TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አቶ መለስ ዓለሙ የደቡብ ክልል ፕሬዘዳንት ሆነው ሊሾሙ ይችላሉ!

ከአሁን ቀደም የማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስትር በመሆን ያገለገሉት አቶ መለስ ዓለሙ፣ ለክልሉ ምክር ቤት በፕሬዚዳንትነት ሊሾሙ እንደሚችሉ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ አቶ መለስ በአሁኑ ወቅት በሚኒስትር ማዕረግ የኢሕአዴግ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ማዕከል ምክትል ዋና አስተባባሪ በመሆን በመሥራት ላይ ይገኛሉ፡፡

#ሪፖርተር_ጋዜጣ

ተጨማሪ የንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-08-28-2
በጋምቤላ ፈቃድ የሌላቸው 11 የውጭ ኮሌጆች ተገኙ!

ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 11 ሕገወጥ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጋምቤላ ክልል ሲያስተምሩ እንደተደረሰባቸው፣ የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡

ኤጀንሲው ከተለያዩ ግለሰቦች በደረሰው ጥቆማ መሠረት ወደ ክልሉ ተንቀሳቅሶ የለያቸው እነዚህ 11 ተቋማት በድኅረ ምረቃና በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ተማሪዎችን እየተቀበሉ እንደሚያስተምሩ ለሪፖርተር የገለጹት፣ የኤጀንሲው የኮሙዩኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ታረቀኝ ገረሱ ናቸው፡፡

ከኤጀንሲው ፈቃድ ሳያገኙ ሊያስተምሩ የተገኙት 11 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በአገር ውስጥ የማይታወቁና እንግዳ መጠሪያ ያላቸውና ከውጭ የገቡ እንደሆኑ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

‹‹በተደጋጋሚ በደረሰን ጥቆማ መሠረት ለማጣራት ወደ ክልሉ ስናመራ የጠበቅነው አንድ ተቋም ብቻ ነበር፡፡ ስንደርስ ግን 11 ሆነው አገኘናቸው፡፡ በወቅቱ ምንም ማድረግ ስላልቻልን ለክልሉ መንግሥት ስለሁኔታው በማስረዳት የክልሉን ነዋሪዎች ከሕገወጦች እንዲጠብቅ ደብዳቤ ጻፍን፤›› የሚሉት አቶ ታረቀኝ፣ ለክልሉ ደብዳቤ ከተጻፈ ስድስት ወራት የተቆጠረ ቢሆንም ምንም ዓይነት ምላሽ ለኤጀንሲው አለመድረሱን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

#ሪፖርተር_ጋዜጣ

ተጨማሪ የንብቡ👇
https://telegra.ph/eth-08-28-3
#አቶ_ርስቱ_ይርዳው

ቀጣዩ የደቡብ ክልል ፕሬዘዳንት ማን ይሆኑ?

TIKVAH-ETHIOPIA ከቤተሰቡ አባላት ታማኝ ምንጮች እንደሰማው ከሆነ-አቶ ሚሊዮን ማቲዮስን በመተካት የደቡብ ክልልን በፕሬዘዳንትነት የሚመሩት አቶ #ርስቱ_ይርዳው ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል።

•በትላንትናው ዕለት #ሪፖርተር_ጋዜጣ የደቡብ ክልል ቀጣይ ፕሬዘዳንት አቶ መለስ አለሙ ሆነው ሊሾሙ እንደሚችሉ መግለጹ አይዘነጋም።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮጵያ የቆዩ ፈንጂዎችን ሙሉ ለሙሉ ለማፅዳት ዓለም አቀፍ ትብብር ጠይቃለች !

ኢትዮጵያ ከውጭ ከመጡ ጠላቶችና በአገር ውስጥ በተደረጉ ጦርነቶች መሬት ውስጥ ተቀብረው የቆዩ ፈንጂዎችን፣ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ሙሉ ለሙሉ ለማፅዳት ዓለም አቀፍ ትብብር እየጠየቀች መሆኑ ተገለጸ፡፡

በሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የፈንጂ ማምከን ቢሮ ኃላፊ ኮለኔል አበራ አዘናው ፥ ኢትዮጵያ በካናዳ እ.ኤ.አ. በ2004 የፈረመችውን የፀረ ሰው ፈንጂ ማውደም ስምምነትን በተያዘለት እ.ኤ.አ. በ2020 አስወግዳ ባለማጠናቀቋ፣ ሁለተኛ የማራዘሚያ ጊዜ በኖርዌ ኦስሎ እ.ኤ.አ. 2020 እንደገና ለአምስት ዓመት ጠይቃ እስከ 2025 እንደተራዘመላት ለሪፖርተር ጋዜጣ ተናግረዋል፡፡

በ5 ዓመታት ውስጥ አፅድታ እንድትጨርስ በስምምነቱ መሠረት ፈቃድ የተሰጣት ቢሆንም፣ ኢትዮጵያ ያሏት የፈንጂ ማምከኛ መሣሪያዎች ኋላ ቀር በመሆናቸውና በፋይናንስ ችግር ሳቢያ የዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡን ትብብር መጠየቋ ተገልጿል፡፡

የድጋፍ ሁኔታዎችን አስመልክቶ የፈንጂ ማምከን ቢሮ የኢፌዴሪ ሰላም ሚኒስቴር፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴርንና ሌሎች አካላትን ጨምሮ ከኤምባሲዎችና ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፍና ትብብር ለማግኘት ግንቦት 12 ቀን 2013 ዓ.ም. ዝግ ውይይት ተካሂዷል፡፡

የፈንጂ ማምከን ቢሮ ኃላፊው፥ አገሪቱ ምንም እንኳ በትግራይ፣ በአፋር ፣ በቤኒሻንጉል ጉምዝ፣ በኦሮሚያ፣ በሶማሌና በጋምቤላ ክልሎች መሬት ውስጥ የተቀበሩ ወይም ተከማችተው የሚገኙ ፀረ ሰው ፈንጂዎች እንዳሉ ቢታመንም የፈንጂዎቹ ትክክለኛ መገኛ ቦታ አይታወቅም ሲሉ ለ #ሪፖርተር_ጋዜጣ ተናግረዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/Reporter-Newspaper-05-23

@tikvahethiopia
#ከመልሚ

በከተሞች ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ለሚጠቀሙበት መንገድ የአገልግሎት ክፍያ የሚከፍሉበት ስርዓት እየተዘረጋ ነው።

ይህ ስርዓት ከተሞች ገቢያቸውን ለማሳደግ ሊሠሯቸው ይገባል ተብለው በዕቅድ ከተያዙ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው ተብሏል።

ሥርዓቱን ተግባራዊ ለማድረግ የመጨረሻው የጥናት ደረጃ ላይ እንደሚገኝ በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የከተሞች ገቢ ሪፎርም ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት አስተባባሪ ወ/ሪት አፀደ ኃይሉ ተናግረዋል።

የከተማ መንገድ የአገልግሎት ክፍያ ሥርዓትን ለመዘርጋት የሚደረገው ጥናት የአዳማ፣ የድሬዳዋ እና የባህር ዳር ከተሞችን ናሙና በመውሰድ እየተከናወነ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

በጥናቱ በአጠቃላይ በከተሞች ውስጥ ያለው የተሽከርካሪዎች ምልልስና በመንገዶች ላይ የሚያሳድሩት ጫና የሚዳሰስ ሲሆን መንገዶቹ ጥገና ሆነ መልሶ መገንባት ሲያስፈልጋቸው ከተጠቃሚዎች በሚያገኙት ገቢ የሚሠሩበትን ሥርዓት ለመዘርጋት ያለመ ነው ብለዋል።

በ3ቱ ከተሞች በሚወሰደው ናሙና መሠረት አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም ከተሞች፣ የከተማ መንገድ ተጠቃሚዎች ክፍያ ይጠይቃሉ ብለዋል።

ወ/ሪት አፀደ ኃይሉ ፤ ሁሉም ተሽከርካሪዎች ተመሳሳይ ክፍያ ባይከፍሉም በጥናቱ ግኝት መሠረት በመንገዶች ላይ እንደሚኖራቸው ተፅዕኖ ክፍያ ይጠየቃሉ ያሉ ሲሆን " ክፍያው ሁሉንም ባለ ሞተር ተሽከርካሪዎች ብቻ ያካትታል። ሞተር የሌላቸው ተሽከርካሪዎች በዚህ ሥርዓት ውስጥ አልተካተቱም " ብለዋል።

ጥናቱ ሲጠናቀቅ የትኞቹ ተሽከርካሪዎች ምን ያህል መክፈል አለባቸው የሚለው ሆነ መቼና የት ይከፍላሉ የሚለው እንደሚለይና ሥርዓቱም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ መግለፃቸውን #ሪፖርተር_ጋዜጣ አስነብቧል።

@tikvahethiopia
የመንገደኞች እንግልት እና የመንግስት አካላት ምላሽ !

ከአማራ ክልል በተለይም #ከሰሜን እና #ደቡብ_ወሎ አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ ለመግባት ብዙዎች እየተንገላቱ ነው።

ይህ ጉዳይ አንድ ወቅት ጠንከር አንዴ ላላ ፤ ያዝ ለቀቅ እያደረገ አሁንም ድረስ ቀጥሏል።

አንዳንዶች በብዙ ልመና ነው የሚያልፉት።

ወደ መጣችሁበት ተመለሱ የሚባሉ ወገኖች ምክንያት ቢጠይቁም በግልፅ አስረድቶ የሚነግራቸው አላገኙም።

ለመሆኑ ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦቻችን ምን አሉ ?

👉 " ... መላ ሊባልለት የሚገባ ነገር ነው። ከደሴ ተነስተን ወደ አ/አ እየሔድን ነበር ግን " ሸኖ " ላይ የአማራ ክልል መታወቂያ ይዛችሒ አትገቡም ተብለን ስንጉላላ ቆይተን ሹፌሩ ይዘሐቸው ተመለስ ተብሏል። ሌሎቹ ተመልሰዋል። እኔ ግን ግድ መሔድ ስላለብኝ ለፈተና ባጃጅም በግሬም ኡ/ ገብቻለሁ ፡፡ እባካችሁ ዛሬ ብቻ አደለም ያዝ ለቀቅ እያደረጉ ነው እንጅ ከብዶናል "

👉 " እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ አሁንም ድረስ ከወሎ መዳረሻቸውን አ.አ አርገው የሚመጡ ተሳፋሪዎች ከበኬ ኬላ አየተመለሱ አሌልቱ ላይ ብዙ እንግልት እየገጠማቸው ይገኛል "

👉 " ወደ አዲስ አበባ አትገቡም ተብለው ብዙዎች ሲንገላቱ ቆይተው ወደ ኃላ እንዲመለሱ ተደርገዋል። እኛ በብዙ ልመና ለህክምና ነው ብለን አልፈናል። "

#ሪፖርተር_ጋዜጣ ያነጋገራቸው ፦

👉 " ሐምሌ 17 ቀን 2014 ዓ.ም. መነሻችንን ከወልዲያ ከተማ አድርገን ወደ አዲስ አበባ ስንጓዝ የአማራ ክልልን አልፈን ኦሮሚያ ክልል ስንገባ ተደጋጋሚ ፍተሻ ተደርጎልናል። ለገዳዲ ከደረስን በኃላ ግን የአዲስ አበባ መታወቂያ የላችሁም በሚል ምክንያት ወደ ደብረ ብርሃን መልሰውናል። ሁኔታው በጣም አሳዛኝ ነው ።

ከሸኖ ከተማ ጀምሮ እስከ ሰንዳፋ ድረስ የተደረገብን ፍተሻ በጣም አድካሚ ከመሆኑም በላይ፣ የአዲስ አበባ መታወቂያ የላችሁም በሚል ሲሳለቁብን ማየት እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ አሳፋሪ ተግባር ነው።

ፖሊሶች ፍተሻ ካደረጉ በኋላ የአዲስ አበባ መታወቂያ የሌላቸውን እዚያው ክልላቸው ወስደህ አውርዳቸው በማለት ለሾፌሩ ተናግሯል።

በዚህም የተነሳ በግዴታ ለገዳዲ ከደረስን በኋላ እንደገና ተመልሰን ደብረ ብርሃን ከተማ አድረናል። በስተመጨረሻም በነጋታው የቤት መኪና ተከራይተን ለቅሶ እንደምንሄድ በመናገር አዲስ አበባ ገብተናል።

የተፈጠረውን ክስተት አስከፊ ነው። በጊዜው ገንዘብ ስለነበረን ከፍለን ተመለስን ነገር ግን ገንዘብ የሌላቸው ሰዎች ከመኪና እንዲወርዱ ሲደረጉ ሕፃን ልጅ የያዙ እናቶች ጭምር ለመመለሻ የሚሆን ገንዘብ አጥተው ሜዳ ላይ ወድቀው ነበር።

ይህን ያህል አማራ ምን አድርጎ ነው ? ወስደህ አውርዳቸው እንዴት ይባላል ? ኢትዮጵያዊ አይደለንም ወይ ? ብዙ ግፍ ያለበት ክልል እኮ ነበር፣ በአማራ ላይ ይህ ሁሉ ሲደረግ ሕግ አለ ወይ ያስብላል ? "

👉 " አደራው ኃይሌ እባላለሁ ከደሴ ከተማ ሐምሌ 19 ቀን 2014 ዓ.ም. ወደ አዲስ አበባ እየተጓዝኩ ነበር 100 ኪሎ ሜትር በማይሞላ ርቀት ውስጥ ከጫጫ ከተማ እስከ ለገዳዲ ከተማ ቢያንስ 7 ጊዜ ተፈትሸናል።

የመጨረሻው የአዲስ አበባ መግቢያ ፍተሻ በነበረው ለገዳዲ ስንደርስ ከጥቂት የአዲስ አበባ ከተማ መታወቂያ ከያዙ ሰዎች ውጪ ቀሪዎቹ ወደ መጡበት እንዲመለሱ ተደርጓል።

ድርጊቱ በጣም የሚያሳዝን ነው።

ከመኪና እንድንወርድ ከተደረገ በኋላ ስልካችንን ከፍተን በውስጥ ያሉ ምሥሎችና ድምፆችን ከፍተን እንድናሳይ ተደርጓል።

👉 " ሁኔታው የሕግ ድጋፍ ያለው እንደማይመስልና አልፎ አልፎ ፖሊሶቹ በመሰላቸው አሠራር እንጂ እንዲህ ዓይነት ድርጊት የሚፈቅድ ምንም ዓይነት የሕግ መሠረት ማቅረብ አይቻልም።

ድርጊቱ አሳፈሪ በመሆኑ በሥልጣን ላይ ያለው መንግሥት ለጉዳዩ አፋጣኝ መልስ መስጠት ካልቻለ፣ እንደ አገር አብሮ በኖረ ሕዝብ ላይ አሁን ያለው የፖለቲካ ግለት ተጨምሮበት የባሰ ቁርሾ፣ እርስ በርስ የመለያየትና ከፋፋይ የሆነ አጀንዳ ይሆናል "

የመንግስት አካላት ምን አሉ (ለሪፖርተር ጋዜጣ) ?

▪️የአማራ ክልል የኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ፦

" ጉዳዩ ስለመከሰቱ መረጃ አለኝ። ነገር ግን የሕወሓት ሠርጎ ገቦችን ለመያዝ በሚል ግልጽ ባልሆነ መንገድ ዜጎች እየተንገላቱ በመሆኑ ጉዳዩን ለኦሮሚያ ክልል መፍትሔ እንዲሰጥበት አሳውቀናል። "

▪️የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ አራርሳ መርዳሳ ፦

ጥያቄ ከሰሙ በኋላ መልስ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡

▪️የሰሜን ሸዋ ዞን የፀጥታና አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ብርሃኑ ፦

" ጉዳዩ መከሰቱን መረጃ አለኝ።

ተሳፋሪዎች ደብረ ብርሃን ከተማ ካለፉ በኋላ እንዲህ ዓይነት ችግር ተፈጥሯል።

ከኦሮሚያ ክልልና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ደውላችሁ አጣሩ "

▪️የአዲስ አበባ የፀጥታ ቢሮ የኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ ፦

" ስለሚባለው ጉዳይ ምንም ዓይነት መረጃ የለንም "

▪️የአ/አ ፖሊስ ኮሚሽን የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ፦

" የተጠቀሰው ጉዳይ አይመለከተንም "

▪️ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ሚኒስትር ደኤታ ወ/ሪት ሰላማዊት ካሳ ፦

" ጉዳዩ የሕወሓት የሽብር ቡድን በወረራ ይዟቸው ከነበሩት የአማራ ክልል አካባቢዎች የተለያዩ የመታወቂያ ማኅተሞችና የአስተዳደር ሰነዶችን በመዝረፉና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እነዚህን ሐሰተኛ መታወቂያዎች ሰነዶችን የያዙ ሠርጎ ገቦች ወደ አዲስ አበባ ሊገቡ ሲሉ በመያዛቸው ምክንያት የሚደረግ የክትትል ሥራ ነው።

የጥፋት ተልዕኮ የያዙና ከአማራ ክልል ተዘርፈው በተወሰዱ ሰነዶች ተመሳስለው የተሰሩ መታወቂያዎችን የያዙ ግለሰቦች አሁንም ወደ አዲስ አበባ ለመግባት የሚያደርጉት ጥረት እንዳለ ለፀጥታ ኃይሎች መረጃው በመድረሱ ይህንን ለመከላከል ጥብቅ ፍተሻዎችና ማጣራቶች እየተደረጉ ነው።

ይሁን እንጂ አዲስ አበባን የጥፋት ተልኳቸው መዳረሻ ለማድረግ እየሞከሩ ያሉትን አካላት ለመከላከል በሚወሰደው ዕርምጃ፣ በመንገደኞች ላይ ተፅዕኖ መፍጠሩንና ዜጎችም ለእንግልት እየተዳረጉ መሆኑን የተመለከቱ ቅሬታዎች ደርሰውናል።

ይህም በደኅንነት ፍተሻና ማጣራት አፈጻጸም ላይ መሻሻል ያለበትን ሁኔታ ለይቶ የፀጥታ ኃይሉ የማስተካከያ ዕርምጃ እንዲወስድ ይደረጋል ። "

▪️የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባልና የአብን ከፍተኛ አመራር አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ ፦

" ... ከአማራ ክልል የወሎ አካባቢዎች ተነስተው መዳረሻቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ዜጎች ኦሮሚያ ክልል ሸኖ ሲደርሱ መታወቂያቸው እየታየ ከተሳፈሩበት መኪና እንዲወርዱና ወደ መጡበት እንዲመለሱ መደረጉን ተጨባጭ መረጃዎች አሉ።

የሚመለከታቸው የፌዴራልና የኦሮሚያ ክልል የሥራ ኃላፊዎች በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለውን መጉላላትና አግላይ የነውር ተግባር ታስቆሙ ዘንድ ጥሪዬን አቀርባለሁ። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#የዩኒቨርሲቲ_መምህራን ! በዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበራት በኩል የቀረቡ ጥያቄዎች ፦ • መንግሥትን የደመወዝ ጭማሪ እና የዕርከን ዕድገት እንዲያደርግ ጠይቀዋል። • ለዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ እና ቴክኒካል ረዳቶች የተሰራውን አዲሱን የስራ ደረጃ ማሻሻያ JEG በተመለከተ ቅሬታ አላቸው። • የመምህራን የቤት አበልን በተመለከተ በፍጥነት አሁን ያለው የቤት ኪራይ ዋጋ ከግምት አስገብቶ ተሻሽሎ ተግባራዊ እንዲደረገ…
የዩኒቨርሲቲ መምህራን ጥያቄ !

የዩኒቨርሲቲ መምህራን ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ምላሽ የመስጠት ሒደቱ አሁን ምን ይመስላል ?  

የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ፕሬዚዳንት ዮሐንስ በንቲ (ዶ/ር) ፦

" በሲቪል ሰርቪስ ባለሙያዎች የሥራ መዘርዝር በድጋሚ ታይቶ ሌላ የደረጃ ምዘና ተዘጋጅቷል፡፡ በዚህም ረዳት ምሩቅ ሁለት፣ ረዳት ሌክቸረር፣ ሌክቸረር፣ ተባባሪ ፕሮፌሰርና ረዳት ፕሮፌሰር ደረጃዎች ተሻሸለዋል፡፡

የረዳት ምሩቅ አንድና የፕሮፌሰር ግን ከነበረበት ደረጃ አልተሻሻለም፡፡ ለፕሮፌሰር ደረጃ ቀድሞም በ2011 ዓ.ም. ላይ ማሻሻያ ሲደረግ ደመወዝ የተጨመረው 233 ብር ገደማ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ዕድሜ ልካቸውን በትምህርት ላይ ያሳለፉ፣ እዚህ ለመድረስ ብዙ ጥናት ያሳተሙና ያማከሩ ናቸው፡፡

ውሳኔዎች ሲተላለፉ የአገር አቅም ከግምት ውስጥ የሚገባ ቢሆንም፣ እነዚህ ሰዎች ከዚህ ሌላ የገቢ ምንጭ የላቸውም፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከዚህ ቀደም ማስተርስ ያላቸው ሆነው በታወቁ ጆርናሎች ላይ ጥናታቸውን ያሳተሙ መምህራን ረዳት ፕሮፌሰር መሆን ይችሉ ነበር፡፡

አሁን በወጣው ደረጃ ግን ረዳት ፕሮፌሰር ለመሆን ሦስተኛ ዲግሪ ስለሚያስፈልግ፣ ማስተርስ ኖሯቸው ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑ መምህራን በአዲሱ ደረጃ የተቀመጠውን የደመወዝ ጭማሪ አያገኙም፡፡

ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ስናነጋግር የሚያነሱ ጉዳዮች አሉ፡፡ አንደኛው ሰዎች በማስተርስ ደረጃ ረዳት ፕሮፌሰር የሚሆኑ ከሆነ ዶክትሬት ለመማር አይበረታቱም የሚል ነው፡፡

የትምህርት ዕድል ሲሰጣቸው ባለንበት ረዳት ፕሮፌሰር መሆን እንችላለን የሚሉ እንዳሉ ይነገራል፡፡

ይህንንና የረዳት ምሩቅ አንድና የፕሮፌሰር ደረጃ አለመሻሻሉን ጉዳይ ገና እየተወያየንበት ነው፡፡ "

ያንብቡ : telegra.ph/RE-08-14-3

#ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከ / ወደ ትግራይ  የየብስ ትራንስፖርት መቼ ይጀምራል ? ከትግራይ ክልል ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች #በቅርቡ የየብስ ትራንስፖርት እንደሚጀምር ከሰሞኑን ተገልጿል። ከአየር ትራንስፖርት በተጨማሪ የየብስ ትራንስፖርት በቅርብ ቀን ለማስጀመር ከፌዴራል መንግስት ጋር በመነጋገር ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን የክልል የኮንድትራክሽንና መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ አሳውቋል። ከሰላም ስምምነቱ በኃላ በህጋዊ…
#Update

ከ/ወደ ትግራይ የየብስ ትራንስፖርት ለመጀመር የአገር አቋራጭ የሕዝብ ትራንስፖርት ማመላለሻ ማህበራት ዝግጁ እንዲሆኑ መመሪያ መተላለፉ ተሰምቷል።

ሪፖርተር ጋዜጣ ከአገር አቋራጭ የሕዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት ማኅበራት ያገኘሁት ባለው መረጀ ፤ የትራንስፖርት ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ወደ ትግራይ የተለያዩ ከተሞች የሕዝብ ማመላለሻ የትራንስፖርት አገልግሎትን ዳግም ለመጀመር ዝግጁ ሆነው እንዲጠብቁ መመርያ ተላልፎላቸዋል፡፡

በዚሁ የሚኒስቴሩ መመርያ መሠረት ማኅበራቱ ለአባሎቻቸው አገልግሎቱን መልሶ ለማስቀጠል ዝግጁ እንዲሆኑ ያሳወቁ ሲሆን አሁን እየጠበቁ ያሉትም የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱን የመጨረሻ ውሳኔ እንደሆነ ለማወቅ መቻሉን #ሪፖርተር_ጋዜጣ ዘግቧል።

ከጥቂት ቀናት በፊት የትግራይ ክልል የኮንስትራክሽንና መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ  ከትግራይ ክልል ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች #በቅርቡ የየብስ ትራንስፖርት እንደሚጀምር ማሳወቁ አይዘነጋም።

ቢሮው ከአየር ትራንስፖርት በተጨማሪ የየብስ ትራንስፖርት በቅርብ ቀን ለማስጀመር ከፌዴራል መንግስት ጋር በመነጋገር ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ መሆኑን መግለፁ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#ሶማሌላንድ

በሶማሌላንድ ግዛት በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎችና በተቃዋሚ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ ግጭት በርከታ ሰዎች ሰላም ፍለጋ ወደ #ኢትዮጵያ እየገቡ ናቸው።

እስካሁን ግጭት የሸሹ ከ83 ሺ በላይ የሶማሌላንድ ነዋሪዎች ወደ ኢትዮጵያ ድንበር በመዝለቅ በሶማሌ ክልል መስፈራቸው ተነግሯል።

የተመድ የስደተኞች ኮሚሽንን ዋቢ በማድረግ #ሪፖርተር ጋዜጣ እንዳስነበበው "ላስካኑድ" በምትባለው ከተማ በተከሰተው ግጭት፣ የበርካታ የሶማሌላንድ ነዋሪዎችን ሕይወት የተቀጠፈ ሲሆን በርካታ ሴቶችና ሕፃናት ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል፤ ዶሎ ዞን እየገቡ ናቸው።

እንደ ኮሚሽኑ መረጃ ፦

- እስከ  ቅዳሜ የካቲት 11 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ 14 ሺሕ የሚሆኑ አዳዲስ አባወራዎች (ወይም 83 ሺሕ ግለሰብ ስደተኞች) ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል።

- ስደተኞቹ በዶሎ ዞን፤ ቦህ፣ ገልሃሙርና ዳኖድ በተባሉ 3 ወረዳዎች ተጠልለው ይገኛሉ።

- አብዛኞቹ ስደተኞች ባለፈው ሳምንት ነው ወደ ኢትዮጵያ የገቡት።

- ስደተኞች በ3 ወረዳዎች በ13 ቦታዎች ሠፍረው የሚገኙ ሲሆን የተወሰኑት በትምህርት ቤትና መሰል የሕዝብ መገልገያ ሥፍራዎች ላይ ተጠልለዋል፤ ሌሎች ደግሞ ያለ መጠለያ ሜዳ ላይ ይገኛሉ።

- ከሶማሌ ክልል የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ቢሮ ጋር በመሆን ከ1,500 በላይ ለሆኑ በከፍተኛ ሁኔታ ለተጎዱ አባዎራዎች የተለያዩ ቁሳቁሶችና መሰል ድጋፎችን እየተሰጠ ነው።  ለተጨማሪ 9 ሺህ አባዎራዎች በቀጣይ ቀናት ድጋፍ ይደረጋል።

የሶማሌ ክልል፤ የስደተኞችን ወደ ኢትዮጵያ መግባት ያረጋገጠ ሲሆን ከተመድ የስደተኞች ኮሚሽን፣ ከዓለም አቀፍ ፍልሰት ድርጅት፣ እንዲሁም ከኢትዮጵያ የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ጋር በመሆን የዳሰሳ ጥናት አካሂዷል።

ያንብቡ : telegra.ph/ER-02-22

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት 'ህወሓት' እና ሸኔ' ን በሽብርተኝነት ፈረጀ። 5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 13ኛው መደበኛ ስብሰባ በመካሄድ ላይ ነው፡፡ ም/ቤቱ ዛሬ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ በሚያካሄደው 13ኛ መደበኛ ስብሰባ "ህዝባዊ…
#TPLF

የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት በአሸባሪነት የሰየመውን ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) የሽብርተኝነት ስያሜ #ይነሳ #አይነሳ በሚለው ጉዳይ ላይ ዛሬ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

በምክር ቤቱ ውስጥ የብልፅና አባላት ሕወሓትን ከአሸባሪነት ለመሰረዝ ያለመ ዝግ ስብሰባ ትናንት መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓ.ም. የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔን ጨምሮ፣ የፍትህ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዮስ (ዶ/ር)፣ እንዲሁም የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በተገኙበት ሲያካሂድ እንደዋለና በውይይቱም በርካታ መግባባት ያላስቻሉ ጠንካራ ሐሳቦች መሰንዘራቸውን ጋዜጣው ከምንጮቼ  ሰምቻለሁ ብሏል።

ይሁን እንጂ በፓርላማው የመንግሥት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲን የ2014 በጀት ዓመት የፋይናንስ ሕጋዊነት ኦዲት ላይ ለመምከር ለመጋቢት 13 ቀን 2015 ዓ.ም. ለጠዋት ጠርቶት የነበረውን ስብሰባ ወደ ከሰዓት በማጠፍ፣ በዚሁ ቀን ጠዋት አስቸኳይ ስብሰባ ለፓርላማ አባለቱ መላኩ ተገልጿል፡፡

ፓርላማው ሕወሓትንና ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ድርጅት ወይም በመንግሥት ‹" ሸኔ "  ተብሎ የሚጠራውን ታጣቂ ቡድን በአሸባሪነት የፈረጀው በሚያዚያ በ2013 ዓ.ም. ነበር፡፡

#ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia
#የዋጋ_ንረት📈

መስከረም 2015 መጀመርያ ላይ ከ6 ሺሕ ብር በታች ይሸጥ የነበረ አንድ ኩንታል ነጭ ጤፍ ለመጀመርያ ጊዜ ከ10 ሺሕ ብር በላይ ዋጋ ያወጣው ሊጠናቀቅ ሰዓታት በቀሩትና አሮጌ ብለን ልንሸኘው በተዘጋጀው 2015 ዓ.ም. ነው፡፡ የጤፍ ዋጋ ነሐሴ 2015 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ እስከ 15 ሺሕ ብር ሲደርስ ይኸው የዋጋ ጭማሪ 1 ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከዕጥፍ በላይ እንደደረሰ ያመለክታል።

#የስንዴ_ገበያም በተመሳሳይ ከፍተኛ የሆነ ዋጋ የተመዘገበበት ዓመት ይኼው 2015 ዓ.ም. ነው፡፡

በአጠቃላይ ከጤፍና ስንዴ በተጨማሪ በሌሊችም ምግብ ነክ እና ምግብ ነክ ባለሆኑ ሸቀጦች ላይ በዚህ ልንሸኘው ጥቂት ሰዓታት በቀረን 2015 ከፍተኛ የሆነ ዋጋ ተመዝግቧል።

የኢኮኖሚው ባለሙያ አቶ አወት ተክኤ ምን ይላሉ ?

" በሀገሪቱ ከፀጥታና አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ የተፈጠሩ ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች የዋጋ ንረትን በማባባስ ዓይነተኛ ሚና ነበራቸው። አዳዲስ ኢንቨስትመንቶች እንዳይስፋፉ ጭምር አድርገዋል።

በ2015 ዓ/ም በጀት ዓመት ለዋጋ ንረቱ መባባስ በተደጋጋሚ ከሚጠቀሱ ምክንያቶች ባሻገር፣ መንግሥት የወሰዳቸው የፖሊሲ ዕርምጃዎች ለዋጋ ንረቱ አስተዋጽኦ ነበራቸው።

ለአብነት የኢኮኖሚ የነዳጅ ጭማሪ እና ሌሎች የመንግሥት የፖሊሲ ውሳኔዎች ለዋጋ ንረቱ የራሳቸው አስተዋጽኦ አድርገዋል።

ይህ የዋጋ ንረት በቀጣይ ዓመትም እንዳይተላለፍ ለችግሩ መንስዔ የነበሩት፣ ለምሳሌ የፀጥታና ያለ መረጋጋቶች መፍትሔ ሊሰጣቸው ይገባል፡፡

በቅርቡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ውሳኔዎችን በአግባቡ መተግበር ለዋጋ ንረት መርገብ መፍትሔ ሊሆኑ ይገባል፡፡ "

ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Ethiopianreporter-09-11

#ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia
አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች መታሰራቸው ተሰምቷል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ቁጥራቸው ለጊዜው ያልታወቁ ሰዎች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው መታሰራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ሰሞኑን መሆኑንና አቶ ታምሩ ገምበታ ግን ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. መሆኑ ተገልጿል።

የምክትል ዳይሬክተሩ ቤት በፍርድ ቤት የብርበራ ፈቃድ መበርበሩንና ዛሬ ጥቅምት 7 ቀን 2015 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ሊቀርቡ እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡

የመንግሥት አስተዳደር ለውጥ ከተደረገ ጀምሮ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ተቋም ውስጥ የተለያዩ ለውጦች (ሪፎርም) የተደረገ ቢሆንም፣ አንዳንድ የተቋሙ ሠራተኞች በድለላ ሥራ የተሰማሩ አካላት ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ እንዳሉም ተመላክቷል።

አገልግሎቱን በዋና ዳይሬክተርነት ይመሩ የነበሩት አቶ ብሩህተስፋ ሙሉጌታ፣ ምክትል ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ፍራኦል ጣፋና አቶ ታምሩ ገምበታን ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከ3 ወራት በፊት ሐምሌ መጀመሪያ ሳምንት አካባቢ ከኃላፊነት ማንሳታቸው ይታወሳል፡፡

ተቋሙ ከፓስፖርትና መሰል አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ ቅሬታ ሲቀርብበት መቆየቱ ይታወቃል።

በተጨማሪ ከዜጎች ከፍተኛ ገንዘብ በመቀበል በሕወጥ መንገድ ወደ ውጭ አገር ሲልኩ ነበር የተባሉ 16 የተቋሙ ሠራተኞች፣ እንዲሁም 5 በአሠሪና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ስም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሰዎችም ከዚህ ቀደም በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

በተያዘው ሳምንት በቁጥጥር ሥር መዋላቸው የተሰማው ምክትል ዳይሬክተሩን ጨምሮ ሌሎች ሰዎችም ከሙስና ጋር በተያያዘ መጠርጠራቸው ተገልጿል፡፡

ምንጭ፦ #ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ተመዝጋቢዎች ወስኖ የነበረው ፍርድ፣ በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ መሻሩን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ባደረገው የሦስተኛ ዓመት የአንደኛ መደበኛ ጉባዔ ላይ በወሰነው መሠረት፣ ፍርድ ቤቶች ያስተላለፉትን ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ ተመዝጋቢዎች ቤቶች እንዲሰጡ የሚለው ውሳኔ የተወሰኑ የሕገ መንግሥቱ ድንጋጌዎችን የሚጥሱና ተቀባይነት የላቸውም በማለት በሙሉ ድምፅ ሽሮታል።

በምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ አቶ አገኘሁ ተሻገር ተፈርሞ ኅዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም. ለከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የተጻፈው ደብዳቤ፣ በ2005 ዓ.ም ወጥቶ የነበረውን የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን የዕጣ ድልድል ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ ቅድሚያ የሚሰጠው መመርያ የሕገ መንግሥት ትርጉም እንደሚያስፈልገው በምክር ቤቱ ታምኖ እንዲታይ ይገልጻል፡፡

" ሕገ መንግሥታዊ የአካታችነትና የፍትሐዊነት መርህን የጣሰ " ሲል የመመርያውን አንድ አንቀጽ የገለጸው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ደብዳቤ፣ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቁጠባ ቤቶች ዋነኛ ዓላማ 40 በመቶ የቆጠቡ ተመዝጋቢዎች ከባንክ በተመቻቸ 60 በመቶ ክፍያ በመደገፍ እንዲያገኙ ማስቻል እንደሆነ ነው የሚያስረዳው፡፡

ሆኖም አንደኛው የመመርያ አንቀጽ ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ ቅድሚያ እንዲሰጣቸው የሚያደርግ ሲሆን፣ ይህም ድንጋጌ መግባቱ ‹
" የመመርያውን ግልጽ ዓላማና መንፈስ ያልተከተለ " ሲል ደብዳቤው ያስረዳል፡፡

" ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ ቅድሚያ መስጠት በመርሐ ግብሩ ለተመዝጋቢዎች እኩል ዕድል ለማሰጠት የታለመውን መሠረታዊ ዓላማ የጣሰ ነው፤ " ሲል ደብዳቤው ያብራራል፡፡

የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች መርሐ ግብርን የሚያስፈጽመው መመርያ በሰጣቸው መብት መሠረት ሙሉ ለሙሉ የሚጠበቅባቸውን ቁጠባ ከቆጠቡ በኋላ፣ ቅድሚያ እንደሚሰጣቸው የጠበቁ 761 ቆጣቢዎች በዕጣ ማውጣት መርሐ ግብሩ ላይ ቅድሚያ ሳይሰጣቸው 40 በመቶ ከቆጠቡት ጋር እኩል ነበር የተሳተፉት፡፡

ለዚህም ነበር 761 ተመዝጋቢዎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝን በመክሰስና እስከ ሰበር ድረስ በመድረስ ሊፈረድላቸው የቻለው፡፡

በፍርድ ቤቶች ተወስኖ የነበረው እየተገነቡ ያሉና ዕጣ ያልወጣላቸውን ቤቶች፣ ከዚህ በኋላ ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ ተመዝጋቢዎች እንዲተላለፉ ነበር፡፡

በውሳኔው ቅር ተሰኝቶ የነበረው የከተማ አስተዳደሩ የቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝ ከአንድ ዓመት በፊት ለሕገ መንግሥታዊው ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ አቤቱታ አቅርቦ፣ ጉባዔው ጉዳዩን በመመርመር በዚህ ዓመት መስከረም ወር ምክር ቤቱ ሲከፈት ውሳውን አሳልፏል፡፡

የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን መርሐ ግብር ለማስፈጸም ወጥቶ በነበረው መመርያ ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ ተመዝጋቢዎች ቅድሚያ የሚያሰጠውን አንቀጽ፣ ከመስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ " ኢሕገ መንግሥታዊ " በመባሉ እንደማይሠራ ምክር ቤቱ ወስኗል፡፡

የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴርም አውጥቶት የነበረው የዚህ መመርያ ድንጋጌ፣ ደብዳቤው ከደረሰው ከኅዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ በአንድ ወር ውስጥ እንዲያሻሽልና ውጤቱን ለምክር ቤቱ እንዲያሳውቅ ያሳስባል፡፡ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ደብዳቤውን በግልባጭ ለሁሉም የክልልና የከተማ አስተዳደሮች አሳውቋል።

#ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia
#ጥናት

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ጥራታቸው ተጠብቆ ባለመገንባታቸው፣ በዕጣ የቤት ባለቤት የሆኑ ዕድለኞች ለከፍተኛ ወጪ እየተዳረጉ መሆናቸውን የአፍሪካ ከተሞች የምርምር ጥምረት (ACRC) እና ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ (FSS) በጋራ ባደረጉት ጥናት ማረጋገጥ መቻላቸውን አስታውቀዋል።

ሁለቱ ተቋማት ጥናቱን ለአንድ ዓመት ያህል ነው ያደረጉት።

በጥናቱ ከ6 በላይ ከፍተኛ ተመራማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን በኢኮኖሚ፣ በመዋቅራዊ ሽግግርና በወጣቶች አቅም ግንባታና በመኖሪያ ቤቶች ላይ የተደረገ ነው።

ጥናቱ ምን ይላል ?

- በአዲስ አበባ ከተማ ከመነሻውም የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሲገነቡ ደረጃቸውን የጠበቁ አይደሉም፡፡

- መንግሥት 40/60 ወይም የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በዕጣ ለደረሳቸው ሲያቀርብ ጥራታቸውን በጠበቀ መንገድ ስለማይገነቡ፣ ዕድለኞች መልሰው አፍርሶ ለመሥራት ይገደዳሉ ለከፍተኛ ወጪ ይዳረጋሉ።

- የጋራ መኖሪያ ቤት የደረሳቸው ዕድለኞች ፦
* ለኤሌክትሪክ ኃይል ዝርጋታ፣
* የሲራሚክ ንጣፍ፣
* ለመፀዳጃ ቤት መስመር፣
* ግድግዳ እንደገና ለመሥራትና ሌሎች የጎደሉ ነገሮች ለማሟላት ለከፍተኛ ወጪ ይዳረጋሉ።

- እነዚህ ጉዳዮች ከፍተኛ ትኩረት የሚፈልጉ በመሆናቸው፣ መንግሥት ለጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ከግብዓት ጀምሮ እስከ ባለሙያ ድረስ ጥራታቸውን በመጠበቅ ማቅረብ ይኖርበታል።

በተጨማሪ ...

በአዲስ አበባ ከተማ በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች ለሥራ ተስማሚ የሆኑ ነገሮች እንደሌላቸው ታይቷል። ወጣቶች በኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ፣ በኢመደበኛ ዘርፍና በጤና ላይ ያላቸውን በጎ ተግባራትና ያሉባቸው ችግሮች ተለይተው በጥናቱ ተካተዋል።

በኢትዮጵያ ከዚህ በፊት አብዛኛውን የቤት አቅርቦት ተፈጻሚ የሚሆነው በመንግሥት ሲሆን በአሁኑ ወቅት የተለያዩ ቤት አልሚ ድርጅቶች ተቋቁመው የማኅበረሰቡን የቤት ጥያቄ እየመለሱ መሆናቸው የሚበረታታ ነው።

በቤት አቅርቦት ላይ ለውጦች እየመጡ ቢሆንም አሁንም የመሬት አቅርቦት፣ እንዲሁም በዝቅተኛና በመካከለኛ ገቢ ላይ የሚገኙ ሰዎች ቤት ለመሥራት ቢፈልጉ የፋይናንስ አቅርቦት ችግር እየገጠማቸው ነው።

👉 በአጠቃላይ ጥናት የተደረገባቸው ጉዳዮች ላይ ያሉትን ችግሮች ለመፍታትና በጥናቱ የቀረቡ ግኝቶች መሬት ወርደው ተግባራዊ እንዲሆኑ፣ ለፖሊሲ አውጪዎች የሚቀርቡ ይቀርባሉ ተብሏል።

#ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AU #Fraud #CBE

ቀሲስ በላይ መኮንን ከአፍሪካ ኅብረት ኦፊሳላዊ የክፍያ ሰነድ ጋር ተመሳስለው የተዘጋጁ የተለያዩ ሐሰተኛ የክፍያ ሰነዶችን በመጠቀም ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍሪካ ኅብረት የባንክ ሒሳብ ወደ ሌላ የባንክ ሒሳብ #ከ6_ሚሊዮን_ዶላር_በላይ (367 ሚሊዮን ብር) ለማዘዋወር ሲሞክሩ ነው በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

ፍድር ቤት ቀርበውም ለፖሊስ ተጨማሪ ቀን ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዜዳንት አቶ አቤ ሳኖ ምን አሉ ?

" በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካለው የአፍሪካ ህብረት ሒሳብ የወጣ ገንዘብ የለም።

አንድ ሰው ሀሰተኛ ሰነዶችን ተጠቅሞ ለማውጣት ቢሞክርም እዛው በቦታው ላይ ተይዟል።

የማጭበርበር ሃሳብና ገንዘብ ለመውሰድ ጥረት ቢደረግም ማክሸፍ ችለናል። ይህንን የሞከሩት ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ናቸው። እኔ የማውቀው ይህን ብቻ ነው።

በመሰረቱ ጥሬ ገንዘብ በውጭ ምንዛሪ ሊሰጥ አይችልም። አጭበርባሪው መጥቶ  ሲጠይቅ ይህን እንኳን አያውቅም ነበር።

ሰውዬው እዚህ ሀገር የዶላር አካውንት ከሌለው ገንዘቡ ቢተላለፍም የትም ውስጥ ሊገባ አይችልም።

አጭበርባሪዎች በየቀኑ ነው ወደ ባንካችን የሚመጡት ፤ ባንክ ስለምንሰራ ይህ የተለመደ ነው። ነገር ን ሁሌም የማጭበርበር ድርጊቶቹ ከመሳካታቸው በፊት እንደርስባቸዋለን። ለፍርድም እናቀርባቸዋለን።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፥ የደንበኞቹን ሒሳቦች የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት ያንን እያደረግን ነው። የአፍሪካ ህብረት እስካሁን ድረስ በይፋ ቅሬታ አላቀረበብንም። "

ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የአፍሪካ ኅብረት ምንጭ ምን አሉ ?

"የእኛ ሒሳብ ላይ መሰል ማጭበርበር ሲያጋጥም ይህ ለሶስተኛ ጊዜ ነው።

አሁን ላይ ማጭበርበሩ #በተከበሩ_ሰዎች አማካኝነት እየተሞከረ ነው። ይህ ደግሞ በጣም አስጨንቆናል። አንድ ቀን ባለስልጣናት ተመሳሳይ ነገር ላለማድረጋቸው ምንም አይነት ዋስትና የለንም።

እምነት እያጣን ነው። ስለዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ ለደሞዝ አነስተኛ መጠን ያለው ፎሬክስ (የውጭ ምንዛሬ) ለመያዝ ወስነናል።

ይህን መሰሉ ሁኔታ የድርጅቱን ገንዘብ በውጭ ማቆየት እንድናስብ እያስገደደን ነው። "

https://telegra.ph/The-Reporter-04-21 #ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia