" ከተወሰኑ ሳምንታት በኃላ የማህበራት የቤት ዕጣ ይወጣል " - አቶ ሽመልስ ታምራት

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከሚገነባቸው ቤቶች ውስጥ ሃያ በመቶው በነባሩ የመንግስት አስተባባሪነት የሚገነቡ ሆነው እንደሚቀጥሉ የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ገልጿል።

የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ታምራት ለብሄራዊ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ፤ " ያሉ ያልተጠናቀቁ ቤቶችን የማጠናቀቅ፣ የማስረከብ ስራ ይሰራል " ያሉ ሲሆን ቆጣቢው በሌሎችም መንገዶች ቢሆን ቅድሚያ የሚያገኝበት ዕድል እየተመቻቸ ነው " ብለዋል።

አቶ ሽመልስ ከተወሰኑ ሳምንታት በኃላ የማህበራት ቤት ዕጣ የሚወጣበት ሁኔታ ይፈጠራል ሲሉ ተግረዋል።

" ከቆጣቢዎቹ ነው ምዝገባ እንዲደረግ የተደረገው ፤ ቆጣቢ ሆነው በማህበር ተደራጅቼ ቤት መስራት ፈልጋለሁ የሚለው አካል በፍቃደኝነት መጥቶ እንዲመዘገብ ተደርጓል ፤ በዛ መሰረት የተለዩ የተደራጁ ማህበራት አሉ እነሱን አሁን ወደ ስርዓት እናስገባለን " ሲሉ አስረድተዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውና መቆጠብ የማይችሉ ነዋሪዎችን በኪራይ ቤቶች ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልጿል።

@tikvahethiopia