TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#EOTC

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ፤ ዛሬ በይፋዊና በተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ያወጣው " የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልአተ ጉባኤ "ን የተመለከተ መረጃ ግርታን ፈጥሯል።

መምሪያው ፤ ቅዱስ ሲኖዶስ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ እና በአዲስ አበባ አቅራቢያ ያሉ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ለሐምሌ 5 ቀን 2015 ዓ/ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት በቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ ለአስቸኳይ የምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ እንዲገኙ መጥራቱን ይገልጻል።

ነገር ግን ይህን መረጃ ያሳወቀው ዛሬ ሐምሌ 6 ቀን 2015 ዓ/ም ነው።

ስብሰባው ለትላንት (ረቡዕ) የተጠራ መሆኑን የሚገልፁ የተለያዩ መረጃዎች በትላንትናው ዕለት ወጥተው ነበር።

መምሪያው ጉባኤው ትላንት ተደርጎ እንደሆነ እና ስለ ተላለፈው ውሳኔ አልያም ያወጣው መረጃ የቀን ስህተት ያለበት መሆኑና ዛሬ የሚደረግ ጉባኤ እንደሆነ የሰጠው ማብራሪያ የለም።

መምሪያው ባሰራጨው መረጃ ላይ ፤ የቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ የአስቸኳይ ስብሰባ ጥሪ እንዲተላለፍ ውሳኔውን ያሳለፈው  በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት ባሳለፍነው ሰኞ ወደ ትግራይ ክልል ለእርቀ ሰላም ጉዳይ በቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት የተጓዘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የልዑካን ቡድን የገጠመውን እክል ከገመገመ በኋላ አሁን ያለው የቤተክርስቲያኗን ወቅታዊ ሁኔታ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውይይትና ውሳኔ እንደሚያስፈልገው በማመኑ ነው ብሏል።

በአስቸኳይ ጉባኤ ላይ በሚደርሰው ስምምነት አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አህጉረ ስብከት ያሉ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ሊጠሩ እንደሚችሉ ተገልጿል።

የመምሪያው መረጃ እስካሁን በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ያለ ሲሆን አስቸኳይ ጉባኤው ትላንት ስለመደረጉ አልያም የወጣው መረጃ የቀን ስህተት ኖሮበት ዛሬ የሚደረግ ስለመሆኑ የተደረገ ማስተካከያ የለበትም።

(መምሪያው ያሰራጨው መረጃ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በትግራይ ያሉ አባቶች የፊታችን ሐምሌ 9 ቀን 2015 ዓ/ም በቅድስት ከተማ አክሱም ፅዮን የኤጲስ ቆጾሳት ምርጫ ለማድረግ ዝግጅት ላይ መሆናቸው ተሰምቷል። በክልሉ ለሚገኙ ሚዲያዎችም በስነስርዓቱ ላይ እንዲገኙ ጥሪ መቅረቡን ለማወቅ ተችሏል። በትግራይ ያሉ አባቶች ከማዕከል በመነጠል " የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤቤተክርስቲያን የመንበረ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ከፍተኛ ቤተ ክህነት " በሚል እየተንቀሳቀሱ…
#EOTC

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ሐምሌ 5 እና 6 ቀን 2015 ዓ/ም አስቸኳይ ስብሰባ ማካሄዱ የታወቀ ሲሆን ይህን ከስብሰባው መጠናቀቅ በኃላ መግለጫ ሰጥቷል።

ቅዱስ ሲኖዶስ በመግለጫው :-

በትግራይ በሚገኙ አህጉረ ስብከት የተመደቡ አባቶች የቅዱስ ሲኖዶስ የሰላም ጥሪን ቸል ከማለት ባሻገር ሐምሌ 9 እናደርገዋለን ያሉት የኤጲስ ቆጶስነት ምርጫ ሕገ ቤተክርስቲያንን ያልተከተለ መሆኑን ገልጾ የሚመለከታቸው አካላት ሂደቱን በማስቆም ከቤተክርስቲያን ጎን እንዲቆሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን አቅርቧል።

ይደረጋል የተባለው የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን አንጻር ተገቢ ያልሆነ የቤተ ክርስቲያንን ማዕከላዊነት የሚጥስ፣ የቤተ ክርስቲያንን አንድነት የሚጎዳና በጦርነት የተጎዳውን ሀብት ንብረቱ የወደመበትን ገዳማቱና አብያተ ክርስቲያናቱ የተጎዱበትን ሕዝብ የማይጠቅም ተገቢነት የሌለው በመሆኑ እንዲቆም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

በትግራይ ክልል ተከስቶ የነበረውን ችግር የፌዴራል መንግሥትና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ችግሩን በውይይት የፈቱት መሆኑ እየታወቀ የሰላም ባለቤት የሆነችው ቤተ ክርስቲያን እስካሁን ሰላም መፈለጓ ያልተቋረጠ ቢሆንም አለመሳካቱ የሚያሳዝን በመሆኑ ለሰላም የሚደረገው ጥረት ዘላቂ መፍትሔ እስከሚገኝ ድረስ የማይቋረጥ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ገልጿል።

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና ክቡር አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እንዲሁም የፌዴራልና የክልሉ መንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እየተደረገ ያለውን ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ያልተከተለ የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ እንዲያስቆሙ ብሎም ሰላም ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ ችግሮቹ በውይይት እንዲፈቱ መንግሥታዊ እገዛ በማድረግ የውይይት መድረክ እንዲያመቻቹ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጥሪውን አቅርቧል።

ቅዱስ ሲኖዶስ፤ " በመላው ዓለም የምትገኙ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ሕዝበ ክርስቲያን እናት ቤተ ክርስቲያናችሁ ያስተላለፈችውን የሰላም ጥሪ ተግባራዊ ሆኖ አንድነቷ ጸንቶ ይኖር ዘንድ በጸሎት ተግጋችሁ ከቤተ ክርስቲያናችሁ ጎን እንድትቆሙ " ሲል ጥሪ አስተላልፏል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#EOTC

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕርዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በክልል ትግራይ ጉዳይ ከተናገሩት ፦

" የኢፌዴሪ መንግሥት  ትናንት ተፈጥሮ በነበረው የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት ችግር (ኦሮሚያ ላይ) በውይይትና በምክክር  በከፍተኛ ኃላፊነት እንዲፈታ ማድረጉን ይታወሳል።

አሁንም በትግራይ  ክልል ባሉ የአህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳትና ሊቃውንት እየተከተሉት ያለውን መፍትሔ የማይሆነውን ችግር  በማስቆምና ሰላማዊ የውይይት መድረኮችን በማመቻቸት የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ እምነታችን ነው።

ይህ ካልሆነ ግን በታሪክ የቤተ ክርስቲያንን አንድነትን ማን ከፋፈለ ሲባል የፌደራልና የክልሉ መንግሥት የሚል የታሪክ ተወቃሽ ሆኖ በታሪክ የሚመዘገብ ይሆናል።

ስለሆነም ይህን በትግራይ ክልል ይፈጸማል የሚባለውን ከቀኖና ቤተ ክርስቲያንና ሕገወጥ የሆነ ሹመት እንዲቆም ብሎም ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ በማመቻቸት ታሪካዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ ቤተ ክርስቲያን ታሳስባለች። "

(ብፅዕ አቡነ አብርሃም የሰጡት ቃል ከላይ ተያይዟል)

በትግራይ ያሉ ብፁአን አባቶች በትግራይ ከነበረው ጦርነት ጋር በተያያዘ ከማዕከል ተነጥለው " የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ከፍተኛ ቤተ ክህነት " በሚል እየተንቀሳቀሱ መሆኑ ይታወቃል።

በቅርቡ በኣክሱም በተካሄደው ስነስርዓት ለዛው ለትግራይ የሚመደቡ 5 እንዲሁም ለውጭ ሀገር 5 በድምሩ 10 የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ አካሂደው የነበረ ሲሆን በቀጣይ ሹመት ይሰጣሉ ተብሏል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ቅዱስ ሲኖዶስ በኣክሱም የተካሄደው ምርጫ አሁን እየተደረገው ያለው የሹመት እንቅስቃሴ ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን አንጻር ተገቢ ያልሆነ የቤተ ክርስቲያንን ማዕከላዊነት የሚጥስ፣ የቤተ ክርስቲያንን አንድነት የሚጎዳና ሕገወጥ ድርጊት መሆኑን በመግለፅ #እንዲቆም እያሳሰበ ነው።

የፌዴራል መንግሥት እና የትግራይ አስተዳደር የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ ዛሬ የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ በጸሎት ተከፍቷል። " የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ በክልል ትግራይ ባሉ አህጉረ ስብከት ለመንፈሳዊ አገልግሎት ተመድበው የነበሩ አራት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በፈጸሟቸው የቀኖና ቤተክርስቲያን እና የሕግጋተ ቤተክርስቲያን ጥሰቶች ዙሪያ ለመወያየትና ሕግጋተ ቤተክርስቲያንን መሠረት ያደረጉ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ ጉባኤውን…
#EOTC

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ፅህፈት ቤት ዛሬ በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ፤ " ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፤ ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ/ም በተጠራው አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ሊያቀርቡት የነበረው አባታዊ ቃለ በረከት " በሚል 6 ገጾች ያሉት መልዕክት አሰራጭቷል።

በዚህ ቅዱስነታቸው " ሊያቀርቡት ነበር " በተባለው መልዕክት ዙሪያ / ለምን እንዳልቀረበ  ዝርዝር መረጃ ፅ/ቤቱ አልሰጠም።

ከቅዱስነታቸው አባታዊ ቃለበረከት የተወሰደ


" በትግራይ ክልል ጦርነት ወቅት በጦርነቱ ውስጥ ላሉ ብፁዓን አባቶች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ እንዲሁም ምእመናን ድምፅ መሆን አልቻልንም።

በትግራይ ክልል ያለው ታሪክና ገዳማት የቤተ ክርስቲያናችን የታሪክ መነሻ ሆነው ሳለ ከአክሱም ጽዮን ጀምሮ በመላ ትግራይ ስለ ተፈጸመው እልቂት፣ ስለ ገዳማቱ መፍረስ፣ ስለ ቅርሶች መውደም አልተቆጨንም፣ ድምጽም አልሆንም።

አንዳንድ አባቶችም በጊዜያዊ ስሜት ተነሳስተው ለተናገሩት ይቅርታ እንዲጠይቁ ለማድረግ ወይም ንግግራቸው ስህተት ነው ብለን መግለጫ ለመስጠትም አልፈቀድንም።

እኔም የሁሉም አባት እንደመሆኔ መጠን የትግራይ ክልል ሕዝብም ሕዝባችን ስለሆነ እና ቤተ ክርስቲያንም እንዳትወቀስ በማሰብ ከአንድም ሦስት ጊዜ በአጀንዳ ተይዞ እንድንነጋገርበት ለቋሚ ሲኖዶስ ሀሳብ ባቀርብም ተቀባይነት አላገኘም፡፡

የአባትነት ኃላፊነት ስላለብኝ ይህ ሁሉ ግፍና በደል እየተፈጸመ ዝም ማለት የለብኝም ብዬ በሚድያዎች ድምጼን ለማሰማት ብፈልግም ፈቃድ አልተሰጠኝም፡፡

በዚህ መሃል ባገኘኋት አጋጣሚ ' በዓለም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ በትግራይ ክልል ግፍ እየተፈጸመ ነው፣ ሕዝቡ እየተጨፈጨፈ ነው፤ ገዳማትና አድባራት እየፈራረሱ ነው፣ ቀሳውስትና መነኮሳት በቤተ መቅደስ ውስጥ ሳይቀር እንደ ዘካርያስ በጭካኔ እየተገደሉ ነው፣ መተኪያ የማይገኝላቸው ቅርሶቻችንም እየወደሙ ነው... ' በማለት የተሰማኝን ኃዘን ገለጽኩ፣ መግለጫዎችንም በተደጋጋሚ ሰጠሁ፡፡

በማግስቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የሃገሪቱን ሚድያዎችን በይፋ በመጥራት፡- ' በፓትርያርኩ የተሰጠ መግለጫ የግላቸው እንጂ ቅዱስ ሲኖዶስን ወይንም ቤተ ክርስቲያንን አይወክልም ' የሚል መግለጫ ሰጡ፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስም ድርጊቱን በዝምታ ከማለፍ ውጪ ምንም ተግሳጽ ስላላስተላለፈ የትግራይ ክልል ሊቃነ ጳጳሳትና ሕዝቡ ወደ ከፍተኛ ቅሬታ እንዲገቡ ምክንያት ሆኗል። "

(የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ፅ/ቤት ያሰራጨው የቅዱስነታቸው ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ጾመ ፍልሰታ እና የቅዱስ ፓትርያርኩ መልዕክት ! በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፤ " የጾመ ፍልሰታ " መልዕክት አስተለልፈዋል። ከመልዕክታቸው የተወሰደ ፦ " . . . እንደ እግዚአብሔር ቃልም እንደ አባቶቻችን ትውፊትም የጾመ…
#EOTC

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፤ እግዚአብሔር ለኢትዮጵያ ሰላምን ይሰጥ ዘንድ ክርስቲያኖች ከመጠላላት ርቀው #በፍቅር እንዲኖሩ እና #ሰላማውያን እንዲሆኑ አሳሰቡ።

ቅዱስ ፓትርያርኩ ይህንን ያሳስቡት ዛሬ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የጾመ ማርያም ሱባኤ ማጠናቀቂያ በዓል ላይ ነው።

ቤተክርስቲያንኗ ፤ " በኢኦተቤ በዐዋጅ ከተደነገጉት አጽዋማት መካከል አንዱ የሆነውና የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ዕርገተ ሥጋ አስመልክተው ሐዋርያት የጾሙት ጾመ ማርያም በየዓመቱ በወርሓ ነሐሴ ከመባቻው አንስቶ ባሉት 16 ቀናት ካህናት እና ምእመናን ሌሊት በሰዓታት ጸሎት፤ ቀን በሥርዓተ ቅዳሴ በመሳተፍ በሕብረት ያሳልፉታል " ብላለች።

" በዚህ በጾመ ማርያም ወይም በተለምዶ የፍልሰታ ጾም ተብሎ በሚታወቀው ወቅት በርካታ ምእመናን እንዲሁም ሕጻናት በቤተ ክርስቲያን ተገኝተው ሥርዓተ ቅዳሴውን ይከታተላሉ፤ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙን ይቀበላሉ " ስትል ገልጻለች።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ  ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትም በዚህ ሕጻን ዐዋቂው፤ ወንድ ሴቱ የክረምት ብርድ እና ዝናብ ሳይበግረው በሕብረት በሚጸልበት የሱባኤ ወቅት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በመገኘት ሥርዓተ ቅዳሴውን በመምራት እና ምእመናንን በመባረክ ማሳለፋቸውን ተገልጿል።

ቅዱስነታቸው በዛሬው ዕለት ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር  በገዳሙ ተገኝተው በዓሉን ያከበሩ ሲሆን በቅዳሴው መካከል ባስተላለፉት ትምህርትና ቃለ ቡራኬ " የሰላም ባለቤት የሆነው ልዑል እግዚአብሔርን ለኢትዮጵያ ሰላምን ይሰጥ ዘንድ ክርስቲያኖች ከመጠላላት ርቀው በፍቅር እንዲኖሩ እና ሰላማውያን እንዲሆኑ አሳስባለሁ " ብለዋል።

ቅዱስ ፓትርያርኩ በሱባኤው ወቅት የሀገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክተው አባታዊ የሰላም ጥሪ ማስተላለፋቸው የሚታወስ ነው፡፡ 

መረጃ እና ፎቶ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ/ጽ/ቤት የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሀገሪቱ ያሉ ችግሮች በውይይት እና በስምምነት እንዲፈቱ በድጋሚ ጥሪ አቀረበች። ይህ ጥሪ የቀረበው ቅዱስ ሲኖዶስ የጥቅምት 2016 ዓ/ም ጉባኤውን ካጠናቀቀ በኃላ ባወጣው መግለጫ ነው። ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ " ትላንት በሰሜኑ ኢትዮጵያ የሀገራችን ክፍል በተካሄደው ጦርነት በጠፋው የሰው ሕይወትና በወደመው ንብረት ከደረሰብን ሐዘን እኛ ኢትዮጵያውያን…
#EOTC

ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  ቅዱስ ሲኖዶስ በሁሉም የኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ ከህዳር 15 ቀን 2016 እስከ ታህሣሥ 27 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ ጸሎትና ምሕላ እንዲፈጸም መወሰኑ አይዘነጋም።

ይህንን በተመለከተ ዛሬ ቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ሰጥቷል።

ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬ መግለጫው ፤ ቤተክርስቲያን ሰላም ያሳጡን ጦርነቶችና ግጭቶች ዘላቂ መፍትሄ እንዲያገኙና በአጭሩ እንዲቋጩ ጥሪዋን ታስተላልፋለች ፤ እምቢ ባዮችንም ታወግዛለች ዘላቂ መፍትሄ የሚገኝባቸውን ሂደቶችንም ትቀይሳለች ብሏል።

ከዚህ በተጨማሪም ቅድስት ቤተክርስቲያን የጥላቻና ሀሰተኛ ትርክቶችን እንደምታወግዝ አስገንዝቧል።

ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ " የአሁኑ ጸሎተ ምኅላ የሚደረገው ፦
- አለመግባባት በምክክር፣  በውይይት፣ በመደማመጥ እንዲፈታ፤
- መከራን በመረዳዳት እንድንሻገር፣ እንደየ ኃላፊነታችን የሚጠበቅብንን ለመወጣትና የሕዝባችንን ጥያቄ ለመመለስ እንድንችል፣ ችግራችን ሁሉ ተፈትቶ ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ ከሃሊው አምላክ እንዲያግዘን በአንድነት ለመጮኽ ነው፡፡ " ብሏል።

የጾም፣ የጸሎትና የምኅላ አዋጁ ዓለማው መንፈሳዊ ብቻ እንደሆነ ያስገነዝበው ቅዱስ ሲኖዶስ ፤ የሚድያ፣ የትምህርትና የፍትሕ፣ መሰል ተቋማት ይህንን በመረዳት በሚያስፈልገው ሁሉ እንዲተባበሩ በቅድስት ቤተክርስቲያን ስም አሳስቧል።

(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#EOTC

ቋሚ ሲኖዶስ ነገ መግለጫ እንደሚሰጥ አሳወቀ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ነገ መግለጫ ይሰጣል።

መግለጫው በምን ጉዳይ ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ባይገለፅም #በወቅታዊ_ጉዳዮች ዙሪያ እንደሆነ ተነግሯል።

ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ለሚሰጠው መግለጫ መንግስታዊ፣ መንግስታዊ ላልሆኑና በቤተክርስቲያኗ ህዝብ ግንኙነት ለተመዘገቡ መገናኛ ብዙሃን በስፍራው እንዲገኙ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EOTC ቋሚ ሲኖዶስ ነገ መግለጫ እንደሚሰጥ አሳወቀ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ነገ መግለጫ ይሰጣል። መግለጫው በምን ጉዳይ ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ባይገለፅም #በወቅታዊ_ጉዳዮች ዙሪያ እንደሆነ ተነግሯል። ከቀኑ 9:00 ሰዓት ላይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ለሚሰጠው መግለጫ መንግስታዊ፣ መንግስታዊ ላልሆኑና በቤተክርስቲያኗ…
#EOTC

ዛሬ ቋሚ ሲኖዶስ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሠጥቶ ነበር።

በዚህም መግለጫ ፤ በአርሲ ዞን ሹርካ ወረዳ ስለተፈፀመው የበርካታ ምዕመናን ግድያ ፣ በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የጎንደር ዓቢየ እግዚእ ኪዳነ ምሕረት የቋቋም መምህር የሆኑት የመምህር ፍሥሃ አለምነው ባልታወቁ አካላት የተፈፀመው ግድያ ተነስቷል።

በተጨማሪ፤ በወለጋ፣ በጎንደር፣ በጎጃም ፣ በወሎ ፣ በሰሜን ሸዋ በመሳሰሉት እየተፈፀመ ስላለው የመጠፋፋት፣ የሃይማኖት ጥላቻ፣ የንፁሃን መቀጠፍ ድርጊት ተነስቷል።

ቋሚ ሲኖዶስ ግድያ፣ ስደት፣ የንብረት ውድመትና መፈናቀል የዕለት ዜናችን ከሆነ ሰንብቷል ብሏል። 

ይኽ እንዳለ ሆኖ ረሀብ፣ ድርቅ፣ የኑሮ ውድነትና ሥራ አጥነት በተጨማሪ በየቦታው በተፈጠሩ አለመረጋጋቶችና ግጭቶች ምክንያት በርካቶች ቀያቸውን ለቀው፣ መነኰሳት ገዳማትን ትተው ተሰደዋል፤ ወላድ እናቶች፣ ሕሙማንና አረጋውያን በሕክምና እጦት እያለቁ ነው፣ ሕፃናትና ወጣቶች ከጤናማ እድገትና ከትምህርት ገበታ ተደናቅፈዋል ብሏል።

በመሆኑም ፦

- ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ከግጭትና ከጦርነት፣ ከርስ በርስ መገዳደል ወጥተው በውይይትና በምክክር፣ በኃላፊነትና በተጠያቂነት ስሜት የታላቋን ሀገር መልካም ስምና ክብር እንዲሁም የዜጎቿን ሁለንተናዊ ደኅንነት የመጠበቅና የማስጠበቅ ተግባር ቅድሚያ እንዲሰጡ አሳስቧል። 

- በቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ንፁሐን ምእመናንና ተቋማት ላይ ያተኮሩ ጥቃቶች  በአስቸኳይ እንዲቆሙ፣ መንግሥትና የሚመለከታቸው ሁሉ ዋስትና እንዲሰጡ፣ ወንጀል ፈጻሚዎችም ለፍርድ እንዲቀርቡ፣ ድርጊቱንም መላው ዓለም እንዲያወግዘው ጠይቋል።

- የሀገርና የዓለም ሀብት የሆኑ ቅዱሳን መካናት፣ እንደ ፦
° ዝቋላ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣
° ደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም፣
° አሰቦት ደብረ ወገግ አቡነ ሳሙኤል ገዳም እና አካባቢው፣
° ደብረ ሮሐ ቅዱስ ላሊበላ ገዳምና አካባቢው የመሳሰሉ ሁሉ ታላላቅ አድባራትና ገዳማት አደጋ የተጋረጠባቸው በመሆኑ ልዩ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ቋሚ ሲኖዶስ አሳስቧል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

Grap. Tikvah Ethiopia

@tikvahethiopia
#EOTC

በአዲስ አበባ ከተማ እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ኦርቶዶክሳዊ #ወጣት የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ዋዜማን በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል በዝማሬ እና በፀሎት አክብሮ ውሏል።

" ጃንደረባው ትውልድ " በተሰኘ ማህበር አዘጋጅነት በተዘጋጀ " የአእላፋት ዝማሬ " የሚል ስያሜ በተሰጠው መርሃ ግብር እጅግ በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምእመን አብዛኛው #ወጣት በቤተክርስቲያን ተገኝቶ የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ዋዜማን በልዩ #በሃማኖታዊ ስነስርዓት ተቀብሏል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም  የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና ሌሎች ብፁዓን አባቶች ተገኝተው ነበር።

" የጃንደረባው ትውልድ ማኅበር " በቅርቡ በመንበረ ፓተርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የማኅበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ የእውቅና ምሥክር ወረቀት ማግኘቱ ተነግሯል።

ፎቶ፦ TMC / ከማህበራዊ ሚዲያ

@tikvahethiopia
#EOTC

ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ፦

(ባለፈው ዓመት የልደት በዓልን ጨምሮ ሌሎች መንፈሳዊ በዓላት አከባበርን በተመለከተ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ቀርበው የተናገሩት)

" ... ይህንን የልደት በዓል ስናከበር የት ነው የምንሄደው ? ቀድሞ በዓሉን ለማክበር የት ነው የምንሄደው ? ስንል ጭፈራ ቤት አይደለም፣ ሙዚቃ ቤት አይደለም ፣ ይሄ በዓል የሚከበረው በጭፈራም አይደለም፤ በዘፈንም አይደለም፣ በሙዚቃም አይደለም፤ በበዓላችን ላይ ሙዚቃ እየቀላቀላችሁ / ጭፍራ እያስገባችሁ የበዓሉን እሴት / ሃይማኖታዊ ትርጉም የምታበላሹት #የሚዲያ አካላት ናችሁ።

ይሄ በዓል የሚከበረው በጭፈራም አይደለም፤ በዘፈንም አይደለም፤ በሙዚቃም አይደለም።

የበዓሉን ትርጓሜውን ማወቅ ያስፈልጋል። ያን እለት መላእክትና ሰዎች አልዘፈኑም እኮ፣ አልጨፈሩም እኮ ፤ መላእክትና ሰዎች ደስታቸውን የገለጡት በምስጋና ነው። ዕለቱ የሚከበረው በምስጋና ነው። አባቶቻችን የበዓሉን አከባበር ወደኛ ያደረሱት በዚህ መንገድ ነው። እኛም ለትውልድ የምናስተለልፈው በዚህ ሁኔታ ነው።

የበዓሉን መንፈሳዊ ስነስርዓት በጠበቀ መልኩ ወደትውልድ ማስተላልፈ ይኖርብናል።

የበዓሉንም መንፈሳዊ ስነስርዓት እሴት ስንል ለምን ተወለደ ? የት ተወለደ ? ከሚለው ትርጓሜ ይጀምራል፤ ሲወለድ ምን ተከሰተ፣ ምን ተደረገ ? መላዕክት፣ እረኞች፣ ሰባሰገል ምን አደረጉ ? ድንግል ማርያም ምን አደረገች ? እንስሳትስ ምን አደረጉ ? የሚሉትን ነገሮች ነው የምንወስደውና የምናስበው። ስለዚህ እነሱ ያደረጉትን እያደረግን ነው ለትውልድ ማስተላለፍ የሚገባን።

ይህ ለልደት በዓል ብቻ ሳይሆን የ #ጥምቀት በዓልም፣ ሌሎች መንፈሳዊያን በዓላቶቻችን ሁሉ ፣ መንፈሳዊያን በዓላት እስከሆኑ ድረስ በመንፈሳዊ ስነስርዓት ነው ማክበር የሚገባን፣ ሃይማኖታዊ በዓል ብለን እስከሰየምን ድረስ ሃይማኖቱ በሚፈቅደው ስነስርዓት/እሴት ነው በዓላቱ ተከብረው መዋል ያለባቸው፤ ተከብረው ማለፍ ያለባቸው።

ትውልዱም ማወቅ እና መማር ያለበት በእንዲህ ያለ ሁኔታ ነው። "

@tikvahethiopia
#EOTC

ዛሬ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

ብፁዕነታቸው በመግለጫቸው ፤ " በዚህ ወቅት ቤተክርስቲያኗ የተለያዩ ፈተናዎች ገጥመዋታል ፤ በየግል በተለያዩ አባቶች፣ በተለያዩ መንገዶች በሚሰበኩ ስብከቶች ፣ በሚፈጠሩ ሁኔታዎች ፣ ለምን ? እንዴት ? ዝም አልሽ ቤተክርስቲያን በሚልም ትልቅ ፈተና ላይ ነች " ብለዋል።

ቤተክርስቲያን ፈተናዋን እንዴት ማለፍ እንዳለባት በጸሎት እግዚአብሔርን እንጠይቀዋለን ሲሉ ገልጸዋል።

" ባለፈው የተለያዩ አባቶች በተለያየ መንገድ ተናገሯቸው ስለተባሉት ጉዳዮች ተነስቶ መንግስት ቀየሜታውን ገልጾ ቤተክርስቲያን መልስ እንድትሠጥበት አሳስቧል " ያሉት ብፁዕነታቸው " ቤተክርስቲያንም በስፋት፣ በትኩረት ተወያይታበታለች (ቅዱስ ቋሚ ሲኖዶስ) ይሁን እንጂ የብፁዓን ሊቃነጳጳሳት ጉዳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ጉዳይ ነው የሚሆነው ፣ ምክንያቱም አንድ ሊቀ ጳጳስ ተጠሪነቱ ለቅዱስ ሲኖዶስ ስለሆነ፤ ቀርቦ ተጠይቆ አውንታዊ መልስ ሰጥቶ ስህተት ነው ? እውነት ነው ? ብሎ የሚወሰን እንጂ ብግድ ተብሎ በቋሚ ሲኖዶስ ወይም በሌላ የተለያየ መልኩ እንዲህ ነው እንዲያነው ብሎ መናገር ህገ ቤተክርስቲያናችን አፈቅድም " ብለዋል።

" ቤተክርስቲያን ሰላምን መፈለግ ፣ መሻት ፣ መልካም ነገር ማድረግ ነው ከዚህ ውጭ ሌላ አቋም የላትም " ያሉት ብፁዕነታቸው ፤ " እንደ ህግ እና ስርዓታችን በአባቶች ደረጃ ቅዱስ ሲኖዶስ የሚወስነውን ይወስናል። ይህ ቅዱስ ሲኖዶስ ቋሚ ሲኖዶስ ተወያይቶ ቅዱስ ሲኖዶስ የሚለውን እንዲል አልፎታል " ሲሉ አሳውቀዋል።

ብፁዕነታቸው ፤ " አሁን ግራ የሚያጋባው ትላንት ለበዓለ ጥምቀቱ የተሰየመው አብይ ኮሚቴ ከከተማ አስተዳደሩ፣  ከሚመለከታቸው የፀጥታ ኃላፊዎች ጋር ፣ከታላላቅ ባለስልጣናት ጋር ውይይት አድርጎ ነበር። በውይይቱ ይህ ከባድ ፈተና እየተነሳ እንዳለና አሁንም በዓለ ጥምቀቱን ለማክበር ቅድመ ዝግጅት ቤተክርስቲያኒቱ እንዲህ አይነቱን ለይታ እንድታወግዝ ፣ የራሷን መልዕክት እንድታስተላልፍ በመንግሥት አቋም ተይዞ ለአብይ ኮሚቴው ተነግሯል " ብለዋል።

" ቤተክርስቲያን ያራሷ ነፃነት አላት ፣ የራሷ ክብር አላት ፣ የራሷ ነፃ መድረክ ፈላጊ ናት ሁሉም እየተነሳ ያም ይሄን አድርጊ፣ ይሄም ይሄን አድርጊ ስላላት እየተጎተተች የተባለችውን አታስተናግድም " ሲሉ ገልጸዋል።

" ክፉውን ክፉ፣ በጎውን በጎ፣ መልካሙን መልካም ፤ መልካም ያልሆነውን መልካም አይደለም ብላ ለማስተላለፍ የራሷ ህግ ስርዓት አላት " ብለዋል።

" የፈለገ የሚያዛት ፣ የፈለገ የሚያሽከረክራት ፣ ያልወደደ እንደ ወደደ ፍላጎቱን ምኞቱን እንድትፈፅምለት የሚጎትታት ቤተክርስቲያንን ኖራም አታውቅም ወደፊትም ልትኖር አይገባም " ሲሉ ተናግረዋል።

" ቤተክርስቲያን በራሷ ነፃ መድረክ ቆማ ችግሩን ችግር ነው ብላ መናገር አለባት እያደረገችም ነው። " ያሉት ብፁዕነታቸው " ይሄ በፍፅሙ አይመጥነኝም። እንዲህ አይነቱ የኔ ቃል አይደለም ብላ #ታውጃለች ግን በግልፅ መጠየቅ ያለባትን ጠይቃ መናገር ያለበትን እንዲናገር ፈቅዳ ሁሉን ነገር በአግባቡ ታደርጋለች እንጂ በኩርፊያ በአላስፈላጊ ብሂል ይሄን ካላደረግሽ በዓል ለማክበር አልችልም ፣ ከናተ ጋር ግንኙነት የለንም እስከሚባል ድረስ የሚኖረው ነገር ከማንም ከምንም በፍፁም አይጠበቅም " ሲሉ አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EOTC ዛሬ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መግለጫ ሰጥተው ነበር። ብፁዕነታቸው በመግለጫቸው ፤ " በዚህ ወቅት ቤተክርስቲያኗ የተለያዩ ፈተናዎች ገጥመዋታል ፤ በየግል በተለያዩ አባቶች፣ በተለያዩ መንገዶች በሚሰበኩ ስብከቶች ፣ በሚፈጠሩ ሁኔታዎች ፣ ለምን ? እንዴት ? ዝም አልሽ ቤተክርስቲያን በሚልም ትልቅ ፈተና ላይ ነች " ብለዋል። ቤተክርስቲያን…
#EOTC

" ኮብልለው አልሄዱም፣ ኮብላይም አይደሉም ! "

ብፁዕ አቡነ አብርሃም ምን አሉ ?

- ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶክተር) ኮብልለው አልሄዱም፣ ኮብላይም አይደሉም። ለእውነት እና ለፅድቅ ለቤተክርስቲያናቸው አንገታቸውን ከሚሰጡ አባቶች አንዱ እንጂ የሚሸሹ የሚኮበልሉ ፣ የሚደበቁ የወንጀል ሰው ሊሆኑ አይችሉም። አይደሉምም።

- ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በቅዱስ ፓትርያርኩ ፍቃድ፣ እንደ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት አውቆት ለአገልግሎት ቤተክርስቲያን ሊባርኩ ታቦታት ይዘው አስፈቅደው ሰሜን አሜሪካ ሄደዋል። ይሄ ደግሞ ዛሬ ብቻ ሳይሆን በየጊዜው ነው የሚሄዱት።

- ቆም ብላችሁ አድምጡ ! እናተ ለፖለቲካችሁ ብዙ እንደምትሉ ብዙ እንደምታስቡ ሁሉ እኛም ለሰማያዊ መንግሥታችን እንቆማለን ፤ ለምድራዊ መንግሥታችን እንገዛለን በሃይማኖት እስካልመጣብን ድረስ በሃይማኖት ከመጣ ግን መገዛት አይደለም አትገዙ ብለን እናውጃለን። ግን ግድሉ አንልም፣ ተገዳደሉ አንልም፤ ቤተክርስቲያን ቃሏ ስላልሆነ። አትገዙ ግን ትላለች አሁን ግን እዚህ አልደረስንም። ቤተክርስቲያን እያስተማረች ያለችው ሰላምን፣ ፍቅርን ብቻና ብቻ ነው።

- ያለ ስም ስም መስጠት ይሄ ማህበራዊ ሚዲያ በሚባለው ንፋስ ፣ ምንም ጭብጥ በሌለው ሃይማኖታዊውን ሰው ሃይማኖታዊ አይደለም፤ ለቤተክርስቲያን የሚሰራውን ፣ለሀገር የቆመውን ኮበለለ ፣ ከዳ የሚባል ደካማ አስተሳሰብ የቤተክርስቲያን ህልውና አያናግም።

- " ደግሞ ሰምተናል አባ ጴጥሮስ ፣ አባ አብርሃም ... ተለውጠዋል ዝም ብለዋል አድር ባይ ሆነዋል የሚለውን ፤ ከሃይማኖት ውጭ ሌላ ማደሪያ የለንም። ለኛ ማደሪያችን መዋያችን ሃይማኖታችን ናት "

- ለመንግስትን እንደ መንግስት እንድንገዛው መፅሀፍ ቅዱስ ያስገድደናልም በሃይማኖታችን እስካለመጣ ድረስ ሃይማኖታችንም ለመንግስት እንድንገዛ ያስገድደናል።

- ከዚህ ውጭ ከውስጥ የምንሰራውን በይፋ እንዲህ ነው ብለን አናወራም በሚል ዝም ብለናል።

- የወሬ ገበያ ያለው ሰው ሁሉ የወሬ ገበያው እንዲደራ ዛሬ አባ አብርሃም ፣ አባ ጵጥሮስ አልተናገሩም በሚል ሌላ ስም ልስጥ ቢል የሱ ወሬ እንጂ የኛ አይደለም።

- አባ ጴጥሮስ ሆኑ አባ አብርሃም ስራቸውን የሚሰሩት በሃይማኖታቸው መሰረት ብቻ ነው።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#EOTC

ብፁዕ አቡነ አብርሃም ምን አሉ ?

- በዓለ ጥምቀቱን ለማክብረ በመንግሥት ዘንድ ቤተክርስቲያን ይሄን ትበል ፣ አለበለዚያ እንዲህ አይደለም የሚሉ መልዕክቶች ደርሰውናል።

- ቤተክርስቲያን ሰላሟን ታውጃለች።

- አሉ አሉ እየተባሉ ስለተነገሩ ንግግሮች እና ግለሰቦች፣ ጳጳሳት እና ሊቃነጳጳሳት ከሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ታያለች፣ ትመክራለች ታስተምራለች። ህግ አላት በህጓ መሰረት ትገስፃላች። ከዚህ ውጭ ሱሪ በአንገት አውጣው የሚባል ነገር ቤተክርስቲያን አትሸከምም አትቀበለም።

- ሰላሟን እያወጀች፣ ሰላሟን እየሰበከች በሰላም መንገድ ትጓዛለች።

- ሁል ጊዜ ቤተክርስቲያን መሞትን ስራዬ ብላው ይዛ ኖራለች ወደፊትም ሞት ከሆነ በሰላም ለመቀበል ዝግጁ ናት።

- " ይሄን ካደረግሽልኝ ይሄን አደርግልሻለሁ " የሚል መደራደሪያ የላትም ፣ ሊኖራትም አይችልም። ድርድሯ ሰላምና ሰላም ብቻ ነው።

- እኔ ያልኩሽን አድርጊ የሚል በቀኝም ይሁን በግራ ፤ ከገዢውም ክፍል ይሁን እገዛለሁ የሚል ሃሳብ ቢመጣ ያን ተቀብላ የማስተናገድ አቅምም ብቃትም የላትም።

- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች፣ በዓሉ ዓለም አቀፍ ስለሆነ የተለያየ እምነት ያላችሁ ልጆች ፣ የሌላ እምነት ተከታይ ሆናችሁ በዓሉ በዓላችን ነው የምትሉ፣ የምትደግፉ በዓሉን እራሳችሁ አክባሪዎች ፣እራሳችሁ የፀጥታው አስተናጋጆች የሰላም መሪዎች ሆናችሁ በዓሉ በሞቀና በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር ቤተክርስቲያን መልዕክት ታስተላልፋለች።

- የፀጥታ አካላት ትላንት እንዲህ ተብያለሁ ይሄ እንደገና በተቃውሞ ካልታወጀልኝ በስተቀር ይሄን አላደርግም የሚለውን አስተሳሰብ ትቶ ህግን በህግ ስርዓትን በስርዓት ለመፈፀም አእምሮውን አስፍቶ የተሻለ ስራ እንዲሰራ ቤተክርስቲያን መልዕክቷን ታስተላልፋለች።

- ሌላው ሌላው ችግር በመድረክ ዙሪያ፣ ማነው ጥፋተኛ ? ምን አስቦ ነው ? ምን ብሎ ነው ? የሚለውን ቅዱስ ሲኖዶስ የሚመክርበት የሚዘክርበት፣  የሚገሰፀውን የሚገስፅበት ፣ ከቀኖና የወጣውን ከቀኖና ወጥተሃል የሚልበት የራሱ ስርዓት ስላለው ለህጉ እንተወዋለን።

- " ይሄን በሉ ይሄን አድርገ፣ ይሄን ካላደረጋችሁ ይሄን አናደርግም " የሚባል መያዣ ነገር ቤተክርስቲያን አስተናግዳ አታውቅም ፤ ወደፊትም አታስተናግድም።

- እገሌ እገሌ ባልልም ቤተክርስቲያን ቤተክርስቲያን ናት በዓሉም የህዝብ ነው ይሄን መያዣ አናድረግም ችግሩ ችግር ሳይሆን እንዲፈታ ይደረግ በመልካም ነገር በዓሉን በሰላም እናክብር ብለው የተናገሩ መሪዎች አሉ በዚህ አጋጣሚ ሊደነቁ ይገባል። ከመሪዎች የሚጠበቀው ይሄ ነው። ችግርን እንዴት እንፍታው ችግርን እንዴት እናስወግደው ፣ ሰላም እንዴት እናስፍን ነው መባል ያለበት።

- በየሄድንበት " ደግሞ ለኦርቶዶክስ፣ ለተዋሕዶ ቤተክርስቲያን " ቃሉም ይከብዳል በየቢሮው ስንሄድ ቢያንስ አይሆንም አይባልም " ያንን ያንን ያርሙ " ይላሉ።

- " ኦርቶዶክስ ሃገር ናት ፣ ለሀገር ዋልታ ናት፣ ምሰሶ ናት አምድ ናት ይሄን ታሪክ አይክደውም። ዘመን ቢያስረጃትም ዘመን ቢጥላትም ዘመን ያነሳታል።

- ዛሬም ሲደረግላት እያመሰገነች ነው። ለሀገር ሰላም ማድረግ ያለባትን እያደረገች ነው ፤ በየመስሪያ ቤቱ ስንሄድ " ደግሞ ለኦርቶዶክስ " የሚለው ቃል ሊታረም ይገባል።

- ቤተክርስቲያን ትከበር ፣ በቤተክርስቲያን ውስጥም #በሃይማኖት_ስም እንደፈለገ የሚዋኙ ሰዎች ቆም ብለው ያዳምጡ፣ የሚናገሩትንም ይመርምሩ ፣ ሃይማኖታዊ ቃል ነው አይደለም ይበሉ ከሃይማኖታዊ ቃል ውጭ የሆነው ሁሉ የእኛ #አይደለም

#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EOTC ብፁዕ አቡነ አብርሃም ምን አሉ ? - በዓለ ጥምቀቱን ለማክብረ በመንግሥት ዘንድ ቤተክርስቲያን ይሄን ትበል ፣ አለበለዚያ እንዲህ አይደለም የሚሉ መልዕክቶች ደርሰውናል። - ቤተክርስቲያን ሰላሟን ታውጃለች። - አሉ አሉ እየተባሉ ስለተነገሩ ንግግሮች እና ግለሰቦች፣ ጳጳሳት እና ሊቃነጳጳሳት ከሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ታያለች፣ ትመክራለች ታስተምራለች። ህግ አላት በህጓ መሰረት ትገስፃላች። ከዚህ…
#EOTC

" ሀገራችን ሰላም ትሁን፤ የሃይማኖት ሰዎች እንደ ሃይማኖት እናስብ፣ እንደ ሃይማኖት እንናገር፣ አላስፈላጊ ጀግንነትን እንርሳው " - ብፁዕነታቸው

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ምን አሉ ?

- የማይደፈር ሲደፈር አይተናል፤ ቤተክርስቲያን ስትደፈር ዝም አንልም።

- " ፖለቲካው የፖለቲካው መስመር ሲደፈር ዝም እንደማይል ሁሉ እኔም ደግሞ የመጀመሪያዋም የመጨረሻዋም ህይወቴም ማንነቴም ክብሬም ቤተክርስቲያኔ ስለሆናች እሷ ስትደፈር ዝም አልልም። እናገራለሁ፤ የመጣውን በፀጋ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ "

- ከዚህ በፊት ለመንግሥት ችግር ካለ እዚህ ጠቅላይ ቤተክህነት ውስጥ ንገሩን ብለናቸዋል። እኛ እናርማለን፣ እኛው እናስተካክላለን፣ አላስፈላጊ እርምጃ አትውሰዱ ብለናቸዋል። ትላንት ግን ከቤተክህነት የሚወጣው በሙሉ ይፈተሻል ዛሬም፣ የሚወጣ መኪና በሙሉ ይፋተሻል፤ የሚገባው ግን አይፈተሽም። የሚገባውን የኛ ዘበኞች ይፈትሹ ይሆናል፤ የመንግሥት ወታደሮች ግን አይፈትሹም። አንዱ ሌላ ነገር ይዞ ገብቶ ሲወጣ ፈታሹ ሌላ ነገር ይዞ ተብሎ የቤተክርስቲያን ስም እና ክብር ቢዋረድ ማነው ኃላፊው?

- ምንድነው የተፈለገው? ከቤተክርስቲያን ምንድነው የሚወጣው? መድፍ ነው? መሳሪያ ነው? አከፋፋይ ናት ቤተክርስቲያኒቱ? አትታመንም? መንግሥትን ያስጮኸ ነገር አለ እኛም የጮህንበት ከመንግስት በፊት፤ ግለሰቦችን ስለተናገሩት ንግግር የማይባል ተብሏል እያልን እኛ ነን የጮህን ይሄ የቤተክርስቲያን ቋንቋ አይደለም ብለን ነበር፤ መግለጫ ለመስጠት ተዘጋጅተን ነበር መንገዱን ስናየው መጠላለፊያ እንጂ ከፅድቅ ስላልሆነ ነው ዝም ያለነው። የፅድቅ ሲሆን ገፍተን ነው የምንወጣው።

- ከቤተክህነት ምንድነው የሚወጣው ? ከተፈለገ መባል ያለበት ጥርጣሬ አለን ቤተክህነት ውስጥ ይባላል፤ እንዲህ አይነት ነገር ቢወጣ ኃላፊነቱ የናተ ነው ጠብቁ ነው ልንባል የሚገባው ወይም ሰው እንሥጣችሁ የሚያንሳችሁ ከሆነ ቤተክርስቲያኒቱን እንዳያስወቅስ ነው መባል ያለበት እንጂ ቤተክርስቲያን የማትታመን ሆነ ከትላንት ጀምሮ እስካሁን እኛ መሪዎቹ በማናውቀው ፈታሽ በር ላይ ቆሞ መፈተሽ ድፍረት ነው። ቤተክርስቲያኒቱን ህልውናዋን መፈታተን ነው። አቅሟንም መፈትን ነው ተገቢ አይደለም።

- መደፋፈሩ በዝቷል፤ መንግስትም ቤተክርስቲያኒቱን ይደፍራል አልፎ ይሄዳል።

- እንደ ግለሰብ በስሜት የሚናገሩ ሰዎች ይኖራሉ። ቤተክርስቲያኒቱን መድፈር አዳጋ ነው። ለሃይማኖቱ የማይሞት የለም፣ ከዚህ በፊት ብዙዎች ሞተዋል፤ ተከባብረን እንኑር ለሰላም እንኑር።

- ካህን ነው ሲሉት ሌላ ነጭ ለባሽ ይሆናል፣ ነጭ ለባሽ ነው ሲሉት ካህን ሆኖ ይገኛል፤ የቤተክርስቲያን መሪ ነው ሲሉት የፖለቲካ መሪ ሆኖ ይገኛል፤ የፖለቲካ መሪ ሲሉት ቀዳሽ ሆኖ ይገኛል ምን አመጣው ይሄን ቀጥ ብለን እንቁም። ደሃ ሲበደል ተበደለ እንበል ሲታሰር ፍቱ እንበል፤ እያልን ነው እኮ፤ መንግሥትን ፍቱ እያልን እንመካከራለን ይፈታል ለዚህ ደግሞ እናመሰግናለን።

- በሃይማኖት ጉዳይ አንደራደርም።

- ካህን ካህን ይሁን፣ ወታደርም ወታደር ይሁን ሌላውም እራሱን ይሁን በሚያስተሳስረን ነገር ተሳስረን ጥላቻና ሁከትን፣ ሽብርና አላስፈላጊ ነገርን እናርቅ።

- ካላስፈላጊ #ጎጠኝነት#ዘረኝነት እንራቅ።

- ሀገራችን ሰላም ትሁን የሃይማኖት ሰዎች እንደ ሃይማኖት እናስብ፣ እንደ ሃይማኖት እንናገር፣ አላስፈላጊ ጀግንነትን እንርሳው። አላስፈላጊ ሙገሳንም እንርሳው። ካላስፈላጊ ሙገሳ አስፈላጊ በሆነ ወቀሳና ለመጨረሻው መከራ እራሳችንን እናዘጋጅ።

ያንብቡ፦ https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-12-2

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia