#ጥቆማ

የሥራ ፈጠራ ውድድር !

የ2ኛ ዙር " አሁን/Ahun " የዲጂታል አንተርፕነሮች የሀሳብ ማበልፀጊያ ፕሮግራም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (#UNDP) አጋዥነት ጀምሯል።

በመጀመሪያ ዙር ተካሂዶ በነበረው ውድድር አሸናፊዎችን ለሥራ ያበቃው ይኸው መርሃግብር #አሁን ሁለተኛ ዙር የሥራ ፈጠራ ውድድር በይፋ መጀመሩን ተነግሯል።

ፕሮግራሙ የ4 ወር የሀሳብ ማበልፀጊያ ድጋፍና የሥራ ማስጀመሪያ ሽልማት ያካትታል፡፡

አዳዲስ እና ችግር ፈቺ የሆኑ የዲጂታል የሥራ ሃሳብ ያላችሁ አመልካቾች በውድድሩ መሳተፍ ትችላላችሁ ተብሏል።

የማመልከቻ ቅጹን ለማግኘት ከዚህ በታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ : https://enkopa.org/high-growth/ አለያም በመልዕክት ሳጥን ቁጥር 25534 ቅፁን ሞልቶ መላክ እንደሚቻል ተገልዬ።

ምዝገባው የሚጠናቀቀው ሐምሌ 24, 2014 ዓ/ም ነው።

@tikvahethiopia