TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" አሜሪካ ዩክሬንን ከመደገፏ በፊት የትምህርት ቤቶቿ ደኅንነት ላይ ታተኩር " - ትራምፕ

የቀድሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ የትምህርት ቤቶችን ደኅንነት ለማረጋገጥ የምታወጣው የገንዘብ ድጋፍ ለዩክሬን ከሚቀርበው እርዳታ ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል ብለዋል።

ይህ የትራምፕ ንግግር የተሰማው በቴክሳስ ግዛት በት/ቤት ውስጥ 19 ህጻናት 2 መምህራኖቻቸው በአንድ በታጠቀ ወጣት ከተገደሉ በኋላ ነው።

የጦር መሣሪያን በተመለከተ እየተካሄደ በሚገኝ ጉባኤ ላይ ንግግር ያደረጉት ትራምፕ፣ አሜሪካ ወደ ዩክሬን ቢሊዮን ዶላሮችን መላክ ከቻለች " በአገራችን ውስጥ ያሉ ልጆቻችንን ደኅንነት ለመጠበቅ እንዲውል የምንችለውን ሁሉ ማድረግ አለብን" ብለዋል።

" በአፍጋኒስታን እና ኢራቅ ትሪሊዮን ዶላሮችን ብናፈስም ጠብ ያለ ነገር ግን ያለም” ያሉት ትራምፕ " የተቀረውን ዓለም ከመገንባታችን በፊት በአገራችን ለልጆቻችን ደኅንነቱ የተጠበቀ ትምህርት ቤት ልንገነባ ይገባል” ሲሉ አክለዋል።

በዚህ ወር መግቢያ ላይ የአሜሪካ ም/ቤት ለዩክሬን ወታደራዊ እርዳታ የሚውል 40 ቢሊዮን ዶላር እንዲላክ ወሰኗል። ጦርነቱ ከተነሳ ጊዜ ጀምሮ 54 ቢሊዮን ዶላር ለዩክሬን አጽድቋል።

ትራምፕ የጦር መሣሪያ ቁጥጥርን የተቃወሙ ሲሆን ሰላማዊ አሜሪካውያን ራሳቸውን "ከመጥፎ" ሰዎች እንዲከላከሉ ሊፈቀድላቸው ይገባል ብለዋል።

በጦር መሳሪያ ላይ ቁጥጥር ከማድረግ ይልቅ በት/ቤቶች ከላይ እስከ ታች የሚዘረጋ የደኅንነት ሥርዓት ሊኖር ይገባል ብለዋል።

በት/ቤቶች መግቢያ ላይ ብረት ነክ ነገሮችን የሚለዩ መሣሪያዎችን ማስቀመጥ እና ቢያንስ 1 የታጠቀ ፖሊስ እንዲኖር ማድረግን ጨምሮ የተጠናከረ ጥበቃ ሊኖር ይገባል ሲሉ ገልጸዋል።

ይህ እንዳይሆን እንቅፋት የሆኑት ዲሞክራቶች ናቸው ሲሉ ከሰዋል።

#ቢቢሲ

@tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ ፦

#ካናዳ ፦ የካናዳው ጠ/ሚ ጀስቲን ትሩዶ አነስተኛ የእጅ ሽጉጥ መግዛትም ሆነ መታጠቅ እንዲከለከል ጠይቀዋል። የትሩዶ መንግሥት በጠቅላላው የእጅ ሽጉጥ መግዛት ሆነ ቤት ማስቀመጥ በሕግ እንዲያስቀጣ ረቂቅ እያወጣ ነው። ረቂቁ እንደሚለው ካናዳዊያን የእጅ ሽጉጦቻቸውን ባይነጠቁም ከዚህ በኋላ አዲስ መግዛት ግን አይችሉም። ትሩዶ ይህን ሐሳብ ያፈለቁት በአሜሪካዋ ቴክሳስ ግዛት አንድ አፍላ ታጣቂ 19 ሕፃናትን ተኩሶ ከገደለ በኋላ ነው።

➡️ #እስራኤል #UAE ፦ እስራኤል እና የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ የነፃ ንግድ ስምምነት ተፈራርመዋል ፤ ይህ እስራኤል ከአረብ ሀገር ጋር ያደረገችው የመጀመሪው ትልቅ ስምምነት ነው።

➡️ #ሴኔጋል ፦ የሴኔጋል ፖሊስ በአንድ ሆስፒታል ውስጥ በደረሰው እና የ11 ህጻናት ህይወት ከቀጠፈው የእሳት አደጋ ጋር በተያያዘ ለመጀመሪያ ጊዜ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተሰምቷል።

➡️ #ሩስያ ፦ በያዝነው ዓመት 70ኛ ዓመታቸውን የሚደፍኑት የሩስያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጤና እክል ምናልባትም በካንሰር ህመም እየተሰቃዩ ሳይሆን አይቀርም የሚሉ ያልተረጋገጡ የመገናኛ ብዙኃን ሪፖርቶች እየወጡ ናቸው። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ግን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ታመዋል መባሉን ሀሰት ሲሉ አስተባበሉ። ላቭሮቭ ፕሬዚዳንት ፑቲን በየቀኑ በአደባባይ እንደሚታዩ እና እንደማኛውም ጤነኛ ሰው የህመም ምልክት አያታይባቸውም ብለዋል።

➡️ #ሶማሊያ ፦ የሶማሊያ ባይዶዋ ከተማ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድን ለመቀበል በዝግጅት ላይ ነች። ከተማዋ ፕሬዝዳንቱ ፈርማጆን አሸንፈው ዳግም የፕሬዜዳንትነት መንበሩን ከተረከቡ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚጎበኟት ከተማ ትሆናለች።

#ቢቢሲ #ቲአርቲ #ሲጂቲኤን #SNTV

@tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ 📣

➡️ #ካሜሮን፦ በካሜሩን መገንጠልን አላማቸው አድርገው ይንቀሳቀሳሉ የተባሉ ታጣቂዎች ናይጄሪያ ድንበር አቅራቢያ በሚገኝ መንደር በፈጸሙት ጥቃት በትንሹ 20 ሰዎችን መግደላቸው ተሰምቷል። ጥቃቱ ባሳለፍነው እሁድ በደ/ምዕራብ የካሜሩን ክፍል ኦቦኒ ሁለት በተሰኘ መንደር የተፈፀመ ሲሆን ከሞቱ ሰዎች ባሻገር ከ60 በላይ ሰዎች ቆስለዋል። ታጣቂዎቹ ነዋሪዎቹ በየወሩ ገንዘብ እንዲከፍሏቸው ይፈልጋሉ፤ ነዋሪዎቹ ደግሞ ፍቃደኛ አልሆኑም። ለዚህም ነው ጥቃት ያደረሱባቸው ተብሏል።

➡️ #ሜክሲኮ ፦ በደቡባዊ ሜክሲኮ በተፈጠረ የመሬት መንሸራተትና የጎርፍ አደጋ በትንሹ 10 ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች የገቡበትን ማወቅ እንዳልተቻለ ተሰምቷል።

➡️ #ቻይና ፦ የሻንጋይ ነዋሪዎች ከሁለት ወር በኃላ የኮቪድ-19 የእንቅስቃሴ ገደብ መነሳቱን ተከትሎ ነፃ ሆነዋል። ነዋሪዎች ባለፉት 2 ወር ኮቪድ-19ኝን ለመከላከል በተጣለ የእንቅስቃሴ ገደብ ምክንያት ከእንቅስቃሴ ርቀው ቆይተዋል።

➡️ #ዩክሬን ፦ የየክሬን ኬርሰን ግዛት በሩስያ ቁጥጥር ውስጥ የሚገኝ ሲሆን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ሁሉንም የግንኙነት መስመሮች እንዲዘጉ ማድረጋቸው ተነግሯል።

➡️ #አሜሪካ ፦ የአሜሪካው ፕሬዜዳንት ጆ ባይደን ሀገራቸው ለዩክሬን 'ቁልፍ ኢላማዎችን' ለመምታት የሚያስችላትን እጅግ የዘመኑ ሮኬቶችን እንደምትልክ አሳውቀዋል።

➡️ #ሶማሊያ ፦ ወደ ባይዶዋ እንደሚሄዱ የተነገረላቸው አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ ፕሬዝዳንት ከሶማሊያ ደቡብ ምዕራብ ግዛት መሪ አብዲአዚዝ ሀሰን ሞሀመድ እና ከባህላዊ የሀገር ሽማግሌዎች ጋር ውይይት አካሂደዋል። ፕሬዜዳንቱ ወደ ባይዶዋ ያደረጉት ጉዞ ዳግም ፕሬዜዳንት ሆነው ከተመረጡ በኃላ የመጀመሪያቸው ነው።

#ቲአርቲ #ቢቢሲ #ፍራንስ24 #ሲጂቲኤን

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#US በየጊዜው በርካቶች በታጣቁ ሰዎች በሚከፈት ተኩስ የሚገደሉባት ሀገረ አሜሪካ ትላንትም እጅግ በጣም ዘግናኝ የሚባል ጥቃት ተፈፅሞ 2 አዋቂዎችን ጨምሮ 19 ሕጻናት ተገድለዋል። በአሜሪካ ቴክሳስ ግዛት አንድ የ18 ዓመት ወጣት በከፈተው የተኩስ እሩምታ 2 አዋቂዎችን ጨምሮ 19 ሕጻናት መገደላቸውን ተዘግቧል። ድርጊቱ የተፈፀመው በደቡብ ቴክሳስ ግዛት፣ ዩቫልዲ ከተማ ሮብ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት…
#አሜሪካ

በአሜሪካ ኦክላሆማ ግዛት ቱልሳ በተሰኘች ከተማ ሆስፒታል ውስጥ በተከፈተ ተኩስ አራት ሰዎች መገደላቸውን እና በርካቶች መቁሰላቸውን ፖሊስ ገልጿል።

ትኩስ እንደከፈተ የተጠረጠረው እና ጠመንጃ እና ሽጉጥ ታጥቆ የነበረው ግለሰብ መሞቱንም ፖሊስ አረጋግጧል።

ፖሊስ ጥቃቱ በተሰነዘረበት ቅዱስ ፍራንሲስ ሆስፒታል በሦስት ደቂቃ የደረሰ ሲሆን በጥቃቱ የሚጎዱ ሰዎችን ቁጥር ለመቀነስ በስፍራው በአስቸኳይ መድረሱ ተገልጿል።

ትላንት ረቡዕ በተፈጸመው በዚህ ጥቃት በርካቶች መቁሰላቸውንም ባለሥልጣናት አረጋግጠዋል።

የቱልሳ ከተማ ምክትል የፖሊስ ኃላፊ ኤሪክ ዳላግሊሽ " አሁን ላይ አራት ሲቪል ሰዎች የሞቱ ሲሆን፣ ጥቃት አድራሹም ሞቷል " ብለዋል።  

እስካሁን ማንነቱ ያልተለየው ጥቃት አድራሽ እራሱ ሳያጠፋ እንዳልቀረ ተገምቷል።

ተጠርጣሪው ሁለት መሳሪያዎችን ታጥቆ የነበረ ሲሆን " አንደኛው ረዝም ያለ፣ ሌላኛው ደግሞ የእጅ ሽጉጥ ነው በስፍራው የተገኘው " ብለዋል የፖሊስ ኃላፊው። 

#ቢቢሲ

@tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ ፦

#ሳዑዲ_አረቢያ ፦ ሳዑዲ አረቢያ የሃጅ ተጓዦችን እየተቀበለች ትገኛለች። ከቀናት በፊት የመጀመሪያው የሃጅ ተጓዦች ቡድን ከኢንዶኔዥያ ወደ ሳዑዲ መግባቱ ይታወሳል። ዛሬ ባገኘነው መረጃ እስከ ትላንት እሁድ ድረስ ከተለያዩ ሀገራት ለሃጅ ጉዞ ሳዑዲ የገቡ ተጓዦች 955 ደርሰዋል። ሳዑዲ አረቢያ ዘንድሮ ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ 1 ሚሊዮን የሃጅ ተጓዦችን እንደምታስተናግድ ይታወቃል።

#ጀርመን ፦ የጀርመኑ መኪና አምራች ኩባንያ መርሴዲስ-ቤንዝ 1 ሚሊዮን ገደማ አሮጌ መኪናዎችን ለጥገና ጠርቷል። ኩባንያው እኚህ መኪናዎች ፍሬናቸው ችግር አለባቸውና ጠግኜ ልመልስላችሁ ብሏል። ኩባንያው መኪኖቹ ከፍተኛ በሆነ ዝገት ምክንያት የፍሬን ሰርዓታቸው ተገቢውን ሥራ ላይሰራ ይችላል ብሏል። ጀርመን ያሉ 70 ሺህ መኪናዎችን ጨምሮ ከ993 ሺህ በላይ መኪናዎች መጠገን አለባቸው።

#UK ፦ ዩናይትድ ኪንግደም ለመጀመርያ ጊዜ ኤም 270 የተባሉ ረዥም ርቀት ተወንጫፊ ሚሳኤሎችን ለዩክሬን ልትሰጥ ነው። እነዚህን እጅግ ዘመናዊ ሮኬት ማስወንጨፍያ መሣሪያዎች መቼ እና በምን ያህል መጠን ወደ ዩክሬን እንደምትልክ አልገለጸችም።

#ሩስያ ፦ የሩስያ ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለአሜሪካ ማስጠንቀቂያ ልከዋል። ሀገሪቱ ለዩክሬን የጦር መሣሪያ ልገሳ እንድታቆም ያስጠነቀቁ ሲሆን ይህ የማይሆን ከሆነ ሩሲያ በዩክሬን የምታደርሰው ጥቃት መጠኑ እየሰፋ እንደሚመጣ ገልፀዋል። አሜሪካ ባለፈው ሳምንት ዘመናዊ ተወንጫፊ ሚሳኤል ሲስተምን ወደ ዩክሬን ልካለች። አሜሪካ መሣሪያውን ብትሰጥም ዩክሬን ይህን መሣሪያ ወደ ሩሲያ ግዛት እንዳትተኩስ አሳስባ ነው።

#ቢቢሲ #ሳዑዲጋዜቴ #ኤፒ

@tikvahethiopia
የጠ/ሚ ጽ/ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት ቢልለኔ ስዩም ምን አሉ ?

- መንግስት የሰሜኑ ጦርነት በሰላም ለመቋጨት በአፍሪካ ሕብረት ጥላ ስር ለሚደረገው ሂደት ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል።

- የሰላም ሂደቱ ውስብስብ እና ረጅም መሆኑን ገልፀዋል። “የትኛውም የሰላም ሂደት ረጅም ነው። ቀላል አይደለም። ውስብስብና የተደራረቡ ሁነቶችን የያዘ ነው” ብለዋል።

- ኢትዮጵያ የአፍሪካ ሕብረት አደራዳሪ ለሆኑት ኦባሳንጆ ትልቅ ቦታ እንዳላት ተናግረዋል።

- ከባለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ 2 ነጥብ 1 ቢሊየን ጥሬ ብር፣ 87 ሺ ሜትሪክ ቶን ምግብ እና ከ783 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ፣ 217 ሺህ ኪሎ ግራም በላይ የህክምና መድሃኒቶች እንዲሁም የመጠለያ ግብዓቶች ጨምሮ 130 ሺህ ኪሎ ግራም ምግብ ነክ ያልሆኑ የሰብዓዊ ድጋፎች ወደ ትግራይ ክልል ተልኳል ብለዋል።

- ህወሓት ቀጣይ የዝናብ ወቅት እየመጣ ባለበት በዚህ ወቅት ለሌላ ጦርነት እየተዘጋጀ መሆኑን ያሉ ሲሆን ህዝቡን በሃይል ለጦርነት እየመለመለ ነው ብለዋል። ድርጊቱ ቀጣዩን የእርሻ ስራ እንደሚያደናቅፍና በክልሉ ያለውን የሰብዓዊ ቀውስ እንደሚያባብስ ያደርጋል ብለዋል።

- በአፋር ክልል በግጭቱ ጉዳት ለደረሳበቸው ዜጎች 19 ሺ ሜትሪክ ቶን ምግብ ለአማራ ክልል ተፈናቃዮችም 244 ሺህ ሜትሪክ ቶን ምግብ መሰራጨቱን ገልፀዋል።

#ቢቢሲ #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #Ethiopia #Sudan " መረጃው ውሸት ነው " - ዶ/ር ለገሰ ቱሉ " በእግረኛ የሚመጡ ከሆነ የአካባቢው ታጣቂ በተጠንቀቅ ቆሟል " - አቶ አብራራው ተስፋ " ሱዳን ትሪቡን " የተባለው የሱዳን ሚዲያ የሱዳን ጦር ሰራዊት ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ኃይሎች ተወሰደብኝ ያለውን እርምጃ ለመበቀል የይገባኛል ጥያቄ በሚናሳበት የአልፋሽጋ አካባቢ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ስር የነበሩ " ካላ…
#Update

ከ1 ወር በፊት ተዘግቶ የነበረው የጋላባት ድንበር ተከፈተ።

ሱዳን ከ1 ወር በፊት ዘግታው የነበረውን እና ከኢትዮጵያ የሚያዋስናትን ቁልፍ የድንበር በረ ከፍታለች።

ሱዳን ድንበሩ የተከፈተው ከኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጋር ገንቢ የሆነ ውይይት ከተደረገ በኋላ ነው ብላለች።

ከአንድ ወር በፊት ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር በሚያወስነኝ አካባቢ በተፈጸመ ጥቃት የጦር አባላቶቼ ተገድለውበኛል ስትል ክስ ማሰማቷ ይታወሳል።

ሱዳን በኢትዮጵያ ጦር ሠራዊት ተፈጽሟል ባለችው ጥቃት 6 ወታደሮቿ እና አንድ ሲቪል መገደሉን ገልጻ ነበር።

የኢትዮጵያ መንግሥት/የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በሰዎች ህይወት መጥፋት ሀዘን እንደተሰማው ገልጾ ነገር ግን በሱዳን የተሰራጨው መረጃ ትክክል እንዳልነበር መግለፁ ይታወሳል።

በመጀመሪያ ደረጃ በቦታው በነበረው ግጭት የአገር መከላከያ ሠራዊት ተሳትፎ እንዳልነበረው የተገለፀ ሲሆን ጉዳቱ ያጋጠመው ደግሞ እራሳቸው የሱዳን ኃይሎች የኢትዮጵያን ድንበር ጥሠው አልፈው ከገቡ በኋላ ከአካባቢው ሚሊሻ ጋር በተደረገ ግጭት ነው።

አሁን የገላባት ድንበር በር እንዲከፈት የተወሰነው ድንበር ላይ ያጋጠመውን ችግር የሁለቱ አገራት መሪዎች ለመፍታት ከተስማሙ በኋላ መሆኑን ሱና የሱዳን ደኅንነት እና መከላከያ ምክር ቤት ቴክኒክ ኮሚቴን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

በድንበር አካባቢ የታጠቁ ኃይሎችን ለመቆጣጠር "በኢትዮጵያ በኩል የታየው በጎ ፍቃድ" የድንበር በሩ እንዲከፈት ምክንያት ከሆኑት መካከል አንዱ መሆኑ ተገልጿል።

ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና የሱዳኑ መሪ ሌ/ጄኔራል አብደል ፋታህ አል ቡርሐን ከሳምንታት በፊት ለኢጋድ ስብሰባ በኬንያ በተገኙበት ወቅት ስለሁለቱ ሀገራት እና ቀጠናዊ ጉዳዮች የጎንዮሽ ውይይት ማድረጋቸው አይዘነጋም። #ሱና #ቢቢሲ

@tikvahethiopia
የልጁን ህይወት አትርፎ ህይወቱ ያለፈው አባት !

የልጁን ሕይወት ለማዳን ከጀልባ ላይ የዘለለው እንግሊዛዊ አስክሬኑ ጣልያን ተገኘ።

ዛሬ ጥዋት ቢቢሲ በደረገፁ አንድ አሳዛኝ ክስተት አጋርቷል።

አረን ቻዳ የተባለ እንግሊዛዊ ልጁን ለመታደግ ከጀልባ ከዘለለ በኋላ ለሳምንታት ጠፍቶ አስክሬኑ ጣልያን ውስጥ ተገኝቷል።

አረን ባለፈው ወር " ጋርዳ " የተባለ ባሕር አካባቢ ከትዳር አጋሩና ከሁለት ልጆቹ ጋር እየተንሸራሸረ ነበር። ሽርሽሩ ተዘጋጅቶ የነበረው የአረንን 52ኛ ዓመት ልደት ለማክበር ነበር።

ቤተሰቡ ጀልባ ተከራይቶ በባሕር እየተጓዘ ሳለ  የአረን ልጅ " ሊሞን " የተባለ ሪዞርት አካባቢ ችግር ገጠመው። አባትም ልጁን ለማዳን ከጀልባው ከዘለለ በኋላ አስክሬኑ ከሊሞን በ800 ሜትር ርቀት፣ በ316 ሜትር ጥልቀት እንደተገኘ የነፍስ አድን ሰራተኞች ገልጸዋል።

#ልጁን_ካዳነ በኋላ ውሃ ውስጥ መስመጡት የተገለፀው አረን  " የሰመጠው አንዳች ሕመም ስላለበት ይመስለኛል " ሲል አንድ ነፍስ አዳን ሰራተኛ ገልጿል።

#ቢቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የልጁን ህይወት አትርፎ ህይወቱ ያለፈው አባት ! የልጁን ሕይወት ለማዳን ከጀልባ ላይ የዘለለው እንግሊዛዊ አስክሬኑ ጣልያን ተገኘ። ዛሬ ጥዋት ቢቢሲ በደረገፁ አንድ አሳዛኝ ክስተት አጋርቷል። አረን ቻዳ የተባለ እንግሊዛዊ ልጁን ለመታደግ ከጀልባ ከዘለለ በኋላ ለሳምንታት ጠፍቶ አስክሬኑ ጣልያን ውስጥ ተገኝቷል። አረን ባለፈው ወር " ጋርዳ " የተባለ ባሕር አካባቢ ከትዳር አጋሩና ከሁለት ልጆቹ ጋር…
የልጁን ህይወት አትርፎ ህይወቱ ያለፈው አባት !

የልጁን ህይወት ለማትረፍ ናይል ወንዝ የገባው አባት አስከሬኑ ተገኘ።

ስሙ ሮበርት ክዌሲ ይባላል የኡጋንዳ ተወላጅ ዜግነቱ ደግሞ እንግሊዛዊው ነው ፤ እድሜው 48 ሲሆን በእንግሊዝ ሀገር ነዋሪ ነበር።

ሮበርት ከባለቤቱ ጀስቲን ካታንታዚ እና ከአራት ልጆቻቸው ጋር ወደ ኡጋንዳ ለእረፍት ይመጣሉ። ኡጋንዳ መጥተው እየተዝናኑ ሳለ የ12 አመት ልጁ እየዋኘ በነበረበት ወቅት በነበረው ማዕበል ችግር ስላጋጠመው አባት ልጁን ለመርዳት ዘሎ ይገባል። ምንም እንኳን አባት ልጁን ቢያተርፍም የእሱ ደብዛ ግን ከዛች ደቂቃ አንስቶ ይጠፋል።

የነፍስ አድን ሰራተኞች እና ጠላቂ ፖሊስ አባላት እንዲሁም የአካባቢው በጎ ፍቃደኞች ካለፈው ረቡዕ ጀምሮ ፍለጋ ያደርጋሉ በኃላም የሮበርትን አስክሬን አግኝተዋል።

ሮበርት ክዌሲ አስክሬኑ የተገኘው በናይል ወንዝ በአንደኛው ክፍል ነው ተብሏል።

ሮበርት በእንግዚዝ ፍሪጅ እና አየር ማቀዝቀዣዎችን በመጠገን በተቋራጭነት ይሰራ ነበር። ከባለቤቱ ጋር ጋብቻቸውን የፈጸሙት ከጥቂት ሳምንታት በፊት በኡጋንዳ እንደነበር #ቢቢሲ ፅፏል።

ትላንትም አንድ እንግሊዛዊ አባት የልጁን ህይወት ለማትረፍ ሲል ከጀልባ ዘሎ ልጁን አትርፎ እሱ ግን ህይወቱ እንዳለፈ አስክሬኑም ጣልያን ውስጥ መገኘቱን የሚገልፅ መረጃ ማንበባችን ይታወሳል።

@tikvahethiopia
#Kenya

የኬንያ ፖሊስ 41 ኢትዮጵያውያንን ናይሮቢ ውስጥ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገለፀ።

ግለሰቦቹ ወደ ደቡብ አፍሪካና ሌሎች አገራት ለመዘዋወር በአንድ ቤት ውስጥ ለአራት ቀናት ያህል ሲጠባበቁ ሰኞ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም መያዛቸውን ገልጿል።

ኢትዮጵያውያኑን በሕገ ወጥ መንገድ ሊያዘዋውሩ ነበሩ የተባሉ ሁለት አዘዋዋሪዎችም በዚሁ አጋጣሚ የተያዙ ሲሆን አንደኛው #ኢትዮጵያዊ መሆኑም ፖሊስ አሳውቋል።

ፖሊስ ጥቆማ ደርሶት በቁጥጥር ሥር ያዋላቸው እነዚህ የሕገ ወጥ ሰዎች አዘዋዋሪዎች በአገሪቱ ውስጥ ካሉ ሌሎች በርካታ ዝውውሮች ጀርባ እንዳሉበት ተገልጿል።

ኢትዮጵያውያኑ በዚህ ሳምንት ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን ወደ ኬንያ እንዴት እንደገቡ ተጨማሪ ምርመራ እስኪደረግ ድረስ ለተጨማሪ ስድስት ቀናት በእስር እንዲቆዩ መታዘዙን #ቢቢሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#ቲክቶክ

ካናዳ ከዛሬ ጀምሮ መንግሥት በገዛው ‘ኤሌክትሮኒክስ’ ቁሳቁስ #ቲክቶክ መጠቀም ክልል መሆኑን አሳውቃለች።

በዚህ ሳምንት መንግሥት ገዝቶ ለሠራተኞች ካደላቸው ተንቀሳቃሽ ስልኮች ውስጥ ቲክቶክ ይጠፋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ፤ መተግበሪያው ለመረጃ ደኅንነት አስጊ እንደሆነ ጠቋሚ ፍንጮች ስላሉ ነው ውሳኔው የተላለፈው ብለዋል።

የቲክቶክ ቃለ አቀባይ በካናዳ መንግሥት ውሳኔ ኩባንያው እንደተከፋ ገልጠዋል።

ቲክቶክ ይህን ውሳኔ ተከትሎ ባወጣው መግለጫ የካናዳ መንግሥት ኩባንያውን ሳያማክር አሊያም በቂ ማስረጃ ሳይኖረው ይህን ማድረጉ አሳዛኝ መሆኑን ገልጧል።

* የአውሮፓ ኮሚሽን

ከቀናት በፊት የአውሮፓ ኮሚሽን ተመሳሳይ ውሳኔ አሳልፏል። የአውሮፓ ሕብረት ኮሚሽን ሠራተኞች ከመጋቢት 15 ጀምሮ ቲክቶክን በኮሚሽኑ ንብረት መጠቀም አይችሉም ሲል ነው ውሳኔ ያሳለፈው።

* አሜሪካ

ባለፈው የፈረጆቹ ዓመት የአሜሪካ የፌዴራሉ መንግሥት ሠራተኞች ቲክቶክን እንዳይጠቀሙ ተከልክለዋል።

ትላንት ዋይት ሐውስ የመንግሥት መ/ቤቶች በሚቀጥሉት 30 ቀናት ከኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎቻቸው ቲክቶክን #እንዲያስወግዱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

በርካታ የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲዎች መተግበሪያውን ከኔትዎርኮቻቸው ላይ አስወግደውታል።

* ሕንድ

ሕንድን ጨምሮ በሌሎች የእስያ ሃገራት የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች በቲክቶክ ላይ ተመሳሳይ እርምጃ እየወሰዱ ነው።

#ቲክቶክ

ቲክቶክ ባይትዳንስ የተሰኘው ኩባንያ ንብረት ነው።

መተግበሪያው ግላዊ መረጃን በመበዝበዝ ከፍተኛ ወቀሳ የሚደርስበት ሲሆን ከቻይና መንግሥት ጋር ግንኙነት አለው በሚልም ስሙ ይነሳል።

ኩባንያው የቻይና መንግሥት መረጃውን እንደማያገኝበትና ቻይና ያለው ቲክቶክ ከሌላው ዓለም ፈፅሞ የተለየ መሆኑን ደጋግሞ አሳውቋል።

#ቢቢሲ

@tikvahethiopia
" ምዕራባውያን እንግዳ የሆነ ባህል (የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት) እንድንፈቅድ #ማዕቀብ በመጣል ጫና ያሳድራሉ " - ፕሬዜዳንት ሙሴቬኒ

የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ምዕራባውያን አገራት የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎችን መብቶች በአፍሪካ አገራት ላይ በኃይል ለመጫን እየጣሩ ነው ሲሉ ወቅሰዋል።

ሙሴቬኒ ይህን ያሉት አገራቸው የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በተመለከተ አዲስ ሕግ እያረቀቀች ባለችበት ወቅት ነው።

የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ወንጀል በሆነባት ኡጋንዳ እየተረቀቀ ያለው ሕግ የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪዎች ላይ የበለጠ ጠንካራ ቅጣት የሚጥል ነው።

ፕሬዝዳንት ሙሴቬኒ ትናንት ሐሙስ መጋቢት 07/2015 ዓ.ም. በአገሪቱ ፓርላማ ቀርበው ይህን ብለዋል ፦

" ምዕራባውያን እንግዳ የሆነ ባህል (የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት) እንድንፈቅድ #ማዕቀብ በመጣል ጫና ያሳድራሉ።

ምዕራባውያን የራሳቸውን አሰራር በሌሎች ላይ ለመጫን የሚያባክኑትን ጊዜ ማቆም አለባቸው።

አውሮፓውያኑ የአጎት እና የአክስት ልጅ ጋር ትዳር ይመሰርታሉ እዚህ [ኡጋንዳ] የአንድ ጎሳ አባልን ማግባት ነውር ነው።

እነሱ የቅርብ ዘመድ እንዳያገቡ ማዕቀብ እንጣል ? ይህ የእኛ ሥራ አይደለም። "

ፕሬዜዳንት ሙሴቬኒ የተመሳሳይ ጾታ አፍቃሪያንን አፈንጋጭ ብለው የገለጿቸው ሲሆን በጉዳዩ ላይ ብዙ ምክክር መደረግ አለበት ብለዋል።

ኡጋንዳ አሁን ላይ እያረቀቀች ባለችው ሕግ መሠረት በተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት ውስጥ ያለ ወይም እራሱን የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነት አፍቃሪ ብሎ የሚገልጽ ሰው እስከ 10 ዓመታት የእስር ጊዜን እንዲያሳልፍ ያዛል።

የኡጋንዳ መንግሥት በአገሪቱ የሚንቀሳቀሱ የውጭ አገራት መንግሥታት ተቋማት እና ምዕራባውያን ኤጀንሲዎች የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን እያስተዋወቁ ነው በማለት ይከሳል።

#ቢቢሲ

@tikvahethiopia
" ትምህርት ቤቶቹን በመጪው ሚያዝያ ወር እንደገና ለመክፈት ዕቅድ ተይዟል " - UNICEF

በትግራይ በጦርነቱ ምክንያት ከሁለት ዓመታት በላይ ተዘግተው የነበሩ ትምህርት ቤቶችን እንደገና ለመክፈት ዕቅድ መውጣቱ ተገልጿል።

በትግራይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ከመራቃቸው ባለፈ መምህራንም ለሁለት ዓመታት ደመወዝ አልተከፈላቸውም።

ትምህርት ቤቶቹን በመጪው #ሚያዝያ_ወር እንደገና ለመክፈት ዕቅድ እንደተያዘም የዩኒሴፍ (UNICEF) የትምህርት ኃላፊ ቻንስ ብሪግስ ተናግረዋል።

ይህን ያሉት ለBBC Focus on Africa ሬዲዮ ነው።

" በትግራይ ሙሉ በሙሉ የትምህርት ሥርዓቱ ፈርሷል። " ያሉት ቻንስ ብሪግስ " ካለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ጀምሮ 2.3 ሚሊዮን ህጻናት ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው የሚያሳይ መረጃ አለን "  ብለዋል።

በመቐለ ከባለቤታቸው እና ከአራት ልጆቻቸው ጋር ነዋሪ የሆኑት አቶ መንግሥት ገብረመድኅን የእርስ በርስ ጦርነቱ በተቀሰቀሰበት ወቅት ሁለቱ ልጆቻቸው የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ይከታተሉ ነበር።

ትምህርት ከተቋረጠም በኋላ " እነሱን ለማስተማር ሞከርኩ፣ ነገር ግን መረጋጋት እና ትኩረታቸውን መሰብሰብ አልቻሉም " ብለዋል።

" የአየር ጥቃቶች እና የድሮን ጥቃቶች ድምጽ ይሰማሉ። ህጻናቱን ጠመንጃ ይዘው የሚሄዱ ወታደሮችንም ያያሉ። እነሱንም ለማስመሰል ይሞክራሉ። " ሲሉ የነበረውን ሁኔታ ገልጸዋል።

በመቐለ ዩንቨርስቲ ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት አቶ መንግሥት ለወራት ደመወዝ ሳይከፈላቸው መቆየቱን ተናግረዋል።

" ደመወዛችን አየተሰጠን ስላልነበር ልጆቻችን ምን እንደምንመግባቸው ያስጨንቀን ነበር። ስለዚህ እነሱን በማስተማር ላይ ማተኮር ፈታኝ ነበር። ነገር ግን ትናንትና ደመወዜን ተቀበልኩ፣ አሁን ለልጆቼም ልብስ እና ምግብ መግዛት እችላለሁ " ብለዋል።

በትግራይ በነበረው ጦርነት ከዛም በፊት በነበረው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሚሊዮኖች ተማሪዎች  ከትምህርት ገበታቸው ርቀዋል ፤ መምህራን ደግሞ በጦርነት ምክንያት ደሞዝ ሳይከፈላቸው ቆይቷል።

#ቢቢሲ #BBCFocusonAfrica

@tikvahethiopia
#ኬንያ

በጎረቤት ኬንያ በተቀሰቀሰ ተቃውሞ አንድ ሰው ተገደለ።

የኬንያ ተቃዋሚው ፖለቲከኛ ራይላ ኦዲንጋ የኑሮ መወደድን እና ፖለቲካዊ ጥያቄዎችን መሠረት አድርገው ደጋፊዎቻቸው ዛሬ ሰኞ መጋቢት 11/2015 ዓ.ም. ለተቃውሞ አደባባይ እንዲወጡ ጠርተው ነበር።

የኬንያ መንግሥት የተቃውሞ ሰልፉ ሕገወጥ እና ያልተፈቀደ ነው ቢልም፣ በተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች ውስጥ በአንስተኛ ደረጃ ወደ ጎዳና የወጡ ተቃዋሚዎች ታይተዋል።

ፖሊስም ተቃዋሚዎችን ለመበተን ከፍተኛ ኃይል ያለው ውሃ እና አስለቃሽ ጋዝ የተጠቀመ ሲሆን፣ እስካሁን አንድ ሰው ከፖሊስ በተተኮሰ ጥይት መሞቱ ተዘግቧል።

የተቃዋሚ ፓርቲው መሪ ራይላ ኦዲንጋ ምንም እንኳን ፍርድ ቤት ክሳቸውን ውድቅ ቢያደርገውም ባለፈው ዓመት ነሐሴ የተካሄደው ምርጫ ተሰርቋል የሚለውን ክሳቸውን አሁንም እያቀረቡ ነው።

በተጨማሪም ሥልጣን ከያዘ ስድስት ወራትን ያስቆጠረው የዊሊያም ሩቶ መንግሥት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ ያለውን የኑሮ ውድነት መፍትሄ ሊያበጅለት አልቻለም በማለት ደጋፊዎቻቸውን ለአደባባይ ተቃውሞ ጠርተዋል።

በተለይ ኦዲንጋ ከፍተኛ ደጋፊ ባላቸው የናይሮቢ የድሆች መኖሪያ በሆነው ኪቤራ አካባቢ ፖሊሶች ከተቃዋሚዎች ጋር ተጋጭተዋል።

በማዕከላዊ ናይሮቢ የሚገኙ የንግድ ተቋማትም የፀጥታ ችግሩን በመፍራት ዝግ ሆነው አስከ እኩለ ቀን ድረስ የቆዩ ሲሆን፣ ፖሊስ ለተቃውሞ የወጡ ሰልፈኞችን በአስለቃሽ ጋዝ በትነዋል።

በማዕከላዊ የከተማዋ ክፍል ውስጥ በሚገኘው የኬንያታ ጎዳና ላይም አንዳንድ ተቃዋሚዎች በፖሊሶች ላይ ድንጋይ ሲወረውሩ መታየታቸውን #ቢቢሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
የIMF ሰዎች እዚህ ኢትዮጵያ ናቸው።

ብሉምበርግ የዜና ወኪል ፤ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ለኢትዮጵያ ሊሰጥ በሚችለው ድጋፍ አስፈላጊውን ዝግጅት ለማድረግ የድርጅቱ ባለሥልጣናት አዲስ አበባ ይገኛሉ ብሏል።

በእርስ በርስ ጦርነቱ ሳቢያ ኢትዮጵያ ከIMF ጨምሮ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ጋር የነበራት ግንኙነት ተቀዛቅዞ መቆየቱ ይታወሳል።

እንደ ብሉምበርግ ዘገባ የተቋሙ የባለሙያዎች ቡድን ኢትዮጵያ ከIMF ሊደረግላት ስለሚችለው ድጋፍ አስፈላጊውን “ቴክኒካዊ ሥራ ለማከናወን” ነው አዲስ አበባ የሚገኘው።

ለኢትዮጵያ የሚያደርገውን ድጋፍ በተመለከተ ውይይት እና አስፈላጊውን ሁኔታ እንዲያመቻቹ የተላኩት የIMF ባለሥልጣናት ለ10 ቀናት ያህል ይቆያሉ።

ቃላቸውን ለሮይተር የዜና ወኪል የሰጡ የIMF ቃል አቀባይ በበኩላቸው ፤ ኢትዮጵያ ለምታካሂደው ምጣኔ ሀብታዊ ለውጥ የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግላት ተቋሙን እንደጠየቀች ተናግረዋል።

ቃል አቀባዩ ፤ " ሊሰጥ የሚችለው ድጋፍ አገሪቱ ለምታካሂደው አገር በቀል የምጣኔ ሀብት ማሻሻያ እና ምጣኔ ሀብቷን በማረጋጋት ለሰብአዊ ድጋፍ፣ ለሥራ ፈጠራ እና ለድህነት ቅነሳ የሚውል ይሆናል " ብለዋል።

የIMF ባለሥልጣናት በዚህ ሳምንት አዲስ አበባ ውስጥ የሚያደርጉት ቴክኒካዊ ውይይት ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ባለሥልጣናት እና በተቋሙ መካከል ሰብአዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ ችግሮችን ለማሻሻል የተደረገ ንግግር ተከታይ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም መካከል ሲካሄድ የነበረው የድጋፍ፣ የብድር ስረዛ እና ሽግሽግ ንግግር በከፊል በትግራይ ሲካሄድ ከነበረው ጦርነት ጋር ተያይዞ ምላሽ ሳያገኝ ቆይቶ ነበር።

ብሉምበርግ እንደዘገበው ኢትዮጵያ ጦርነቱ ያስከተለውን ውድመት መልሶ ለመገንባትና የገጠማትን የውጭ ምንዛሪ እጥረት በመሸፈን አስፈላጊ ለሆኑ የገቢ ምርቶች ክፍያ ለመፈጸም ድጋፍ ያስፈልጋታል።

ጦርነቱ ካስከተለው ሰብአዊ እና ቁሳዊ ውድመት ባሻገር በአፍሪካ ካሉ የመዋዕለ ነዋይ አፍሳሾች መዳረሻ ከሆኑ አገራት መካከል አንዷ በሆነችው ኢትዮጵያ ላይ ተጽእኖ ማሳደሩን እና ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ በተፈጸሙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች የተነሳ ከዓለም ባንክ (World Bank) አንዲሁም ከIMF የምታገኘውን ድጋፍ ገትቶት መቆየቱን አስታውሷል።

በጦርነቱ እና በዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎች ምክንያት ኢትዮጵያ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ችግር የገጠማት ሲሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት ከፍተኛ የሸቀጦች ዋጋ ጭማሪ ከመመዝገቡ በላይ እጥረትም ተከስቷል።

#ቢቢሲ #ብሉምበርግ #ሮይተርስ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" በሚዲያ ጥፋት የተጠረጠሩ ታሳሪዎች በሙሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከእስር ሊለቀቁ ይገባል " - ኢሰመኮ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የፖለቲካ ፓርቲዎች መሪዎችንና አባላትን፣ የሚዲያ አባላትንና የማኅበረሰብ አንቂዎችን ዒላማ ያደረገ እስር እና ወከባ በእጅጉ አሳሳቢ መሆኑን ገልጿል። ኢሰመኮ በተለያየ ዓይነት ወንጀል ተጠርጥረው በፖሊስ ከተያዙ ሰዎች ውስጥ በተለይ የሚዲያ አባላትን፣ የተቃዋሚ…
" የዜጎች መብት በፍትሕ አካላት በተደጋጋሚ እየተጣሰ ነው " - የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ምክር ቤት

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ም/ ቤት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ጋዜጠኞች ከሕግ አግባብ ውጪ ታፍነው እየታሰሩ እና የመገናኛ ብዙሃን ተቋማት ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ብርበራ እየተካሄደባቸው መሆኑን ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።

ምክር ቤቱ ፤ በሚዲያ አማካኝነት ተፈጽሟል በተባለ ወንጀል ተጠርጣሪ የሆኑ ጋዜጠኞች በፖሊስ ሲያዙም ሆነ ፍርድ ቤት ሲቀርቡ በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ባለመሆኑ ባለሙያዎች ስራቸውን በነጻነት እንዳይሰሩ ከማድረጉ በላይ የፕሬስ ምህዳሩ እንዲጠብ እያደረገው ነው ሲል ገልጿል።

በሚዲያ አማካይነት የወንጀል ድርጊት በመፈፀም የተጠረጠረ በወንጀል ሥነ-ሥርዓት የሕግ ድንጋጌዎች መሠረት ለተጨማሪ ምርመራ በእስር እንዲቆይ ሳይደረግ ክሱ በቀጥታ በዓቃቤ ሕግ አማካኝነት ለፍርድ ቤት መቅረብ እንዳለበት ምክር ቤቱ አዋጅ ቁጥር 1238/13 ጠቅሶ አስታውሷል።

ይሁን እንጂ ጋዜጠኞች እንደ ማንኛውም ተከሳሽ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተጠይቆባቸው ለፖሊስ በመፍቀድ እንዲታሰሩ ማድረግ በምንም መለኪያ ተቀባይነት የለውም ብሏል።

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ም/ቤት የዜጎች መብት በፍትሕ አካላት በተደጋጋሚ እየተጣሰ ነው ያለ ሲሆን ከሕግ አግባብ ውጪ የታሰሩ ጋዜጠኞች እንዲፈቱ ጠይቋል።

መንግሥት መንግሥታዊ ኃላፊነቱን ሲወጣ ተግባሩ ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ መብትን በማያጠብና የዜጎችን የዴሞክራሲያዊ ስርዓት ተሳትፎ በማያቀጭጭ መልኩ ሊሆን ይገባልም ብሏል።

የፍትሕ ሥርዓቱ በመገናኛ ብዙሃን አዋጁ ድንጋጌ ብቻ በመመራት ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታውን እንዲወጣ ምክር ቤቱ ጠይቋል። #ቢቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ የፀጥታ እና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል ፥ ከሀገር ውጭ የሚገኙትን ፖለቲከኛው አቶ ልደቱ አያሌውን ፣ በቅርቡ ከልዩ ኃይል ጋር በተያያዘ በአማራ ክልል የተፈጠረውን አለመግባባት በስምምነት እንደፈታ የተነገረለት የምስራቅ አማራ ፋኖ አመራር ምሬ ወዳጆን ጨምሮ በሀገር ውስጥ በተደጋጋሚ ጊዜ በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩ የሚዲያ ሰዎች እና በውጭ ሀገር ያሉ በርካታ የሚዲያ ሰዎችን " ህገ መንግስታዊ…
" ክስ ከተመሰረተብኝ እመለሳለሁ " - አቶ ልደቱ አያሌው

መንግሥት በ "ሽብር ወንጀል እጠረጥራቸዋል" ያላቸውን በውጭ ሀገር ያሉና ተላልፈው እንዲሰጡ ማዘዣ ካወጣባቸው ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆኑት ጉምቱው ፖለቲከኛ አቶ ልደቱ አያሌው "ክስ ከተመሠረተባቸው" ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመለሱ አሳውቀዋል።

አቶ ልደቱ እስካሁን ክስ እንዳልተመሠረተባቸው በጠበቃቸው እንደተነገራቸውና ክስ ከተመሠረተባቸው ግን ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመመለሱ ገልጸዋል።

ይህን የገለፁት ከቢቢሲ አማርኛ ጋር በነበራቸው ቃለምልልስ ነው።

ፖለቲከኛው አቶ ልደቱ አያሌው ምን አሉ ?

"...ከጠበቃዬ ጋር እየተነጋገርኩ ነው። እስካሁን ክስ አልተመሠረተብኝም። ዝም ብሎ በራድዮና በቴሌቪዥን ይነገራል እንጂ የቀረበ ክስ የለም። ክስ ሲመሠረት ነው የምሄደው።

ክስ ከመመሥረቱ በፊት መሄዴ ጥቅም የለውም። በጊዜ ቀጠሮ መጉላላት ነው እንጂ ምንም ፋይዳ የለውም። እስከዚያ ድረስ ሕክምናዬን እከታተላለሁ /አቶ ልደቱ ለልብ ህመም በአሜሪካ የህክምና ክትትል ላይ ናቸው/ ።

ክስ ሲመሠረት ዳኞቹ የሚቀጥለው ሕክምናዬ ድረስ እንድቆይ የሚፈቅዱ ከሆነ እቆያለሁ። የማይፈቅዱ ከሆነም የሕክምና ቀጠሮዬን አቋርጬ እሄዳለሁ። "

አቶ ልደቱ ስለ ሽብር ክስ...

" የሕክምና ቀጠሮ ስለነበረኝ ነው እንጂ መጀመሪያም የመጣሁት እዚህ ለመኖር አይደለም። በቅርብ ጊዜ ወደ አገሬ እመለሳለሁ ብዬ እያሰብኩ ነበር። የዘገየሁት ያልተቋጨ የሕክምና ቀጠሮ ስለነበረኝ ነው። የሽብርተኛነት ክስ ሲመጣ ካሰብኩት ጊዜ ፈጥኜ ነው የምሄደው አልኩ።

የሕግ ተፈላጊነት ካለ፣በሽብርተኛነት የመጠየቅ ጉዳይ ካለ፣እኔ ከፍ/ቤት ውሳኔ እና ጥያቄ ርቄ መኖር ስለማልፈልግ ነው ለመሄድ የወሰንኩት።

...አገሪቱ ካለችበት ሁኔታ አንጻር ተመልሼ ለመውጣት ችግር ሊገጥም ይችላል ብዬ ነው እስካሁን የዘገየሁት። አሁንም የሕክምና ቀጠሮ አለኝ። ግን የሕግ ተጠያቂነት ከመጣ ምንም ማድረግ አይቻልም።

የተከሰስኩበት ወንጀል በፍጹም ከእኔ ታሪክ እና ማንነት ጋር የማይሄድ ነው። ሥርዓቱ ደግሞ ይሄንን ያደረገበት የራሱ ምክንያት አለው። አንደኛው ምክንያት እንደዚህ ዓይነት ክስ ፈርቼ ወደ አገሬ እንዳልመለስ ለማድረግ ስለሆነ ይሄንን በፈቃደኛነት ለመቀበል ዝግጁ አይደለሁም።

እኔ ሰላማዊ ታጋይ ነኝ። ሁልጊዜም በሕግ ነው የምተማመነው። ካሁን ቀደምም አምስት ስድስቴ ታስሬ በፍርድ ቤት ነው ነጻ የሆንኩት። አሁንም በዚያ መንገድ ሄጄ የግድ ሥርዓቱን መጋፈጥ አለብኝ በሚል ነው የምመለሰው።

ማናችንም ላለመታሰር፣ ዋጋ ላለመክፈል የየራሳችን ምክንያት ይኖረናል። ትግል ሲባል ግን እነዚህን ሁሉ ነገሮች ጥሶ መከፈል የሚገባውን ዋጋ መክፈል ነው።

ወደኢትዮጵያ ሲገቡ ስለሚገጥማቸው ችግር...

" ስሄድ የሚገጥመኝ ችግር ቀላል ነው ብዬ አይደለም። ከባድ እንደሚሆን አምናለሁ። ያ ችግር ምናልባት ሕይወቴንም ጭምር የሚያሳጣ ሊሆን ይችላል።

ግን ኢትዮጵያ ያለችበት ሁኔታ፣ ሕዝቡ ያለበት ሁኔታ፣ ሰዎች በዚህ ደረጃ ዋጋ ለመክፈል ካልተዘጋጀንና ካልከፈልን ይለወጣል የሚል እምነት የለኝም። በእኔ ደረጃ ያለ ሰው ያን ዋጋ መክፈል እና ለትግሉ አርአያ መሆን አለበት ብዬ አምናለሁ።

ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ በፖሊስ ሊያዙ ስለሚችሉበት ሁኔታ...

" ልምዱ አለኝ። መታሰር የመጀመሪያዬ አይደለም። በዚህ ዓይነት ትግል ውስጥ ላለፉት 31 ዓመታት ቆይቻለሁ። ወደ 6 ጊዜ ስለታሰርኩ ለእኔ አዲስ ነገር አይደለም።

ከእኔ ጋር በመግለጫ የተጠቀሱ ግለሰቦች እየታደኑ እያተሰሩ እንደሆነ አውቃለሁ፤ ኤርፖርት የሚጠብቀኝ ፖሊስ እንደሚሆንና እንደምታሰር አውቃለሁ። ለዚህ የሥነ ልቦና ዝግጅት አለኝ።"

#ቢቢሲ

@tikvahethiopia
#ነዳጅ

ሳዑዲ አረቢያ ከነዳጅ ምርቷ በቀን 1 ሚሊዮን በርሜል እቀንሳለሁ ማለቷን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ መጨመሩ ተነገረ።

ሌሎች የዓለማችን ነዳጃ አምራች አገራትም በተመሳሳይ የነዳጅን ዋጋን ለማረጋጋት በማሰብ የምርት አቅርቦታቸውን ለመቀነስ ተስማምተዋል ተብሏል።

ሳዑዲ አረቢያ በቀጣዩ ሀምሌ ወር በየቀኑ 1 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ ከምርት አቅርቦቷ ላይ እንደምትቀነስ የገለጸች ሲሆን የነዳጅ ላኪዎች ሀገራት ማህበር ወይም ኦፔክ+ እንደ አውሮፓውያኑ በ2024 ዕለታዊ የነዳጅ አቅርቦት በ1.4 ሚሊዮን በርሜል እንደሚቀንስ ገልጿል።

ኦፔክ+ የዓለምን 40 በመቶ የነዳጅ ፍላጎት የሚያሟላ ሲሆን ውሳኔው በዓለም የነዳጅ ምርት ዋጋ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ ሊያሳድር ይችላል።

የሳዑዲን ውሳኔ ተከትሎ በእስያ ገበያ የደፍድፍ ነዳጅ ዋጋ በ 2.4 በመቶ አሻቅቦ በበርሜል 77 ዶላር ሆኗል።

የሳዑዲ ኢነርጂ ሚንስትር ልዑል አብዱላዚዝ ቢን ሰልማን ፤ የነዳጅ ምርት አቅቦቱን የመቀነሱ ውሳኔ አስፈላጊ ከሆነ ከሃምሌም በኃላ #ሊራዘም ይችላል ብለዋል። ውሳኔው የዓለም የነዳጅ ዋጋን እንደሚያረጋጋ ገልጸዋል።

#ቢቢሲ

@tikvahethiopia
" ሁላችሁም የውጭ አገራት ጣልቃ እንዳትገቡ " - ኮሎኔል ሜጀር አማዱ

በአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት መፈንቅለ መንግሥት ሲደረግ በተደጋጋሚ ተሰምቷል።

አሁን ደግሞ በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ኒጀር #ወታደሮች መፈንቅለ መንግሥት አውጀዋል።

ወታደሮሹ ሕገ-መንግሥቱን መበተናቸውን፤ ሁሉም የመንግሥት ተቋማት ለጊዜው ሥራ ማቆማቸውን እና የሃገሪቱ ድንበሮች መዘጋታቸውን ይፋ አድርገዋል።

ከረቡዕ ጀምሮ የኒጀር ፕሬዝደንት ሞሐመድ ባዙም በወታደሮች ቁጥጥር ሥር እንዳሉ ተነግሯል።

ተመድ እንዲሁም አሜሪካ ለፕሬዝደንቱ ድጋፍ እንደሚያደርጉ አሳውቀዋል።

ረቡዕ ዕለት ዘጠኝ የወታደር መለዮ በለበሱ ሰዎች ተከበው በቴሌቪዥን መስኮት መግለጫ የሰጡት ኮሎኔል ሜጀር አማዱ አብድራማኔ ፤ " እኛ የመከላከያና የፀጥታ ኃይሎች የምታውቁት መንግሥት ከሥልጣን አውርደናል " ብለዋል።

የሃገሪቱ ሁሉም ተቋማት ለጊዜ ሥራ እንደሚያቆሙ የገለጹት ኮሎኔሉ ሚኒስትሮች የቀን ተቀን ሥራውን እንደሚመሩ ገልጠዋል።

" ሁሉም የውጭ አገራት ጣልቃ እንዳይገቡ እንጠይቃለን። ሁኔታዎች እስኪረጋጉ በምድርም ሆነ በአየር ድንበራችንን ዘግተናል " ብለዋል።

አክለው ላልተወሰነ ጊዜ ከምሽት 4 ሰዓት እስከ ንጋት 11 የሚቆይ ሰዓት እላፊ መታወጁንም ማሳወቃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

የኒጀር ጎረቤት የሆኑት ማሊ እና ቡርኪና ፋሶ በቅርብ ዓመታት በተመሳሳይ በመፈንቅለ መንግሥት ምክንያት ታምሰው እንደነበር አይዘነጋም። #ቢቢሲ

@tikvahethiopia