TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ችሎት #ክርስቲና_መላኩ #ጊዮናዊት_መላኩ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 2ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ፤ የህጻን ግዮናዊት መላኩ እና ህጻን ክርስቲና መላኩን በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው እንዲያልፍ አድርጋለች የተባለችው ተጠርጣሪ ላይ ፖሊስ ተጨማሪ ምርመራ እንዲያደርግ የ14 ቀን ጊዜ ሰጠ። ተጠርጣሪ ህይወት መኮንን ሀይሉ በነሃሴ 26 ቀን 2014 ዓ/ም ከጠኋቱ 3:30 ላይ በለሚ ኩራ…
#Update

2 ህጻናትን በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው እንዲያልፍ አድርጋለች ተብላ የተከሰሰችው የቤት ሰራተኛ የጥፋተኝነት ፍርድ ተላለፈባት።

የጥፋተኝነት ፍርዱ ተከሳሿ የመከላከያ ማስረጃ የለኝም ማለቷን ተከትሎ ነው የተሰጠባት።

የጥፋተኝነት ፍርዱን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የከባድ ግድያና የውንብድና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።

ተከሳሿ ወንጀሉን አልፈጸምኩም ማለቷን ተከትሎ በጥቅምት 30 ቀን በነበረ ቀጠሮ ዓቃቢህግ  የሟች ግዮናዊት እና ክርስቲና  መላኩ ወላጆችን ጨምሮ ስድስት ምስክሮችን አቅርቦ የምስክርነት ቃላቸውን አሰምቶ ነበር።

ፍ/ቤቱም የምስክር ቃል መርምሮ ተከሳሿ በተሰሰችበት ወንጀል እንድትከላከል በዛሬው ቀጠሮ ብይን ሰየሰጠ ቢሆንም ተከሳሿ የመከላከያ ማስረጃ እንደሌላት ገልጻለች።

ፍ/ቤቱም የተከሳሽን በፖሊስ ጣቢያ ቃል በመያዝና የዓቃቢህግ የሰው ምስክሮችን ቃል መርምሮ በተከሰሰችበት ተደራራቢ ወንጀል ጥፋተኛ ብሏታል።

ከቀጠሮ በፊት የዓቃቢህግ  የቅጣት ማክበጃ አስተያየት እና የተከሳሽ የቅጣት ማቅለያ አስተያየት ካላት በጽ/ቤት እንዲቀርቡ ያዘዘ ሲሆን የቅጣት አስተያየትን ተመልክቶ የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ለህዳር 26/2015 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰቷል።

ተከሳሽ ህይወት መኮንን ሀይሉ በነሃሴ 26 ቀን 2014 ዓ/ም ከጥዋቱ 3:30 ላይ አራብሳ ኮንዶሚኒዬም በቤት ሰራተኛነት ተቀጥራ በምትሰራበት መኖሪያ ቤት ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ህጻን ግዮናዊት መላኩ እና ህጻን ክርስቲና መላኩን በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወታቸው እንዲያልፍ አድርጋለች በዚህም በግድያ ወንጀልና በወቅቱ የሟች ቤተሰቦችን የሰነድ ማስረጃዎች ቀዳዳ በመጣል በአጠቃላይ በተደራራቢ ክስ  ዓቃቤ ህግ ጥቅምት 15 ቀን ክስ መመስረቱ ይታወሳል።

Credit : ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ

@tikvahethiopia
" ከተወሰኑ ሳምንታት በኃላ የማህበራት የቤት ዕጣ ይወጣል " - አቶ ሽመልስ ታምራት

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከሚገነባቸው ቤቶች ውስጥ ሃያ በመቶው በነባሩ የመንግስት አስተባባሪነት የሚገነቡ ሆነው እንደሚቀጥሉ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ገልጿል።

የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ታምራት ለብሄራዊ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ፤ " ያሉ ያልተጠናቀቁ ቤቶችን የማጠናቀቅ፣ የማስረከብ ስራ ይሰራል " ያሉ ሲሆን ቆጣቢው በሌሎችም መንገዶች ቢሆን ቅድሚያ የሚያገኝበት ዕድል እየተመቻቸ ነው " ብለዋል።

አቶ ሽመልስ ከተወሰኑ ሳምንታት በኃላ የማህበራት ቤት ዕጣ የሚወጣበት ሁኔታ ይፈጠራል ሲሉ ተግረዋል።

" ከቆጣቢዎቹ ነው ምዝገባ እንዲደረግ የተደረገው ፤ ቆጣቢ ሆነው በማህበር ተደራጅቼ ቤት መስራት ፈልጋለሁ የሚለው አካል በፍቃደኝነት መጥቶ እንዲመዘገብ ተደርጓል ፤ በዛ መሰረት የተለዩ የተደራጁ ማህበራት አሉ እነሱን አሁን ወደ ስርዓት እናስገባለን " ሲሉ አስረድተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውና መቆጠብ የማይችሉ ነዋሪዎችን በኪራይ ቤቶች ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጿል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia #USA

ትላንት አንቶኒ ብሊንከን ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር በስልክ መነጋገራቸውን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አሳውቋል።

የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ብሊንከን ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ጋር በነበራቸው የስልክ ውይይት የሰላም ስምምነቱ አተገባበር ላይ እና በሰሜን ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለመፍጠር እየተደረገ ስላለው ጥረት መምከራቸውን ተገልጿል።

ብሊንከን ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ክልል እንዲሁም በአጎራባች አፋር እና አማራ ክልሎች ያልተገደበ ሰብአዊ ርዳታ እና መሰረታዊ አገልግሎቶችን ወደ ነበረበት ለመመለስ እያደረገ ያለውን ጥረት እውቅና ሰጥተዋል።

ሁሉም የውጭ ሃይሎች ከትግራይ ለቀው እንዲወጡ እና የትግራይ ሃይሎችን ትጥቅ ማስፈታትን ጨምሮ የግጭት ማቆም ስምምነቱን በአስቸኳይ ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አስምረውበታል።

ብሊንከን ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር በነበራቸው ውይይት ሀገራቸው አሜሪካ በአፍሪካ ህብረት የሚመራውን የሰላም ሂደት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኗን እንዳረጋገጡ ከአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#Tigray

በናይሮቢው የሰላም ስምምነት ሰነድ ላይ ፊርማቸውን ያኖሩት የትግራይ ኃይሎች አዛዥ ጄነራል ታደሰ ወረደ በናይሮቢው ስምምነት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ባለፉት ቀናት ለኃይሎቻቸው ኦረንቴሽን ሲሰጥ እንደነበር እና ይኸው ኦረንቴሽን በቀጣይ ሁለት ቀን እንቀሚያልቅ ገልፀዋል።

ይህን የገለፁት በክልሉ ለሚገኙት የመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ ነው።

ጄኔራል ታደሰ ወረደ ምን አሉ ?

" በናይሮቢው ሰላም ስምምነት ጊዜ ሰሌዳ መሰረት የመጀመሪያው ከሰራዊቱ ጋር መግባባት ነው ስለ ሰላሙ ጉዳይ አጠቃላይ መግባባት መፍጠር ነው (orientation phase) ። ህዝቡ ጋርም ማለት ነው ፤ ምክንያቱም ህዝቡም ማወቅ አለበት ፤ ሰራዊቱም ማወቅ አለበት።

ቀጥታ ከእኛ ከስራችን ጋር በተያያዘ ፤ ከሰራዊቱ ጋር እየጨረስን ነው ፤ ከሰራዊት አዛዦች እስከታች ድረስ ስለሰላሙ የመግባባት ሁኔታ (ኦረንቴሽን) እየጨረስን ነው ያለነው ፤ ምነልባትም በዚህ ሁለት (2) ቀን ሙሉ በሙሉ እንጨርሳለን እስከታች ድረስ።

ከዛም ቀጥሎ ወደ ሰራዊቱ Disengage አድርጎ / ተላቆ ካለበት ቦታ የውጊያ ግንባሮች የማፍረስ ሰራዊቱ ወደ ተቀመጠለት ቦታ አለ እሱን ጨርሰናል ማን የት ይንቀሳቀሳል የሚለው  ወደዛ የማጓጓዝ ጉዳይ ነው ይሄ ደግሞ ተከታትሎ የሚጀምር ነው የሚሆነው ፤ የሎጅስቲክስ አቅማችን ወይም የማጓጓዝ አቅማችን እስከፈቀደ ድረስ በአንድ ጊዜም ልናነሳው እንችላለን ምናልባት የተወሰኑ ቀናት ሊወስድ ይችላል ማጓጓዝ፤ ይሄ ይጀመራል፤ Already #ጀምረነዋል

የመጀመሪያው ስራ የመግባባት ( #orientation ) ፣ የማሳመን ፣ የመተማመን ሁኔታውን ከጀመርን ጀምረናል ማለት ነው፤ በዛ ነው የጀመርነው፤ ይሄ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በኩልም እንደተጀመረ እየሰማሁ ነው።

ከእኛ በኩል እየጨረስን ነው ያለነው፤ አንድ ከፍተኛ ስራ ይሄ ነው፤ ስምምነቱን ከማድረግ አንፃር፤ why የሚሉ ነገሮችን መመለስ ነው ፤ ሰራዊቱን አንድ አስተሳሰብ አንድ ዕዝ ሆኖ እንዲንቀሳቀስ ማድረግ በቆየበት ማድረግ ነው ስለዚህ አንዱ ትልቅ ስራ ይሄ ይመስለኛል፤ ጀምረናል ብቻ ሳይሆን እየጨረስን ነው ያለነው። ከዚህ በኃላ የሚቀጥሉት ስራዎች ቀላል ናቸው።

ከእኛ በኩል ፤ #ማንኛውም በትግራይ ውስጥ ያለው የትግራይ ኃይል ከአንድ የኮማንድ ስርዓት ውስጥ ሆኖ የሚንቀሳቀስ ፣ ግዳጅ የሚፈፅም ነው ከዚህ ውጭ የሆነ ኃይል #የለንም ፤ ከዚህ ውጭ የሆነ የታጠቀ የሚባልም ኃይል የለም ፤ ትግራይ ውስጥ ያለው የኢትዮጵያ ኃይል ተመሳሳይ ነገር ነው ያለው ስለዚህ ከቁጥጥር ውጭ የሚሆን ነገር የሚኖር አይመስለኝም።

የስነምግባር ደንብ ሊሆን ሚችል ሰላሙን ለማስከበር ስምምነቱንም ተግባራዊ ለማድረግ (code of conduct) አውጥተናል እያንዳንዱ ይሄኛውን code of conduct እንዲያውቀው አድርገናል አመራሩም አባሉም ሁለተኛው ስራ ይሄ ነው ከኦረንቴሽን ጋር የተያያዘ ነው።

ኃይል ማንቀሳቀሱ ቀላል ነው የሚሆነው ፤ አቅም ነው የሚወስነው ይሄ የሎጅስቲክስ ጉዳይ ነው ፤ ስለዚህ ትግበራው ተጀምሯል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ አንዳንዶቹ በሁለቱም ዶክመንቶች ግልፅ ያልሆኑ ነገሮች አሉ more የፖለቲካው ስራ ፈጥኖ ተጀምሮ መፍታት ያለበት/ ሊፈታቸው የሚገባ። በስምምነቱ መሰረት  በክልሉ ውስጥ ያለ መስተዳደር አለ ስለዛ ትንሽ የተባለ አለ local መስተዳዳሮች በየዞኑ በየወረዳው በየቀበሌው ያሉ መስተዳደሮች አሉ ስርዓት ያለው ህዝብ የራሱ የአስተዳደር ማዋቅር ያለው ህዝብ ነው ከምስራቅ ይሁን ከደቡብ ከየትኛውም እነዚህ እንደሚቀጥሉ ነው ተስፋ የማደረገው እንጂ እኚህ እንዲፈርሱ አይደለም።

ሰራዊቱ ነው እንጂ disengage የሚያደርገው እንጂ ሲቪል መስተዳደሩን disengage የሚያደርገው የለም ይቀጥላል። የእነዚህን ደህንነት በሚመለከት መሰራት ያለበት ነገር አለ ፤ የቆየ ፖሊስ አለ እንደ አደረጃጀት ፖሊስ አለ እሱ በቀጣይ የpolitical dialogue መፍታት ያለበት ነገር አለ።

አሁን ላይ disengage ከምናደርግባቸው ግንባሮች ዓዲግራት ፣ ማይጨው ... ወዘተ የመሳሰሉ ትላልቅ ከተሞች ፤ የዞን የመስተዳደር ማዕከሎች ይቅርና እነሱ ጋርም ያሉት አክሱም ፣ ሽረ አይነትም አዲስ መስተዳደር ይቆማል ይፈርሳል ምናም የሚባል ነገር አይደለም ፤ እነዛም reset መደረግ አለበት የሲቪል መስተዳደሩ ፤ የ Poltical Dialogue ይሄን መፍታት አለበት መፍጠን ያለበት ይሆናል ፤ ይሄ በዘገየ ቁጥር ለ Conflict መነሻ ሊሆን ይችላል፤ እነዚህ ዝርዝር ነገሮች አሉ ንፁሁ የ Security Agreement መተግበር ግን ጀምረናል በጣም ጥሩ ሆኖ እንዲተገበር የ Political Dialogue ፈጥኖ መጀመር ያለበት ይሆናል። "

@tikvahethiopia
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት መቼ ይገለጻል?

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ውጤትን በተመለከተ የትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቀናል።

ሚኒስቴሩ በተለያዩ ምክንያቶች ፈተናውን ላልወሰዱ ተማሪዎች ሁለተኛ ዙር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ሰምተናል።

አጠቃላይ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ውጤት ከሁለተኛ ዙር ፈተና በኋላ የሚገለጽ መሆኑን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

More : @tikvahuniversity

@tikvahethiopia
ፎቶ፦ በአፍሪካ ህብረት/AU መሪነት የተካሄደውን የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት የሰላም ስምምነትን የመሩት ፤ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንትና በአፍሪካ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን አባሳንጆ የተመራ ልዑክ ዛሬ መቐለ ገብቷል።

Photo Credit : ትግራይ ቴሌቪዥን

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ተማሪዎች ፈተናውን ለመፈተን ዝግጅት አድርጉ " - የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ

በተለያየ ምክንያት የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል ላልተፈተኑ ተማሪዎች ፈተናውን በታህሳስ ወር መጀመሪያ ሳምንት ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርይ መምሪያ አሳውቋል።

ትምህርት መምሪያው ፦

- በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ በመሸጋገሪያ ድልድይ ተሰብሮ በደረሰው አደጋ ምክንያት የመጀመሪያውን ቀን ፈተና ያልተፈተኑ፤

- በወሊድ ምክንያት ፈተናውን ያልወሰዱ፤

- የተለያየ ማህበራዊ ችግር አጋጥሟቸው ጉዳዩ ለሚመለከተው አካል አሳውቀው ለፈተና ያልተቀመመጡ ፤

- በሀዋሳ ከተማ ማዕከላዊ ማረሚያ ትምህርት ቤት የሚገኙ ተማሪዎች ፈተናውን ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ብሏል።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ፤ " ትምህርት ሚኒስቴር ፈተናውን ላልወሰዱ ተማሪዎች በታህሳስ ወር 2015 ዓ.ም በመጀሪያ ሳምንት አከባቢ ፈተናው ለመስጠት ቅድመ ዝግጅቱን እያጠናቀቀ ነው " ያለ ሲሆን ተማሪዎች ይህንን አውቀው ፈተናውን ለመፈተን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል።

ምንጭ፦ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

" ሀይድሮሴፋለስ እና ስፓይና ቢፊዳ / የነርቭ ዘንግ " ክፍተት በጽንስ ላይ በቅድመ ወሊድ ወቅት ሊከሰቱ የሚችሉ ለህይወት አስጊ የጤና እክሎች ናቸው፡፡

የነርቭ ዘንግ ክፍተት ተጠቂ በሆኑ ላይ የመንቀሳቀስ ዕክል፣ የስሜት ማጣት፣ ሽንትና ሰገራ የመቆጣጠር ችግሮች እና ትምህርት/ነገሮችን የመረዳት ዕክልን ያስከትላል፡፡

በዚህም መሰረት ለነረቭ ዘንግ ክፍተት ተጠቂዎች የሚያስፈልገውን ሁሉን አቀፍ እንክብካቤ ለማድረግ የሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት ያስፈልጋል፡፡

ትላንት የጤና ሚኒስቴር ከሆፕ ኤስ. ቢ. ኤች. ጋር በመተባበር በአለም አቀፍ ፌዴሬሽን በተወሰነው መሰረት “ድምፃችንን ከፍ እናድርግ” በሚል መሪ ቃል የስፓይና ቢፊዳ እና ሃይድሮሴፋለስ ቀን በሃገር አቀፍ ደረጃ አክብሯል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ፦ በአፍሪካ ህብረት/AU መሪነት የተካሄደውን የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት የሰላም ስምምነትን የመሩት ፤ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንትና በአፍሪካ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን አባሳንጆ የተመራ ልዑክ ዛሬ መቐለ ገብቷል። Photo Credit : ትግራይ ቴሌቪዥን @tikvahethiopia
#Update

" በሁለት ሶስት ቀን ውስጥ ሽረ ላይ ስብሰባ ይደረጋል ፤ በአንዳንድ ቴክኒካል ጉዳዮች ዘሪያ የሁለቱም ጦር ተወካዮች ተገናኝተው ይወያያሉ "

ትላንት በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል የተካሄደውን የሰላም ድርድር / ስምምነቱን የመሩት የቀድሞው የናይጄሪያው ፕሬዜዳንት የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ የትግራይ መዲና ፤ #መቐለ መግባታቸው ይታወሳል።

ኦባሳንጆ ወደ መቐለ ያመሩት የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ምክትል ፕሬዜዳንት ፑምዝሎ ማላምቦ፣ የአፍሪካ ህብረት የፖለቲካ ጉዳዮች የፀጥታ እና የሰላም ኮሚሽነር አምባሳደር ባንኮሊ አዱዬ ከያዘ ልዑክ ጋር ነበር።

በመቐለ ከሃይማኖት አባቶች ጋር እንዲሁም ክልሉን እያስተዳደሩ ካሉት አካላት ጋር ምክክር አድርገውም ነበር።

በምክክሩን ምን ተነሳ ? ምን ተባለ ?

(ከሃይማኖት አባቶች ጋር በነበረ ውይይት/ የሃይማኖት አባቶች የተናገሩት)

- የትግራይ ህዝብ የሰብዓዊ እርዳታ / መድሃኒት በፍጥነት ማግኘት ባለመቻሉ ለከፍተኛ አደጋ መጋለጡን ገልፀዋል።

- የኤርትራ ኃይሎች በያዟቸው ቦታዎች ከፍተኛ ግፍ እየተፈፀመ መሆኑን አስረድተዋል።

(ልዑካን ቡድኑ)

- አፋጣኝ ሰብዓዊ እርዳታ እንዲገባ የውጭ ኃይሎችም እንዲወጡ ከመንግስት ጋር መነጋገራቸውን ገልፀዋል።

ክልሉን እያስተዳደሩት ካሉት ሲቪል እና ወታደራዊ አመራሮች ጋር በተደረገው ውይይት ወቅት ስለተነሱት ሃሳቦች አምባሳደር ወንድሙ አሳምነው የተናገሩት ፦

- የልዑካን ቡድኑ የሰላም ስምምነቱ ከተፈረመ በኃላ አፈፃፀሙ ምን እንደሚመስል ለመመልከት ፤ ለስምምነቱ ተግባራዊነት መስጠት የሚችሉት ድጋፍ  ይኖር እንደሆነና ድጋፍ ለመስጠት ነው መቐለ የገቡት።

- ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካሄል እስካሁን ስምምነቱን ለማስፈፀም እየተሰሩ ስላሉት ስራዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል።

- ስምምነቱ ትልቅ ስምምነት መሆኑንና በሁሉም ትብብር ሊፈፀም የሚገባው በመሆኑ ባለፉት ሁለት ሳምንታት አጠቃላይ ህዝቡ የመንግስት ፣ የድርጅት አመራሮች፣ ሰራተኞች፣ ከላይ እስከታች ያሉ ወታደራዊ አካላት እንዲወያዩበትና መግባባት ላይ እንዲደረስ የተሰራ ሲሆን አጠቃላይ ህዝቡ ስምምነቱን መቀበሉን ዶ/ር ደብረፅዮን ተናግረዋል።

- ዶ/ር ደብረፅዮን  ፤ ለልዑካን ቡድኑ ህዝቡ በሰላም ስምምነቱ ላይ መስማማቱን አስረድተዋል።

- ስምምነቱ ጥሩ ነው ግን እርዳታ በብዛት ከማስጋባት እና ከአገልግሎት መጀመር ጋር በተያያዘ ከሚፈለገው ፍጥነት አንፃር እየሄደ አይደለም ፤ አገልግሎት ለማስጀመር እየታዩ ያሉት ምልክቶች ጥሩ ናቸው ግን ካለው ችግር አንፃር ፍጥነት ያንሰዋል የሚል ነገር ተነስቷል።

- ስምምነቱ ሰፊ ከመሆኑ ጋር በተያያዘ ስምምነቱን የማስፈፀሚያ ፕላን መሰራቱ ተብራርቷል።

- " በተደረገው የሰላም ስምምነት የስምምነቱ ፈራሚ ያልሆኑ አካላት አሉ ፤ ፈራሚ አለመሆን ብቻ ሳይሆን ስምምነቱ እንዲደናቀፍ የሚፈልጉ ኃይሎች አሉ ዋናው የኤርትራ መንግስት ነው ፤ የኤርትራ መንግስት እኛ ኢትዮጵያውያን የቤታችንን ጉዳይ ለማስተካከል የተስማማነውን ስምምነት ለማፍረስ እየናካካን ነው ፤ ጦርነቱ ድጋሚ እንዲጫር ለማድረግ ወንጀል እየሰራ ነው ፤ በሺዎች እያለቁ ስለመሆኑ ብዙ ማስረጃ አለን እሱን ማስረጃ ለልዑካኑ ተናግረናል " ሲሉ አምባሳደር ወንድሙ አሳምነው ተናግረዋል።

- "አሁን ላይ ሰራዊቱ መካከል በጣም ተስፋ የሚሰጥ ግኝኑነት ነው እየተፈጠረ ያለው ፤ ይሄ ቀረ ሊባልበት በማይችል ሁኔታ ሰራዊቱ ተግባብቶ እየሰራ ነው። በሁለት ሶስት ቀን ውስጥ ሽሬ ላይ ስብሰባ ይደረጋል በአንዳንድ ቴክኒካል ጉዳዮች ዘሪያ የሁለቱም ጦር ተወካዮች ተገናኝተው ይወያያሉ። " ሲሉ አምባሳደር ወንድሙ ተናግረዋል።

- " አሁን ላይ ችግር እየሆነ ያለው የኤርትራ ሰራዊት ነው ፤ የሰላም አጋጣሚውን ለማፍረስ ፤ እኛም ደግሞ በቁጣ ተነሳስተን ጦርነት እንድንገባ ህዝቡን እየፈጀ ነው ፤ ስለዚህ አንደኛ የኢትዮጵያ መንግስት ኃላፊነት አለበት ፤ ሁለተኛ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኃላፊነት አለበት እየተፈፀመ ያለው ወንጀል ዓለም አቀፍ ነው ፤ ስምምነቱ የተፈረመው በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ምስክርነት ነው ኃላፊነት አለባችሁና አስቁሙልን ብለናቸዋል። ጦርነቱን እዚህ ያደረሰው ይኸው ኃይል ነው፤ እንዳይቆምም እየሰራ ነው ስለዚህ የኢትዮጵያ መንግስት እኛ ሁላችንም ኢትዮጵያውያን እና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይሄን ወንጀል ለማስቆም ጥረት ማድረግ አለብን ብለን ገልፀንላቸዋል " ሲሉ አምባሳደር ወንድሙ አሳምነው ለክልሉ የመገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
#UN

እ.ኤ.አ. ከህዳር አጋማሽ ጀምሮ በኢትዮጵያ መንግስት እና በሰብአዊ ድጋፍ አጋሮች አማካኝነት ከ17,000 ሜትሪክ ቶን በላይ የእርዳታ እህል ትግራይ መድረሱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዛሬ አሳውቋል።

ድርጅቱ በሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል ተጨማሪ በግጭት የተጎዱ ወገኖችን ለመድረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UN እ.ኤ.አ. ከህዳር አጋማሽ ጀምሮ በኢትዮጵያ መንግስት እና በሰብአዊ ድጋፍ አጋሮች አማካኝነት ከ17,000 ሜትሪክ ቶን በላይ የእርዳታ እህል ትግራይ መድረሱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) ዛሬ አሳውቋል። ድርጅቱ በሰሜን ኢትዮጵያ ክፍል ተጨማሪ በግጭት የተጎዱ ወገኖችን ለመድረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል። @tikvahethiopia
#WFP

ከሰላም ስምምነቱ በኃላ...

(የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) የዛሬ ሪፖርት)

- የዓለም ምግብ ፕሮግራም #አራቱም የተከፈቱትን የመንገድ ኮሪደሮች በመጠቀም ስራ ከጀመረበት እኤአ ከህዳር 15 ጀምሮ በ96 የጭነት መኪናዎች 170 ሺህ ሰዎችን ሊመግብ የሚችል ከ2,400 ሜትሪክ ቶን በላይ ምግብ እንዲሁም 100,000 ሊትር ነዳጅ ወደ ትግራይ አጓጉዟል።

- በWFP የሚመራው የሎጂስቲክስ ክላስተር 250 ሜትሪክ ቶን የሰብአዊ ድጋፍ ካርጎ ከጎንደር፣ ኮምቦልቻ እና ሰመራ ለስምንት ተባባሪ አጋሮች የህክምና ቁሳቁሶችን ጨምሮ በአየር እንዲጓጓዝ አመቻችቷል።

- ካለፈው እኤአ ነሃሴ ወር መጫረሻ በኃላ የWFP የUNHAS የመንገደኞች በረራ ዛሬ ወደ #መቐለ አድርጓል። በረራውን ደረገው ከፌዴራል ፍቃድ ካገኘ በኃላ ሲሆን ወደ መቐለ መደበኛ የUNHAS በረራ መቀጠል አለበት ብሏል።

- WFP ፤ በትግራይ ሰሜናዊ ምዕራብ እና ደቡብ ዞኖች ለሚገኙ ወረዳዎች በአማራ በኩል አዲስ የሰብአዊ ድጋፍ አገልግሎት ቢያገኙም ወደ አንዳንድ የትግራይ #ምስራቃዊ እና #ማዕከላዊ ዞኖች አሁንም መግባት ውስን መሆኑንና እስከ 170 ሺህ የሚደርሱ እናቶችና ህፃናት የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው WFP አሳውቋል።

- ወደ ትግራይ የሚያስገቡ መንገዶች ከተከፈቱ ወዲህ WFP በሰሜን ምእራብ ዞን ማይ ፀብሪ እና በደቡብ ዞን አላማጣ ላሉ ከ100,000 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች እህል ማቅረቡን ገልጿል። በህዳር ወር መጀመሪያ ላይም በመቐለ 540,000 ሰዎችን ደርሷል። ከህዳር ወር መጀመሪያ ጀምሮ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ፤ በትግራይ ክልል የምግብ ድጋፍ ከሚያስፈልጋቸው 2.1 ሚሊዮን ሰዎች ውስጥ መድረስ የቻለው 29 በመቶውን መሆኑን ገልጿል።

ተጨማሪ ያንብቡ : https://telegra.ph/WFP-11-25

@tikvahethiopia