትን ጨምሮ 2 አዋቂዎችን የገደለው።

ከተገደሉት ሁለት አዋቂዎች አንዷ በዚያው ትምህርት ቤት የምታስተምር መምህርት ነበረች።

ፖሊስ እንዳለው ድርጊቱ የፈፀመው ወጣት የታጠቀው ኤአር-15 ከፊል አውቶማቲክ ጠመንጃ ነበር።

ወጣቱ መጀመርያ ሴት አያቱን ከገደለ በኋላ ነው ሕጻናቱን በግፍ የገደላቸው ተብሏል።

አንዳንድ መገናኛ ብዙኃን ወጣቱ በዚያው አካባቢ በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት የ2ኛ ደረጃ ተማሪ እንደሆነ እየዘገቡ ይገኛሉ።

የቴክሳስ ግዛት ገዥ ግሬግ አቦት ወጣቱ " ሳልቫዶር ራሞስ " እንደሚባልና መኪናውን ደጅ አቁሞ ወደ ትምህርት ቅጥር ግቢው ከገባ በኋላ አሰቃቂው ድርጊት እንደፈጸመ ተናግረዋል።

አሶሲየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ከትምህርት ቤቱ በቅርብ የነበረ አንድ የድንበር ጠባቂ ፖሊስ የተኩስ ድምጽ ሰምቶ ወደ ትምህርት ቤቱ በመግባት ይህን ወጣት ታጣቂ ተኩሶ ባይገድለው ኖሮ የሟቾች ቁጥር ከዚህ በላይ ሊሆን ይችል ነበር።

እንደ Gun Violence Archive ድረገፅ መረጃ በአሜሪካ ሀገር ከጦር መሳሪያዎች ጋር በተያያዘ (በመሳሪያ እራሳቸውን የሚያጠፉትን ጨምሮ) በየዓመቱ #አርባ_ሺህ (40,000) ይሞታሉ።

(ኤፒ/ቢቢሲ - ፎቶ - ሶሻል ሚዲያ)

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ #አሜሪካ #ሩስያ

በመጪዎቹ ቀናት ኢትዮጵያ የሩስያ እና የአሜሪካ ባለስልጣናትን ታስተናግድለች።

ነገ ማክሰኞ የሩስያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
ሰርጌ ላቭሮቭ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ያደርጋሉ።

ለቭሮቭ በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት ለማድረግ ነው ነገ አዲስ አበባ የሚገቡት።

በአዲስ አበባ ቆይታቸው ፦
- በኢትዮጵያ እና ሩስያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ዙሪያ ውይይት ያደርጋሉ፤
- ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ እና ሩስያ መካከል የተፈረሙ ስምምነቶች ላይ ይመክራሉ፤
- ከአፍሪካ ህብረት ኃላፊዎች ጋር ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ላቭሮቭ ኢትዮጵያ ሲመጡ የመጀመሪያቸው አይደለም። እ.ኤ.አ 2018 ላይ ኢትዮጵያን ጎብኝተው ነበር።

(ሰርጌ ላቭሮቭ ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው ቀደም ብሎ #በግብፅ የስራ ጉብኝት አድርገዋል)

#US የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር ከሐምሌ 17- ሐምሌ 25 2014 ዓ.ም ኢትዮጵያን ጨምሮ በግብፅ፣ በዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ጉብኝት ያደርጋሉ።

በኢትዮጵያ ግብኝታቸው የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት በሰላም ለመቋጨት ሊደረግ የታሰበው የሰላም ድርድር ላይ ይወያያሉ።

በተጨማሪ ፦
- የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ያለበትን ሁኔታ ይገመግማሉ።
- በጦርነቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የፈጸሙ አካላት ተጠያቂ ማድረግን በተመለከተ ይመክራሉ።

ሐመር የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሆነው ከተሾሙ በኃላ ወደኢትዮጵያ ሲመጡ ሁለተኛቸው ይሆናል ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ መጥተው ከምክትል ጠ/ሚ እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጋር መወያየታቸው አይዘነጋም።

(ማይክ ሐመር ወደ ኢትዮጵያ ከመምጣታቸው በፊት #በግብፅ ጉብኝት ያደርጋሉ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝታቸውን አጠናቀው ታይዋንን ለቀው ወጥተዋል። የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ እና በሀገሪቱ የስልጣን እርከን ሶስተኛ ሰው የሆኑት ናንሲ ፔሎሲ ታይዋን ጎብኝተዋል። ትላንት ታይዋን ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ብዙ ሲባልለት የነበረ እና በአሜሪካ እና ቻይና መካከል የፈጠረው ከፍተኛ ውጥረት ዓለምን ያሰጋ ነበር። ቻይና ፔሎሲ ወደታይዋን እንደሚመጡ…
#US #CHINA

" ቻይና ማንንም መከልከል አትችልም " - ፔሎሲ

" ሀገሬን የሚዳፈሩ ሁሉ ይቀጣሉ " - ቻይና

በአሜሪካ በስልጣን እርከን 3ኛዋ ሰው ናንሲ ፔሎሲ ከታይዋን ጉብኝታቸው በኋላ " ቻይና የዓለም መሪዎችን ወይም ማንንም ወደ ታይዋን እንዳይጓዙ መከልከል አትችልም " ሲሉ ተናግረዋል።

ቻይና ፤ ከፔሎሲ ጉብኝት በፊት ጉብኝቱ እንዳይደረግ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያና ዛቻ ብታሰማም ፔሎሲ ወደ ታይዋን ገብተው ፤ ጉብኝት አድርገው ባለስልጣናትን አነጋግረው ሄደዋል።

ምንም እንኳን የፔሎሲ ጉብኝት ቢጠናቀቅም በቻይና እና አሜሪካ መካከል ያለው ውጥረት የቀጠለ ሲሆን ቻይና " ሀገሬን የሚዳፈሩ ሁሉ ይቀጣሉ " ስትል ዝታለች።

በሌላ በኩል ወደ ታይዋን ትልክ የነበረውን የተፈጥሮ አሸዋ መላክ ያቆመች ሲሆን ፍራፍሬና የዓሣ ምርቶችን ከታይዋን ማስገባት አቁማለች።

ታይዋን አካባቢ አሁንም የቻይና ወታደራዊ እንቅስቃሴ መቀጠሉ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia #US

የማይክ ሐመር ስለ ኢትዮጵያ ቆይታቸው ምን አሉ ?

አሜሪካ የኢትዮጵያን #ሉዓላዊነቷን እና #የግዛት_አንድነቷን_በማክበር ኢትዮጵያን ለመደገፍ ያላትን ፍላጎት እንደሚያረጋገጡ የሀገራቸውን አቋም ገልፀዋል።

በአሜሪካ ህዝብ ለጋስነት ሀገሪቱ ለተቸገሩ ኢትዮጵያውያን ሰብዓዊ ድጋፍ እያደረገች መሆኑን አመልክተዋል።

ሰላምን በማረጋገጥ በኩል የጋራ ፍላጎቶችን በሚመለከቱ ጉዳዮች ዙሪያ ከመንግስት ጋር የመነጋገር እድሉን ማግኘታቸውን እንደሚያደንቁ ገልፀዋል።

ሀመር በኢትዮጵያ ቆይታቸው ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እና የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ልማት እቅዶች ይበልጥ እንዳወቁና እንደተማሩ አሳውቀዋል።

በአፍሪካ ኅብረት ጥላ ስር ባለ ዲፕሎማሲ፣ በናይል ወንዝ ዳር የሚኖሩትን ሁሉ የሚያገለግል ስምምነት ላይ መድረስ ይቻላል ብለዋል።

ሀመር በኢትዮጵያ ለሁለት ሳምንት የሚጠጋ ጊዜ የቆዩ ሲሆን ቆይታቸው አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ረጅም የግንኙነት ታሪክ እና በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን ለአፍሪካ ህብረት የምታደርገውን ጥረት የሚያንፀባርቅ መሆኑን በአ/አ የአሜሪካ ኤምባሲ ገልጿል።

ሀመር በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከእነማን ጋር ተገናኙ ?
- ከፕ/ት ሳህለወርቅ ዘውዴ
- ከም/ጠ/ሚ እና ውጭ ጉዳይ ሚ/ር አቶ ደመቀ መኮንን
- ከኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ ሌንሳ ቢየን
- ከተለያዩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ቡድኖች
- ከተመድ መርማሪዎች (በአ/አ)
- ከAU የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦባሳንጆ
- ከመንግስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች አመራሮች
- ወደ ትግራይ ተጉዘው ክልሉን እያስተዳደሩ ካሉት ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል እና ሌሎች የህወሓት አመራሮች ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።

https://telegra.ph/US-08-09

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USAirstrike የአሜሪካ አየር ጥቃት - በጎረቤት ሶማሊያ ! በጎረቤታችን ሶማሊያ ሂራን ክልል የሶማሊያ ብሄራዊ ጦር ኃይል የፀረ ሽብር ዘመቻ እያካሄደ ሲሆን ጦሩን ለመደገፍ #አሜሪካ የአየር ጥቃት መሰንዘር መጀመሯ ተገልጿል። አሜሪካ የአየር ላይ ጥቃቱን እንድትሰነዝር የተጠየቀችው በሶማሊያ መንግስት መሆኑን የሀገሪቱ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል። በክስተቱ ንፁሀን ዜጎች ላይ ምንም አይነት…
#US #SOMALIA

አሜሪካ ትላንትና ማክሰኞ ፤ ከሶማሊያ መንግስት ጋር በመተባበር በፈፀመችው የአየር ድብደባ 4 የአልሸባብ የሽብር ቡድን አባላትን መግደሏን አሳውቃለች።

የአልሸባብ ታጣቂዎች የሶማሊያ ጦር ላይ በቤልድዌይኔ ጥቃት የከፈቱ ሲሆን ይህን ተከትሎ የአሜሪካ ጦር በአየር በፈፀመው ድብደባ 4 የቡድኑን አባላት መግደሉ ተገልጿል።

አሜሪካ እርምጃው በሶማሊያ መንግስት በኩል ፍቃድ ኖሮት መፈፀሙን አሳውቃለች።

በጥቃቱ በሲቪል ሰዎች ላይ ጉዳት እንዳልደረሰ / ሲቪሎች እንዳልተገደሉ ተመላክቷል።

@tikvahethiopia
#US

አሜሪካ መላ ዜጎቿን ለመግደል በቂ የሆነ " ፌንታሊን " የተሰኘ አደንዛዥ ዕፅ ማያዟን አስታወቀች።

የአሜሪካ የዕጽ ተቆጣጣሪ ባለሥልጣን እየተጠናቀቀ ባለው 2022 መላውን የአሜሪካ ዜጋ ለመግደል በቂ የሆነ " ፌንታሊን " የተሰኘ አደገኛ አደንዛዥ ዕጽ መያዙን አሳውቋል።

ባለስልጣኑ፤ በአንዴ እንዲወሰዱ ተደርገው የተዘጋጁ እያንዳንዳቸው ሁለት ሚሊግራም የሚመዝኑ ገዳይ የሆኑ 379 ሚሊዮን ፌንታሊን የተሰኘ ዕጾችን ይዣለሁ ብሏል።

ይህ አደንዛዥ ዕጽ ከሄሮይን 50 እጥፍ በላይ ገዳይ እንደሆነ የገለፀ ሲሆን "ፌንታኒል አሜሪካ በአሁኑ ወቅት የገጠማት ገዳይ ስጋት ነው " ሲል ገልጾታል።

ይኸው የዕፅ ተቆጣጣሪ መ/ቤት እንደሚለው፤ ከፍተኛ መጠን ያለው ፌንታሊን ወደ አሜሪካ የሚገባው #ከሜክሲኮ ሲሆን ከ4 ሺ 500 ኪግ በላይ ፌንታሊንና 50.6 ሚሊዮን በእንክብል መልክ የተዘጋጁ ዕጾች ተይዘዋል።

በእንክብል መልክ የተዘጋጁት ዕጾች ህመም ማስታገሻ መድኃኒቶች እንዲመስሉ መደረጋቸውን ተገልጿል።

እየተጠናቀቀ ባለው በዚህ የፈረንጆቹ ዓመት የተያዘው የዕጽ መጠን ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በእጥፍ ጨምሯል።

አንደ ባለስልጣኑ መረጃ፤ በአሜሪካ የሚያዙት ዕጾች " በሲናሎዋ እና ጃሊስኮ " ዕጽ አዘዋዋሪ ቡድኖች አማካይነት ሜክሲኮ ውስጥ በምስጢራዊ ስፍራ በሚገኙ ፋብሪካዎች ይመረታሉ።

"ፌንታሊን" እጅግ አደገኛ የሆነ ዕጽ ሲሆን የእርሳስ ጫፍ ላይ ልትቀመጥ የምትችል ትንሽ መጠን እንኳን የመግደል አቅም አላት።

ማጠቃለያ፦

- ባለፈው ዓመት 100 ሺ አሜሪካውያን ከመጠን በላይ ዕጽ ወስደው ሕይወታቸው አልፏል። ከዚህ ውስጥ ሁለት ሦስተኛው ሞት ከፌንታሊን ጋር የተገናኘ ነው።

- በዚህ ዓመት የተያዘው ፌንታሊን መጠን 330 ሚሊዮን የአሜሪካ ነዋሪዎች መግደል የሚችል ነው።

#BBC

@tikvahethiopia
#Ethiopia #US

አሜሪካ ከ #አማራ_ፋኖ ታጣቂዎች ጋር የሰላም ንግግር እንዲጀመር የኢትዮጵያ መንግሥትን እንደጠየቀች አሳውቃለች።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ እንዲሁም የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሃመር በኦንላይን መግለጫ ሰጥተው ነበር።

መግለጫቸው ባለፉት ቀናት በኢትዮጵያ የነበራቸውን የስራ ቆይታ የተመለከተ ነበር። 

በዚህ ወቅት በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ጨምሮ ከተለያዩ ባለስልጣናትና የተቋማት መሪዎች ጋር በኢትዮጵያ ያሉ ግጭቶች #በውይይት እንዲፈቱ መነጋገራቸውን አሳውቀዋል።

አሜሪካ በኦሮሚያ እየተካሄደ ያለው ግጭት እልባት እንዲያገኝ የበኩሏን ሚና እየተጫወተች መሆኑን ገልጸው በአማራ ክልልም ግጭቶች በሰላም እንዲቋጩ ከፋኖ ጋር ንግግር እንዲጀመር ጥሪ መቅርቡን ተናግረዋል።

አምባሳደር ማይክ ሃመር ምን አሉ ?

" ባለፈው ሕዳር ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር በዳሬሰላም በተደረገው ውይይት ላይ በቀጥታ ተሳትፈናል። አሁን ይህን ለመቀጠል ዝግጁ ነን። ግጭቱ በሰላም እንዲፈታ እንዴት መመቻቸት እንደሚቻል ለሁለቱም አካላት ሃሳብ አቅርበናል።

ከፋኖ ጋር ንግግር እንዲደረግ አምባሳደር ማሲንጋ ለመንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን እናውቃለን።

ሰላምን ለማረጋገጥ ያሉትን እድሎች በመጠቀም ጥረታችንን ለመቀጠል ዝግጁ ነን። በተደጋጋሚ እንዳልነው ለነዚህ ግጭቶች ወታደራዊ መፍትሄ አማራጭ አይሆንም አሁንም ትኩረት መደረግ ያለበት ውይይት ላይ ነው። " ብለዋል።

ሞሊ ፊ ምን አሉ ?

" ኢትዮጵያ በአሁን ወቅት በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ያጋጠሟትን ፈተናዎች በሰላም ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ቁርጠንኝነታቸው እንዲቀጥሉ እናበረታታለን።

በታጣቂዎች ለሚፈፀሙት ጥቃቶች የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ስለሚወስዱት እርምጃ አሳሳቢነት ገልጸናል። የጸጥታው ሁኔታን አሳሳቢነት ብንረዳም የሲቪሎችን መብት ለመጠበቅ ተጨማሪ ጥሪ ያስፈልጋል " ብለዋል።

አምባሳደር ማይክ ሃመር ፤ " ከተለያዩ ባለስልጣናት ጋር በተደረገው ስብሰባ ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር ውይይት ለማመቻቸት እንዲሁም የቀጠሉትን ግጭቶች በሰላም ለመፍታት ከአማራ ፋኖ ጋር ሊደረግ የሚችል ንግግር ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳለን ገልጸናል " ብለዋል።

ሃመር በኢትዮጵያ ላለው ግጭት ወታደራዊ መፍትሄ እንደሌለ ገልጸው የኢትዮጵያ መንግሥትም ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁነት እንዳለው መግለፁን እናደንቃለን ሲሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ከዚህ ቀደም ግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ ፅኑ አቋም እንዳለው መግለፁ ይታወቃል። ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋርም በይፋ ሁለት ጊዜ ድርድር ቢቀመጥም መጨረሻ ላይ መሳካት አልቻለም። በአማራ በኩል ከፋኖ ጋር ለድርድር ስለመቀመጥ እስካሁን በይፋ የተባለ ነገር የለም።

አሜሪካውያኑ ባለስልጣናት በሰጡት መግለጫ ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር ሳይሳካ ቀርቶ የተቋረጠው ድርድር መቼ እንደሚቀጥል እንዲሁም መንግሥት ከፋኖ ጋር ለድርድር ይቀመጥ እንደሆነ በግልፅ ባይናገሩም የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁ እንደሆነ እንዳሳወቃቸው ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው የቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ / ጋዜጠና ኬኔዲ አባተ መሆኑን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
#Somaliland #US

ዛሬ በሶማሊያ የአሜሪካ አምባሳደር ሶማሌላንድ፣ ሀርጌሳ ነበሩ።

አምባሳደር ሪቻርስ ሪሌይ ፤ ሶማሌላንድ ሀርጌሳ ሄደው ከሶማሌላንድ ፕሬዜዳንት ሙሴ ባሂ አብዲ ጋር መክረዋል።

ከሌሎችም ከፍተኛ የፖለቲካ መሪዎች ፣ የሲቪል ማህበረሰብ መሪዎችና የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ጋርም መወያየታቸው ተሰምቷል።

አምባሳደሩ ፤ አሜሪካ በቀጠናው ብልጽግናን እና የዴሞክራሲ ተቋማትን ለመደገፍ የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት እንዳላት አረጋግጠዋል።

ዲፕሎማሲያዊ እና የጸጥታ ችግሮችን ለመፍታት ቀጠናዊ ትብብር እና ውይይትን ያበረታቱም ሲሆን ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር የምርጫ ጊዜን በማክበር አስፈላጊነት ላይ ተወያይተዋል።

ከግሉ ሴክተር መሪዎች ጋር በመገናኘት ከአሜሪካ የንግድ ማህበረሰብ ጋር ግንኙነት እንዴት እንደሚጠናከር መነጋገራቸው ታውቋል።

የነቃ ሲቪል ማህበረሰብ እና ነፃና ሙያዊ ስርዓቱን ያከበረ ፕሬስ አስፈላጊነት ላይ አጽንኦት ሰጥተዋል ተብሏል።

ፕሬዜዳንት ሙሴ ቢሂም ከአሜሪካው አምባሳደር ጋር ተገናኝተው መምከራቸውን አሳውቀዋል።

በቀጠናዊ ጉዳዮች ፣ በአፍሪካ ቀንድ ትብብርን ማጎልበት ፣ በምርጫ ጉዳይ ፣ በሶማሌላንድ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን ግንኙነት ማጠናከር ላይ መወያየታቸውን ገልጸዋል።

በሶማሊያ፣ ሞቃዲሹ ያለው ኤምባሲ የዛሬውን የአምባሳደሩን የሀርጌሳ ጉብኝት በተመለከተ ያሰራጨውን የጽሁፍ መግለጫን አንዳንዶች ' ያልተለመደ ነው ' ብለውታል።

ሀገሪቱ " ሶማሌላንድ፣ ሀርጌሳ ፤ የሶማሌላንድ ፕሬዜዳንት " እያለች መጥራቷ በቋንቋ አጠቃቀም ላይ የታየ ጉልህ ለውጥ ነው ያሉ አልጠፉም።

የአምባሳደሩን ሀርጌሳ ላይ መገኘትን የኮነኑም አሉ። ገለልተኛ አይደሉም ሶማሊያን ይደግፋሉ በሚል።

ሶማሊያውያን ደግሞ በየማህበራዊ ሚዲያ ላይ አሜሪካን መቃወም ይዘዋል።

" መግላጫው ሶማሌላድ ስለ ተፈራረመችው የመግባቢያ ስምምነት (MoU) ምንም ያለው ነገር የለም " በማለት እንዲሁም " ሶማሌላንድ የሶማሊያ ግዛት እንደሆነች ሳይገለጽ መቅረቡ ሌላ ነገር ከጀርባው የያዘ ነው " በሚል ነው የተቃወሙ ያሉት።

#Somaliland
#Hargeisa

@tikvahethiopia
#US #Egypt

የዴሞክራት ፓርቲ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ላይ የግብፅን ፍላጎት ለማስከበር ጉቦ ተቀብለው በአሜሪካ ሴኔት ውስጥ የግብፅን አጀንዳ በማራመድና በሌሎች ክሶች ጥፋተኛ ተባሉ። 

በሴናተሩ ላይ የቀረቡትን ክሶች የተመለከተው የኒውዮርክ ፍ/ቤት በመጪው ጥቅምት ወር የቅጣት ውሳኔ ለማሳለፍ ቀጠሮ መያዙ ታውቋል። 

ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ በአሜሪካ ሴኔት ውስጥ የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆነው ሲያገለግሉ በነበሩበት ወቅት፣ ለዓመታት የግብፅን አጀንዳ በሴኔት ውስጥ ሲያራምዱ እንደነበር ለዚህም ከግብፅ መንግሥት ክፍያ ማግኘታቸውን ዓቃቤ ሕግ የሰነድ ማስረጃና የሰው ምስክሮችን በማቅረብ አረጋግጧል።

የሴናተር ሜኔንዴዝ ባለቤት የሆነችው ናዲኔ ሜኔንዴዝ  እ.ኤ.አ. በማርች 2020 ገደማ ባለቤቷ ሴናተር ሜኔንዴዝ ከአንድ የግብፅ ጦር ጄኔራል ጋር እንዲገናኙ ፕሮግራም ማዘጋጀቷንና በፕሮግራሙ ላይም ሴናተሩ ከግብፅ ጄኔራል ጋር ተገናኝተው በወቅቱ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን አስመልክቶ በግብፅ፣ በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል ይካሄድ ስለነበረው ድርድር መወያየታቸውን የምርመራ መዝገቡ ያስረዳል።

በወቅቱም ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ዋነኛ የትኩረት አጀንዳ ተደርጎ ይወሰድ እንደነበር የምርመራ ሰነዱ ይገልጻል።

ሴናተሩ ከግብፅ ጄኔራል ጋር በተገናኙ በቀጣዩ ወር ውስጥ (በኤፕሪል 2020 ወይም ገደማ)፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር ላይ ለሚሳተፉት ለወቅቱ የአሜሪካ ግምጃ ቤት ፀሐፊና የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደብዳቤ መጻፋቸውን ያትታል።

በደብዳቤያቸው መግቢያ ላይም፣ " እኔ ይህንን ደብዳቤ የምጽፈው ግብፅ፣ ኢትዮጵያና ሱዳን በግድቡ ዙሪያ ያደርጉት የነበረው ድርድር መቋረጥ እንዳሳሰበኝ ለመግለጽ ነው " ማለታቸውን ያስረዳል።

በማከልም፣ " የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በግድቡ ድርድር ላይ የሚያደርገውን ተሳትፎ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሳድግ እጠይቃለሁ "ማለታቸውን የምርመራ መዝገቡ ይጠቅሳል።

እ.ኤ.አ. በ2021 መገባደጃ ላይ የሴናተር ሜኔንዴዝ ባለቤት የሆነችው ናዲኔ ሜኔንዴዝ አዘውትራ ከምትገናኘው ከግብፅ ጄኔራል ጋር በመነጋገር እሷና ባለቤቷ ሜኔንዴዝ ወደ ግብፅ እንዲጓዙ ፕሮግራም ማመቻቸቷንና ጉዞውም በጥቅምት 2021 መደረጉን ያስረዳል። 

በመጀመሪያ ጉዞው መደበኛ ያልሆነ ወይም ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቁጥጥር ውጭ እንዲካሄድ የታቀደ መሆኑን የሚያለክተው የምርመራ መዝገቡ፣ በኋላ ላይ አንድ የአሜሪካ ሴኔት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ ባልደረባ በካይሮ የሚገኘውን የአሜሪካ ኤምባሲ በማነጋገር ጉዞው በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እውቅናና ቁጥጥር የሚደረግበት መደበኛ የኮንግረንስ ልዑክ የሥራ ጉብኝት እንዲሆን ማነጋገሩን ይጠቅሳል።

ነገር ግን ይህ ጥያቄ መቅረቡን ያወቀው የግብፅ ባለሥልጣን እንደዚያ ሊሆን እንደማይችል የሚገልጽ መልዕክት ለናዲን ሜኔንዴዝ መላኩንና ናዲን ሜኔንዴዝም ምልዕክቱን ለሴናተር ሜኔንዴዝ መላኳን በዚህም ምክንያት ሴናተሩና ባለቤታቸው ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እውቅና ውጪ እንደተካሄደ በምርመራ መዝገቡ ተጠቅሷል።

ሜኔንዴዝና ባለቤታቸው ወደ ግብፅ ከተጓዙ በኋላም በካይሮ ከበርካታ የግብፅ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተውና በአንድ ከፍተኛ የግብፅ የስለላ መሥሪያ ቤት ባለሥልጣን የግል መኖሪያ ቤት እራት መብላታቸውን ያስረዳል።

በእነዚህ ወቅቶችም ልዩ መለያ ቁጥር የተከተበባቸው ባለ አንድ ወቄት የሚመዝኑ 22 የወርቅ ባሮችን (አሞሌዎችን) ከግብፅ መንግሥት በክፍያ (በጉቦ) መልክ ማግኘታቸውን፣ በዚያ ወቅት የገበያ ዋጋ መሠረት አንዱ ወቄት የወርቅ ባር 1,800 ዶላር እንደነበርና ክስ ከተመሠረተ በኋላ በወጣ የፍርድ ቤት የብርበራ ማዘዣ ሁለት የወርቅ አሞሌዎች በመኖሪያ ቤታቸው መገኘቱን የምርምራ መዝገቡ ያስረዳል።

የአሜሪካ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በክሱ እንደገለጸው፣ ሴናተር ሜኔንዴዝ በተለያዩ ጊዜያት ከግብፅ የስለላ ባለሥልጣናት ጋር መገናኘታቸውን፣ ከእነዚህም መካከል በአሜሪካ የምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) ሚስጥራዊ ክትትል በተደረገበት በሞርተን ሬስቶራንት ውስጥ ከግብፅ የስለላ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝተው እራት በመብላት ለግብፅ መረጃ አሳልፈው መስጠታቸውን እንዲሁም ለግብፅ ምቹ ወታደራዊ የጦር መሣሪያ ድጋፍ ለማስገኘት ማሴራቸውን ይገልጻል።

ሜኔንዴዝ ለግብፅ መንግሥት ራሳቸው ደብዳቤ አዘጋጅተው ከሰጡ በኋላ ይህንኑ ደብዳቤ በመጠቀም በግብፅ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ሌሎች የኮንግረስ አባላት ያላቸውን ሥጋት ለማግባባት እንደተጠቀሙበት የአሜሪካ ፌዴራል ዓቃቤ ሕግ የክስ ሰነድ ያስረዳል።

በጥቅሉ የአሜሪካ የምርመራ ቢሮ እ.ኤ.አ. በጁን 16 ቀን 2022 ከሜኔንዴዝ ቤት በድምሩ 486,461 ዶላር፣ አንድ ወቄት የሚመዝኑ 11 የወርቅ አሞሌዎችንና አንድ ኪሎ ግራም የሚመዝኑ ሁለት የወርቅ አሞሌዎችን በቁጥጥር ሥር አውሏል።

በአጠቃላይ የኒው ጀርሲው ሴናተር ቦብ ሜኔንዴዝ የውጭ መንግሥት ፍላጎትን ለመፈጸም ሥልጣናቸውን መጠቀም፣ ጉቦ መቀበል፣ ማጭበርበር፣ ፍትሕን ማደናቀፍን ጨምሮ በ16 የወንጀል ድርጊቶች የተከሰሱ ሲሆን፣ ባለፈው ማክሰኞ በሁሉም ክሶች ጥፋተኛ ተብለው ተበይኖባቸዋል።

የቅጣት ውሳኔውን ለማስተላለፍ ለመጪው ጥቅም ወር 2017 ዓ.ም. ቀጠሮ የተያዘ ሲሆን፣ ሴናተሩ በትንሹ ከ20 ዓመት በላይ እስር ሊፈረድባቸው እንደሚችል ሲኤንኤንን ጨምሮ የተለያዩ የአሜሪካ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

Credit - Reporter Newspaper

@tikvahethiopia