TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነርነት ከቀረቡት ዕጩዎች መካከል 42ቱን መለየቱን የም/ቤቱ አፈ-ጉባኤ የተከበሩ አቶ ታገሰ ጫፎ ዛሬ አሳውቀዋል። አቶ ታገሰ ፥ ከመላው የሀገሪቱ ክፍሎች 632 የእጩ ኮሚሽነሮች ጥቆማ መቅረባቸውንና አብዛኛዎቹ ስራውን ለመስራት የሚያስችል ልምድና ዕውቀት ያላቸው መሆኑን መገንዘብ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡ አዋጁ ለአፈ-ጉባኤውና ለአፈ…
#አሁን

በቅርቡ ለተሾሙ የሚሲዮን መሪዎች የተዘጋጀ ስልጠና እየተሰጠ ነው።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፤ በቅርቡ በተለያዩ ሀገራት ለተሾሙ የሚሲዮን መሪዎች እንዲሁም በዋናው መ/ቤት በተለያዩ የስራ ኃላፊነት ላይ ለተመደቡ የስራ ኃላፊዎች ያዘጋጀው ስልጠና ዛሬ መሰጠት መጀመሩን ገልጿል።

በቅርቡ ጄነራል ባጫ ደበሌ ፣ ጄነራል ሀሰን ኢብራሂም ፣ ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ፣ አቶ ደሴ ዳልኬ እና አቶ ተፈራ ደርበውን ጨምሮ ሌሎችም ግለሰቦች የባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደርነት ሹመት እንደተሰጣቸው እንዲሁም ሌሎችም ግለሰቦች በአምባሳደርነት ሹመት እንደተሰጣቸው ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

የሥራ ፈጠራ ውድድር !

የ2ኛ ዙር " አሁን/Ahun " የዲጂታል አንተርፕነሮች የሀሳብ ማበልፀጊያ ፕሮግራም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (#UNDP) አጋዥነት ጀምሯል።

በመጀመሪያ ዙር ተካሂዶ በነበረው ውድድር አሸናፊዎችን ለሥራ ያበቃው ይኸው መርሃግብር #አሁን ሁለተኛ ዙር የሥራ ፈጠራ ውድድር በይፋ መጀመሩን ተነግሯል።

ፕሮግራሙ የ4 ወር የሀሳብ ማበልፀጊያ ድጋፍና የሥራ ማስጀመሪያ ሽልማት ያካትታል፡፡

አዳዲስ እና ችግር ፈቺ የሆኑ የዲጂታል የሥራ ሃሳብ ያላችሁ አመልካቾች በውድድሩ መሳተፍ ትችላላችሁ ተብሏል።

የማመልከቻ ቅጹን ለማግኘት ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ : https://enkopa.org/high-growth/ አለያም በመልዕክት ሳጥን ቁጥር 25534 ቅፁን ሞልቶ መላክ እንደሚቻል ተገልዬ።

ምዝገባው የሚጠናቀቀው ሐምሌ 24, 2014 ዓ/ም ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት የሀገር በቀልና የውጭ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን በማስተባበር 60 ልዑካንን በመያዝ መቐለ ገብቷል። የጉዞው ወነኛ አላማዎች በትግራይ ያለው የሰብአዊ እና መልሶ ግንባታ እና መልሶ ማቋቋም ፈተናዎችና ሁኔታዎች በክልሉ ካሉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ለመስማትና ለመረዳት ነው። የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በስፍራው ስለሚገኙ ሂደቱን እየተከታተሉ ያሳውቁናል።…
#አሁን

አሁን በመቐለ ከተማ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ም/ቤት ልዑክ ከትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር ምክክር እያደረገ ይገኛል።

የትግራይ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ህብረት / ACSOT የቦርድ ሊቀመንበር እና የትግራይ ልማት ማህበር ዋና ዳይሬክተር ተስፋይ ገብረ እግዚያብሔር ውይይቱን ሲከፍቱ ከተናገሩት ፦

" ስለደርሰብን ስብራት ኣብዝተን በማውራት የምንቀይረው ብዙ ኣይኖርም።

በትንሹ ከተግባባን፣ በብዙ ከሰራን በመከራ ላይ ላለው ህዝባችን ልንደርስለት እንችላለን።

ሁኔታው ልትገነዘቡ የመጣቹህ እንግዶች፣ ትላንት ዕዱልን ኣጥታቹህ ሞራላዊና ህጋዊ ግዴታቹ ሳትወጡ ለቀራቹህ ሁሉ፣ ዛሬም ህዝባችን ስቃይ ኣለበቃም እና፣ ድምፃቹህ፣ እውቀታቹህ፣ ጉልበታቹህ ያስፈልገዋል እና

✓ መጠልያ ውስጥ ያሉት ወደ ቀያቸው፣ የተሰድዱትም ወደ ኣገራቸው

✓ ተማሪዎች ወደ ናፈቃቸው ትምህርታቸው፣ ሰራቶኞችም ወደ ስራቸው፣

✓ ህመምተኞች የሚፈልጉት መድሃኔት እንዲያገኙ፣ የተማላ የምግብ ኣቅርቦት እንዲኖር፤

✓ ነፃ የዜጎችና የሸቀጦች እንቅስቃሴ እንዲኖር፣ የባንክ ኣገልግሎት እንዲጀመር በፍፁም ቅንነት ድምፃቹ እንድታሰሙ፣ የምትችሉትን ሁሉ እንድትሰሩ በታላቅ ትህትና እጠይቃቸዋለሁኝ፣ ትችላላቹም። "

(ሙሉ ንግግራቸው ከላይ ተያይዟል)

Photo : Tikvah Family (Mekelle)

@tikvahethiopia
#EOTC #አሁን

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአሁኑ ሰዓት በወቅታዊ ጉዳይ መግለጫ እየሰጠች ነው።

ቤተክርስቲያኗ ፤ ከሃያ (20) ዓመታት በላይ በጅማ የም ኮንታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመሆን የሚያገለግሉት ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ዛሬ በጅማ ዞን  ፖሊስ ታስረው መዋላቸውን ገልጻ ድርጊቱን በፅኑ አውግዛለች።

በአሁኑ ሰዓት ሊቀ ጳጳሱ #በግዳጅ ከጅማ እንዲወጡ መገዳቸውን እና ከሊቀ ትጉሃን ታጋይ ታደለ የኢትዮጵያን የሃይማኖት ተቋማት ጠቅላይ ጸሐፊ ጋር ወደ አዲስ አበባ በመመለስ ላይ መሆናቸውን ቤተክርስቲያኗ አሳውቃለች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙሃን ድርጅት ፤ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ከክልል የተሰጠ ትዕዛዝ ነው በማለት በነገው እለት በጅማ የቅድስት ድንግል ማርያም ሕንጻ ቤተመቅደስ ቡራኬ ቤተክርስቲያን ሳያከናውኑ በፀጥታ ኃይሎች ወደ አዲስ አበባ  እንዲመለሱ የተገደዱት ብሏል።

በተጨማሪ ቤተክርስቲያኗ በሰጠችው መግለጫ " በሕገ ወጥ ከተሾሙ አባቶች መካከል ይቅርታ ጠይቀው የተመለሱትና ቅዱስ ሲኖዶስ ይቅርታቸውን የተቀበለው መጋቤ ሐዲስ አባ ጸጋዘአብ አዱኛ ከመንበረ ፓትርያርክ ማረፊያ ተይዘው ወዳልታወቀ ሥፍራ ተወስደዋል " ስትል ገልፃለች።

በመግለጫው መንግሥት ሕግ የማስከበር ኃላፊነቱን እንዲወጣ የጠየቀች ሲሆን ቅዱስ ፓትርያርኩ በሚገኙበት ግቢ አፈና መፈጸሙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኦርቶዶክሳውያንን ያሳዘነ ነው ብላለች።

#Update : መጋቤ ብሉይ ወሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ ታፍነው ከተወሰዱበት ተለቅቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#አሁን

የኢፌዴሪ ብሄራዊ የተሃድሶ ኮሚሽን ከባለድርሻ እና አጋር አካላት ጋር የቀድሞ ተዋጊዎችን የመልሶ ማቋቋም ሂደት ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በመቐለ እያካሄደ ይገኛል።

ፎቶ፦ ትግራይ ቴሌቪዥን / ድምፂ ወያነ

@tikvahethiopia
#አሁን

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 11ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ነው።

የም/ ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን እየቀረቡ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቀረቡላቸው ጠያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

እስካሁን ፦

- ከኦነግ ሸኔ፣
- ከአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ፣
- ከሰሜኑ የሰላም ስምምነት፣
- ከዜጎች መፈናቀልና ግድያ፣
- ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ ስለተከለከሉ ዜጎች፣
- አርሶ አደሩ ምርቱን ለመሸጥ ከመቸገሩ ጋር በተያያዘ፣
- ወደ አዲስ አበባ ምርት እንዳይገባ ከመከልከሉ ጋር፣
- ከክልሎች የርስ በርስ መናበብ አለመቻል፣
- የሱዳን ወታደሮች ወረው የያዙትን የኢትዮጵያ መሬትና ያወደሟቸውን ንብረቶች የተመለከቱ ጥያቄዎች ቀርበዋል።

አሁንም የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄዎችን በማቅረብ ላይ ናቸው። 

#ኢፕድ

@tikvahethiopia
#አሁን

በትግራይ ስለተፈፀሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እና የሽግግር ፍትህ በማረጋገጥ ሂደት ዙርያ ያለመ የውይይት መድረክ በመቐለ እየተካሄደ ይገኛል።

ውይይቱ ፤ የፍትህ ሚኒስትሩን ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለን ያካተተ የፌደራል ልኡካን ቡድን እንዲሁም የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የመንግስት ከፍተኛ ኃላፊዎች በተገኙበት እየተካሄደ እንደሚገኝ ድምፂ ወያነ ዘግቧል።

ፎቶ፦ ትግራይ ቴሌቪዥን

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
* Update በሸገር ከተማ ስለፈረሱት መስጂዶች ከኦሮሚያ ክልል አመራሮች ጋር 5 ሰዓታት የፈጀ ውይይት መደረጉ ተሰምቷል። ዛሬ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም የተመራ ልዑክ በኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት በአቶ ሽመልስ አብዲሳ ከተመራ የኦሮሚያ ክልል የሥራ ሀላፊዎች ጋር በሸገር ከተማ ስለፈረሱት መስጂዶች ጉዳይ ከቀኑ 9:00 እስክ ምሽት 2:00 ሰዓት ድረስ…
#አሁን

" በሸገር ከተማ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ብዛት ያለው መስጂድ ፈርሷል " - ሼህ ሐጂ ኢብራሂም

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም የተመራ ልዑክ ከኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት በአቶ ሽመልስ አብዲሳ የተመራ የኦሮሚፓ ክልል የሥራ ሀላፊዎች ጋር በሸገር ከተማ ስለፈረሱት መስጂዶች ጉዳይ የደረሱበትን ሁኔታ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ እየተሰጠ ነው።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ባደረጉት ንግግር ፤ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ብዛት ያለው መስጊድ መፈረሳቸውን ገልፀዋል።

በንግግራቸው ፤ ድርጊቱን በመቃወም ሁሉም ሙስሊም ላደረገው ተጋድሎ በኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ስም አመስገነዋል እንዲሁም ለመላው ሙስሊም መፅናናትን እና ሰብረን ተመኝተዋል።

መግለጫው አሁንም ቀጥሏል።

Credit : Harun Media

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#አሁን

የነባሩ ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባኤውን በወልቂጤ እያደረገ ነው።

ነባሩ ክልል ስያሜውን ወደ " ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል " የሚለውጥ ሲሆን ፦
- ህገ መንግስት ማሻሻያ ረቂቅ ሰነድን መርምሮ ማፅደቅ፣
- የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የአስፈፃሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን የወጣ ረቂቅ አዋጅ ቀርቦ ውይይት በማድረግ ማፅደቅ
- ልዩ ልዩ ሹመቶችን መስጠት የምክር ቤቱ ዋና ዋና አጀንዳዎች መሆናቸውን የደ/ሬ/ቴ/ድ ዘግቧል።

ከነባሩ ክልል / ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጋር ተያይዞ የተቋማት መቀመጫዎች ጉዳይ የሰሞኑን አነጋጋሪ ጉዳይ እንደነበር ይታወሳል።

በተለይም በከምባታ ጠምባሮ ዞን በኩሉ ድልድሉ ፍትሐዊ አይደለም በሚል ተቃውሞ ተነስቶ ነበር። ከምስርታው ጉባኤ በፊት በህዝቡ ዘንድ ለተነሱ ቅሬታዎች ምላሽ እንዲሰጥ ተጠይቆ ነበር።

የዞን ምክር ቤቱም ድልድል የሠራው የጋራ ኮሚቴ በፍትሐዊነት የቢሮዎች ምደባን አላደረገም በሚል የፍትሃዊነት ጥያቄ ያነሳ ሲሆን በክፍፍሉ ጉዳይ የፌዴራሉ አካል ጣልቃ እንዲገባ በመስማማት ይህንን የሚጠይቅ ደብዳቤ በፅሁፍ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት እና ለጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት አስገብቷል።

በሌላ በኩል ፤ 6 ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች በአንድ ክልል ለመደራጀት በተስማሙት መሠረት አዲሱ የ " ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል " የምስረታ ጉባኤ በጋሞ ዞን አርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

ፎቶ ፦ ደ/ሬ/ቴ/ድ

@tikvahethiopia
#አሁን #ሲዳማ

የሲዳማ ክልል ም/ ቤት አስቸኳይ ጉባዔ በሀዋሳ እያካሄደ ነው።

ምክር ቤቱ 6ኛ ዙር 3ኛ የስራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ነው እያካሄደ ያለው።

ለአንድ ቀን ብቻ ይካሄዳል በተባለው በዚህ አስቸኳይ ጉባኤ በሶሰት የተለያዩ አጃንዳዎች ላይ ውይይት ይደረጋል ተብሏል።

- ለጉባኤው ሞሽን ቀርቦ ይጸድቃል።

- የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ የስራ ሃላፊዎች ሹመት ለምክር ቤቱ አቅርበው ያፀድቃሉ።

- የምክር ቤቱ አባላት #የህግ_ከለላ ማንሳት ላይ ተወያይተው ውሳኔ ይሰጣሉ።

#ኢዜአ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#HoP ነገ ማክሰኞ ጥዋት ከ2:00 ሰዓት ጀምሮ የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል። ምክር ቤቱ ስብሰባውን የሚያካሂደው የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ይሰጣሉ ተብሏል። @tikvahethiopia
#Update #አሁን

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 3ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባ እየተካሄደ ነው፡፡

ስብሰባው የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ነው እየተካሄደ የሚገኘው።

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላትም ጥያቄዎችና አስተያየቶችን እያቀረቡ ይገኛሉ።

እስካሁን ባለው ከተወካዮች ም/ ቤት አባላት ምን ምን ጉዳዮች ተነሱ ?

- የኦሮሚያ እና አማራ ክልል የፀጥታ ሁኔታ ፣

- የሀገራዊ ትርክት ጉዳይ ፣

- የዜጎች ደህንነት ጉዳይ፣

- በየቦታው ያሉና ህዝቡን ሰላም እየነሱ ያሉ ታጣቂዎችን በተመለከተ ምን እየተሰራ እንዳለ፤

- የትምህርት ጥራት አፈፃፀም፣ የመፅሀፍት እና የቁሳቁስ እጥረት ጉዳይ፣ በተጨማሪ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች እጣፈንታ ምንድነው ?

- ከባህር በር ጉዳይ ጋር ተያይዞ እንዲሁም በአጠቃላይ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ስላለው የዲፕሎማሲ ሁኔታ፤

- ሰፊ የሀብት ብክነት እና ሌብነት የሚታይባቸው እንደ መሬት አስተዳደር፣ ገቢዎች  ፣ የጉምሩክ አገልግሎት ፣ ትላልቅ ግዢዎችና ትላልቅ የኮንስትራክሽን ስራዎች ከሌብነት እና ብክነት ለማፅዳት መንግስት ስለያዘው አቋም ፤

የሚመለከቱ ጥያቄዎች እና ሀሳቦች ተነስተዋል።

የሚሰጡት ምላሾችን እና ሌሎች ሀሳቦችን ተከታትለን እናቀርባለን።

@tikvahethiopia
#አሁን

የኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን እያካሄደ ይገኛል።

በስበስባው ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን በምክር ቤት አባላት ጥያቄዎች እየቀረበላቸው ይገኛሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርብላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ይሰጣሉ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray " ጊዚያዊ አስተዳደር ተቆጥረው የተሰጡት ስራዎች አሉት ፤ ስራዎቹን ፍፅሞ ስልጣኑ ያስረክባል " - አቶ ጌታቸው ረዳ ትናት የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ ፤ ከነሀሴ 9 አስከ 11/2016 ዓ.ም  " ትግራይ ከአስከፊውና ደም አፋሳሽ  ጦርነት ወደ ከፍታ ወይስ ወደ ብዥታ ጉዞ !! " በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የትግራይ ሙሁራን ማህበር ያዘጋጀው የውይይት መድረክ…
#አሁን : በመቐለ ከተማ በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ምክትል ሊቀ መንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ በወቅታዊ የህወሓት የፓለቲካ ሁኔት ላይ ያተኮረ ውይይት እየተካሄደ ነው።

በውይይቱ መድረኩ ላይ " 14ኛው የህወሓት ጉባኤ ህጋዊ አይደለም " ብለው የተቃወሙ ፦
➡️ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ፣
➡️ የድርጅቱ የማእከላዊ ቁጥጥር ኮሚሽን ፣
➡️ የክልል ፣ የዞን ፣ የወረዳና ሌሎች አመራሮች በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል።

የህወሓት ምክትል ሊቀ-መንበር ጌታቸው ረዳ፥ " የውይይት መድረኩ ህወሓትን ለማዳንና ትግራይን ወደ ነባራዊ ሁኔታዋ ለመመለስ ወሳኝ ነው " ማለታቸውን ከድምጺ ወያነ ቴሌቪዥን የተገኘው መረጃ ያሳያል።

ተጨማሪ ይኖረናል።

የፎቶ ባለቤት ፦ ድምጺ ወያነ

@tikvahethiopia