TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጥብቅ ማስጠንቀቂያ‼️

#ሼር #Share

በምዕራብ እና ማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች ለምትገኙ በሙሉ -- የተከሰተውን #ግጭት ለማርገብ እና ሰላም ለማስከበር የመከላከያ ሰራዊት ከዛሬ ጀምሮ ይሰራል።

አስተማማኝ ሰላም እስኪገኝ ድረስ #የተከለከሉ ተግባራት፦

• ከጎንደር - መተማ መስመር 5 ኪ.ሜ. ክልል በቡድንም ይሁን በግል ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ #በጥብቅ የተከለከለ ነው።

• በሁመራ መስመርም በተመሳሳይ 5 ኪ.ሜ ክልል በቡድንም ይሁን በግል ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

• በጎንደር ከተማ ከፀጥታ አካላት ውጭ ማንኛውም ሰው መሳሪያ ታጥቆ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

• "ሰላም ለማስከበር" በሚል ሰበብ ማንኛውም ግለሰብ ከኮሚሽኑ ፍቃድ ውጭ መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

#ማንኛውም በፀጥታ መደፍረስ ተሳትፎ ያደረገ ኃይል #እርምጃ ይወሰድበታል‼️

የሰላም ጥሪ፦

የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጎንደር ወጣቶችና አክቲቪስቶች በጎንደር እና በአካባቢው ሰላም እንዲሰፍን ከፀጥታ ሀይሉ ጋር እንድትሰሩ #መከላከያ_ሰራዊት ጥሪ አቅርቧል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ #TIKVAHETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጥብቅ ማስጠንቀቂያ‼️

#ሼር #Share

በምዕራብ እና ማዕከላዊ ጎንደር ዞኖች ለምትገኙ በሙሉ -- የተከሰተውን #ግጭት ለማርገብ እና ሰላም ለማስከበር የመከላከያ ሰራዊት ከዛሬ ጀምሮ ይሰራል።

አስተማማኝ ሰላም እስኪገኝ ድረስ #የተከለከሉ ተግባራት፦

• ከጎንደር - መተማ መስመር 5 ኪ.ሜ. ክልል በቡድንም ይሁን በግል ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ #በጥብቅ የተከለከለ ነው።

• በሁመራ መስመርም በተመሳሳይ 5 ኪ.ሜ ክልል በቡድንም ይሁን በግል ትጥቅ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

• በጎንደር ከተማ ከፀጥታ አካላት ውጭ ማንኛውም ሰው መሳሪያ ታጥቆ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

• "ሰላም ለማስከበር" በሚል ሰበብ ማንኛውም ግለሰብ ከኮሚሽኑ ፍቃድ ውጭ መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።

#ማንኛውም በፀጥታ መደፍረስ ተሳትፎ ያደረገ ኃይል #እርምጃ ይወሰድበታል‼️

የሰላም ጥሪ፦

የአማራ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የጎንደር ወጣቶችና አክቲቪስቶች በጎንደር እና በአካባቢው ሰላም እንዲሰፍን ከፀጥታ ሀይሉ ጋር እንድትሰሩ #መከላከያ_ሰራዊት ጥሪ አቅርቧል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ #TIKVAHETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ATTENTION

ሰንበቴ !

የሰንበቴ ከተማ አስተዳደር ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ከነሐሴ 26/ 2014 ዓ/ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ የሰዓት እላፊ ገደብ አውጇል።

በዚህም መሰረት ፦

- የከተማ ባለ 3 እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጆች) ከምሽቱ 12 ሰአት ጀምሮ በከተማው ውስጥ ማሽከርከር ተከልክለዋል።

- ከተመደበው የጸጥታ ኃይል በስተቀር ከምሽቱ 3 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ #ማንኛውም_ሰው መንቀሳቀስ ተከልክሏል።

የተጠቀሰው የሰአት እላፊ ገደብ ጥሶ የተገኘ ግለሰብ ላይ አስፈላጊው የህግ እርምጃ እንዲወሰድ ታዟል ሲል የከተማ አስተዳደሩ አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia
#Tigray

በናይሮቢው የሰላም ስምምነት ሰነድ ላይ ፊርማቸውን ያኖሩት የትግራይ ኃይሎች አዛዥ ጄነራል ታደሰ ወረደ በናይሮቢው ስምምነት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ባለፉት ቀናት ለኃይሎቻቸው ኦረንቴሽን ሲሰጥ እንደነበር እና ይኸው ኦረንቴሽን በቀጣይ ሁለት ቀን እንቀሚያልቅ ገልፀዋል።

ይህን የገለፁት በክልሉ ለሚገኙት የመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ ነው።

ጄኔራል ታደሰ ወረደ ምን አሉ ?

" በናይሮቢው ሰላም ስምምነት ጊዜ ሰሌዳ መሰረት የመጀመሪያው ከሰራዊቱ ጋር መግባባት ነው ስለ ሰላሙ ጉዳይ አጠቃላይ መግባባት መፍጠር ነው (orientation phase) ። ህዝቡ ጋርም ማለት ነው ፤ ምክንያቱም ህዝቡም ማወቅ አለበት ፤ ሰራዊቱም ማወቅ አለበት።

ቀጥታ ከእኛ ከስራችን ጋር በተያያዘ ፤ ከሰራዊቱ ጋር እየጨረስን ነው ፤ ከሰራዊት አዛዦች እስከታች ድረስ ስለሰላሙ የመግባባት ሁኔታ (ኦረንቴሽን) እየጨረስን ነው ያለነው ፤ ምነልባትም በዚህ ሁለት (2) ቀን ሙሉ በሙሉ እንጨርሳለን እስከታች ድረስ።

ከዛም ቀጥሎ ወደ ሰራዊቱ Disengage አድርጎ / ተላቆ ካለበት ቦታ የውጊያ ግንባሮች የማፍረስ ሰራዊቱ ወደ ተቀመጠለት ቦታ አለ እሱን ጨርሰናል ማን የት ይንቀሳቀሳል የሚለው  ወደዛ የማጓጓዝ ጉዳይ ነው ይሄ ደግሞ ተከታትሎ የሚጀምር ነው የሚሆነው ፤ የሎጅስቲክስ አቅማችን ወይም የማጓጓዝ አቅማችን እስከፈቀደ ድረስ በአንድ ጊዜም ልናነሳው እንችላለን ምናልባት የተወሰኑ ቀናት ሊወስድ ይችላል ማጓጓዝ፤ ይሄ ይጀመራል፤ Already #ጀምረነዋል

የመጀመሪያው ስራ የመግባባት ( #orientation ) ፣ የማሳመን ፣ የመተማመን ሁኔታውን ከጀመርን ጀምረናል ማለት ነው፤ በዛ ነው የጀመርነው፤ ይሄ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በኩልም እንደተጀመረ እየሰማሁ ነው።

ከእኛ በኩል እየጨረስን ነው ያለነው፤ አንድ ከፍተኛ ስራ ይሄ ነው፤ ስምምነቱን ከማድረግ አንፃር፤ why የሚሉ ነገሮችን መመለስ ነው ፤ ሰራዊቱን አንድ አስተሳሰብ አንድ ዕዝ ሆኖ እንዲንቀሳቀስ ማድረግ በቆየበት ማድረግ ነው ስለዚህ አንዱ ትልቅ ስራ ይሄ ይመስለኛል፤ ጀምረናል ብቻ ሳይሆን እየጨረስን ነው ያለነው። ከዚህ በኃላ የሚቀጥሉት ስራዎች ቀላል ናቸው።

ከእኛ በኩል ፤ #ማንኛውም በትግራይ ውስጥ ያለው የትግራይ ኃይል ከአንድ የኮማንድ ስርዓት ውስጥ ሆኖ የሚንቀሳቀስ ፣ ግዳጅ የሚፈፅም ነው ከዚህ ውጭ የሆነ ኃይል #የለንም ፤ ከዚህ ውጭ የሆነ የታጠቀ የሚባልም ኃይል የለም ፤ ትግራይ ውስጥ ያለው የኢትዮጵያ ኃይል ተመሳሳይ ነገር ነው ያለው ስለዚህ ከቁጥጥር ውጭ የሚሆን ነገር የሚኖር አይመስለኝም።

የስነምግባር ደንብ ሊሆን ሚችል ሰላሙን ለማስከበር ስምምነቱንም ተግባራዊ ለማድረግ (code of conduct) አውጥተናል እያንዳንዱ ይሄኛውን code of conduct እንዲያውቀው አድርገናል አመራሩም አባሉም ሁለተኛው ስራ ይሄ ነው ከኦረንቴሽን ጋር የተያያዘ ነው።

ኃይል ማንቀሳቀሱ ቀላል ነው የሚሆነው ፤ አቅም ነው የሚወስነው ይሄ የሎጅስቲክስ ጉዳይ ነው ፤ ስለዚህ ትግበራው ተጀምሯል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ አንዳንዶቹ በሁለቱም ዶክመንቶች ግልፅ ያልሆኑ ነገሮች አሉ more የፖለቲካው ስራ ፈጥኖ ተጀምሮ መፍታት ያለበት/ ሊፈታቸው የሚገባ። በስምምነቱ መሰረት  በክልሉ ውስጥ ያለ መስተዳደር አለ ስለዛ ትንሽ የተባለ አለ local መስተዳዳሮች በየዞኑ በየወረዳው በየቀበሌው ያሉ መስተዳደሮች አሉ ስርዓት ያለው ህዝብ የራሱ የአስተዳደር ማዋቅር ያለው ህዝብ ነው ከምስራቅ ይሁን ከደቡብ ከየትኛውም እነዚህ እንደሚቀጥሉ ነው ተስፋ የማደረገው እንጂ እኚህ እንዲፈርሱ አይደለም።

ሰራዊቱ ነው እንጂ disengage የሚያደርገው እንጂ ሲቪል መስተዳደሩን disengage የሚያደርገው የለም ይቀጥላል። የእነዚህን ደህንነት በሚመለከት መሰራት ያለበት ነገር አለ ፤ የቆየ ፖሊስ አለ እንደ አደረጃጀት ፖሊስ አለ እሱ በቀጣይ የpolitical dialogue መፍታት ያለበት ነገር አለ።

አሁን ላይ disengage ከምናደርግባቸው ግንባሮች ዓዲግራት ፣ ማይጨው ... ወዘተ የመሳሰሉ ትላልቅ ከተሞች ፤ የዞን የመስተዳደር ማዕከሎች ይቅርና እነሱ ጋርም ያሉት አክሱም ፣ ሽረ አይነትም አዲስ መስተዳደር ይቆማል ይፈርሳል ምናም የሚባል ነገር አይደለም ፤ እነዛም reset መደረግ አለበት የሲቪል መስተዳደሩ ፤ የ Poltical Dialogue ይሄን መፍታት አለበት መፍጠን ያለበት ይሆናል ፤ ይሄ በዘገየ ቁጥር ለ Conflict መነሻ ሊሆን ይችላል፤ እነዚህ ዝርዝር ነገሮች አሉ ንፁሁ የ Security Agreement መተግበር ግን ጀምረናል በጣም ጥሩ ሆኖ እንዲተገበር የ Political Dialogue ፈጥኖ መጀመር ያለበት ይሆናል። "

@tikvahethiopia
#FDREDefenseForce

የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሠ ምን አሉ ?

" ለኢትዮጵያ ዕድገት እንቅፋት ለመፍጠር የሚጥሩ በአካባቢያችን ያሉ #ታሪካዊ_ጠላቶቻችን እና #አዳዲስ_ኃይሎች እየተሰባሰቡ እንዳለ እያየን ነው።

እነኝህ ጠላቶች ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ በቅርበት እየተከታተልን እንገኛለን።

ሀገራችን ኢትዮጵያ የማንንም ሃገር ብሔራዊ ጥቅም መንካት ተገቢ አለመሆኑን በማመን በዘመኗ የሌላ ሀገር ብሔራዊ ጥቅም ነክታ አታውቅም አሁንም አትነካም ታሪኳም አይደለም።

የሌላን ሀገር ብሔራዊ ጥቅም እንደማንነካው ሁሉ እኛም የሃገራችንን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈን አንሰጥም።

ለሃገራችን ሁለንተናዊ ብሔራዊ ጥቅም እንደወትሮው ሁሉ ዛሬም ዘብ እንቆማለን። "

ጄነራሉ ይህን የተናገሩት " አዋሽ አርባ " የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሜካናይዝድ ጦርን እና እየወሰደ ያለውን ስልጠና ከጎበኙ በኃላ ነው።

ሰልጣኞቹ በስነ-ልቦና ዝግጁነት ብቁ በመሆን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም እና ክብር መረጋገጥ ሲባል የሚወስዱትን ሙያዊ ስልጠና በፍጥነት ማጠናቀቅና ለሚሰጣቸው #ማንኛውም_ግዳጅ ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው #አፅንኦት ሰጥተዋል።

#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Asset Recovery draft proc. Amharic from COM to HPR (1).pdf
#ኢትዮጵያ

የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅ ፤ " ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ስለማስመለስ " ምን ይላል ?

➡️ #ማንኛውም_ሰው በቀጥታ ሆነ #በተዘዋዋሪ ያለው ንብረት ወይም የኑሮ ደረጃው አሁን ላይ ባለበት ወይም አስቀድሞ በነበረበት ስራ ወይም በሌላ መንገድ ከሚያገኘው ወይም ሲያገኝ ከነበረው ህጋዊ ገቢ የማይመጣጠን እንደሆነ እና የንብረቱን ወይም የኑሮ ደረጃውን ምንጭ በተመለከተ ምክንያታዊ የሆነ የወንጀል ጥርጣሬ በኖረ ጊዜ የዚህ አይነቱ የኑሮ ደረጃ ወይም ያለው ንብረት እንዴት ሊኖረው እንደቻለ ለፍርድ ቤት ካላስረዳ በስተቀር ንብረቱ #ይወረሳል

➡️ ህጋዊ ገቢ እንዳለው የሚያስረዳ የተመዘገበበት ስርዓት የሌለው ወይም ገቢው እነስተኛ በመሆኑ #ከግብር_ነጻ የሆነ ሰው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያለው ንብረት ወይም የኑሮ ደረጃው ከሚያገኘው ወይም ሲያገኝ ከነበረው ህጋዊ ገቢ የማይመጣጠን እንደሆነ የዚህ አይነቱ የኑሮ ደረጃ ወይም ያለው ንብረት እንዴት ሊኖረው እንደቻለ ለፍርድ ቤት ካላስረዳ በስተቀር ንብረቱ ይወረሳል፡፡

➡️ " በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ ያፈራው ንብረት " ማለት ፦

° በራሱ ስም የሚገኝ ንብረት፣

° በራሱ ስም ባይሆንም ለራሱ ጥቅም ሲያዝበት ወይም ሲቆጣጠረው የነበረው ንብረት ፣

° የተጠቀመው ወይም ደግሞ ያስወገደው ንብረት፣

° በሽያጭ ፣ በስጦታ ወይም በማንኛውም ሁኔታ #ያስተላለፈውን ንብረት ይጨምራል፡፡

➡️ ዐቃቤ ሕግ " #ምንጩ_ያልታወቀ_ነው " ብሎ የጠረጠረውን ማንኛውንም ንብረት ዝርዝር እና የተገኘበትን አግባብ የሚያሳይ መግለጫ እንዲያቀርብ በፅሁፍ ጥያቄ የቀረበለት ማንኛውም ሰው ጥያቄው በደረሰው በ1 ወር ጊዜ ውስጥ ለዐቃቤ ህግ ዝርዝር ማስረጃዎችን በማያያዝ በፅሁፍ ማቅረብ ይኖርበታል።

➡️ የንብረቱን ምንጭ እንዲያስረዳ የተጠየቀው ሰው የንብረቱን ምንጭ ለማስረዳት የሚያቀርበው ማስረጃ ሀጋዊ መሆን አለበት።

ተጨማሪ ....

☑️ አንድ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ አውጥቶ የሚሰራ ነጋዴ ወይም ድርጅት ሕጋዊ ገቢው ተብሎ የሚገመተው ለተገቢው ባለስልጣን በወሩ ወይም በአመቱ ከንግዱ ያገኘሁት ብሎ ያሳወቀው የገቢ መጠን ሲሆን ወይም ተገቢው ታክስ የተከፈለባቸው ገቢዎች ሆነው ሲገኙና የታክስ ደረሰኝ ሲቀርብ ሲሆን ከዚህ ውጪ ህጋዊ ታክስ ያልተከፈለባቸው ገቢዎች ከህጋዊ ገቢ ውጪ ያፈራው ምንጩ ያልታወቀ ሀብት ተብሎ ሊወሰን ይችላል።

☑️ ምንጩን ሲያስረዳ " ከውጪ የተላከለኝ ገንዘብ ነው " የሚል ማንኛውም ግለሰብ ገንዘቡ በሕጋዊ መንገድ #በባንክ_ሥርዓት ውስጥ ያለፉ ግብይቶች ወይም ክፍያዎች ስለመሆናቸው በተገቢው የባንክ ደረሰኝ አስደግፎ ማቅረብ የሚገባው ሲሆን ከዚህ ውጪ ያለው ግን እንደ ምንጩ ያልታወቀ ገቢ ተደርጎ ይቆጠራል።

በረቂቅ አዋጁ ላይ #ምንጩ_ያልታወቀ_ንብረት ክስ የሚቀርብበት ጊዜ እና የገንዘብ መጠን ተደንግጓል፡፡

በዚህም አዋጁ ወደኋላ 10 ዓመታት ተመልሶ የሚሠራ ሲሆን ይህንንም ለመክሰስ የ5 ሚሊዮን የገንዘብ ገደብ ተቀምጧል፡፡

ይህ የገንዘብ ገደብ የተቀመጠበት ዋነኛው ምክንያት በአሁኑ ወቅት ላይ በሀገሪቱ ያለውን የሰው ሃይል ፣ የመክሰስ አቅም እና የፋይናንስ አቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት አነስተኛ የሃብት መጠን ያላቸውን ግለሰቦች በመተው ከፍተኛ ንብረት ያላቸውን ተጠያቂ ለማድረግ እንደሆነ ተብራርቷል።

ከዚህ በተጨማሪ ሕጉ ወደኋላ (10 ዓመታት) ተመልሶ እንደመስራቱ በሀገሪቱ #ኢኮኖሚ#ማሕበራዊ እና #የፋይናንስ_ሥርዓት ላይ ከፍተኛ የሆነ ተጽዕኖ ያደርሳሉ ተብሎ የሚገመቱትን ግለሰቦችና ሕጋዊ ሰውነት ያላቸው ድርጅቶችን ተጠያቂ ማድረግ የተሻለ አማራጭ ሆኖ በመገኘቱ እንደሆነ ተብራርቷል።

አዋጁ ሥራ ላይ ከዋለ በኋላ ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ተጠያቂነት ያለምንም የገንዘብ መጠን ተፈጻሚ ይደረጋል።

ስለ ረቂቅ አዋጁ አጭር ማብራሪያ ⬇️
https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/88313

ረቂቅ አዋጁ⬇️
https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/88314

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM