TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#US #Uk

አሜሪካ እና ዩናይትድ ኪንግደም በዩክሬን ሰማይ ላይ የበረራ ክልከላ መጣልን እንደማይደግፉት በድጋሚ ገልፀዋል።

ሀገራቱ ከሩሲያ ጋር በቀጥታ ወታደራዊ ግጭት እንዲፈጠር አንፈልግም ብለዋል።

ይህን አቋማቸውን ዳግም ያንፀባረቁት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮቻቸው በዋሽንግቶን ዲሲ ተገናኝተው ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው።

የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን የባይደን አስተዳደር ዓላማው ግጭቱ እንዲቆም እንጂ እንዲሰፋ አይደለም ሲሉ ተደምጠዋል።

ብሊንከን የአሜሪካ ፓይለቶችን ወደዩክሬን አየር ክልል ማስገባት በአሜሪካ/NATO እና ሩስያ መካከል ቀጥተኛ ግጭት ይፈጥራል ብለዋል። "ይህ ደግሞ ግጭቱን ያሰፋዋል፣ ያራዝመዋል፤ አሁን ካለውም በላይ ገዳይ ያደርገዋል። ይህ ደግሞ የሀገሮቻችንም ሆነ የዩክሬን ፍላጎት አይደለም " ሲሉ አስረድተዋል።

የዩኬ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኤልዛቤት ትሩስ በዩክሬን ሰማይ የበረራ ክልከላ ተግባራዊ እንዲሆን የሚደረገውን ግፊት ውድቅ አድርገዋል። ሚኒስትሯ ውድቅ ያደረጉት የሰብዓዊ መተላለፊያን ለመጠበቅ የተወሰነም ቢሆን ክልከላ ማድረግን ጭምር ነው።

የበረራ ክልከላ ማድረግ በሩስያና NATO መካከል ቀጥተኛ ግጭት እንዲፈጠር ያደርጋል ያሉት ትሩስ፤ "እኛ እየተመለከትን ያለነው ያንን አይደለም፤ እየተመለከትን ያለነው ዩክሬናውያን በተቻለ መጠን በፀረ-ታንክ የጦር መሣሪያዎች እና በአየር መከላከያ ዘዴዎች ሀገራቸውን መከላከል መቻላቸውን ማረጋገጥ ነው" ብለዋል።

ይኸው የአሜሪካና ዩኬ አቋም የተንፀባረቀው የዩክሬኑ ፕሬዜዳንት ቮድሚር ዜሌንስኪ ምዕራባውያኑ የዩክሬን የአየር ክልል ላይ የበረራ ክልከላ እንዲጥሉ እየተማፀኑ ባሉበት ወቅት ነው።

ሩስያ ምዕራባውያን እንዲህ ያለውን ነገር እንዳያስቡት ማስጠንቀቋ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም ውሳኔ አሳለፈ። መንግስት ባወጣው መግለጫ ፤ በአሁኑ ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ክልል ነዋሪዎች የሰብዓዊ እርዳታን ፍለጋ ወደአጎራባች ክልሎች እየተጓዙ መሆኑን አመልክቷል። እነዚህ ዜጎች የሰብዓዊ እርዳታው ከቀያቸው ሳፈናቀሉ ባሉበት እንዲርሳቸው ቢደረግ እንግልታቸውን እንደሚቀንስ በጽኑ እንደሚያምን አሳውቋል። በመሆኑም በከፍተኛ…
#UK

ዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ መንግሥት ያሳለፈውን ውሳኔ በደስታ እንደምትቀበል እና መንግስት የሰብዓዊ ድጋፍ ፍላጎት ምላሹን ለማሳደግ የሚያደርገውን ጥረት ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን አስታውቃለች።

ዩናይትድ ኪንግደም ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት አዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲዋ ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም መወሰኑን እና ያልተገደበ ሰብዓዊ እርዳታ ወደ ትግራይ እንዲደርስ ያሳለፈውን ውሳኔ በደስታ እንደምትቀበል ገልፃለች።

የትግራይ ባለሥልጣናትም ምላሽ እንዲሰጡ ጠይቃለች።

ዩናይትድ ኪንግደም ፤ መንግስት የሰብዓዊ ድጋፍ ፍላጎት ምላሹን ለማሳደግ የሚያደርገውን ጥረት ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን አስታውቃለች።

የኢትዮጵያ መንግስት ዛሬ ከሰዓት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ማቆሙን ማብሰሩ እና ዓለም አቀፍ ለጋሾች እያቀረቡ ያለውን ድጋፍ እና እርዳታ #በከፍተኛ_መጠን_እንዲጨምሩ ጥሪ ማቅረቡ ይታወቃል።

እስካሁን በትግራይ ክልል በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም።

@tikvahethiopia
#UK

ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ መጥተው ስለሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት እና ስለወቅታዊ የኢትዮጵያ ሁኔታ ላይ ከከፍተኛ የሀገሪቱ ባለሰልጣናት ጋር ውይይት አድርገው የነበሩት የዩናይትድ ኪንግደም የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ቪኪ ፎርድ ፤ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም እና ያልተገደበ የሰብዓዊ ድጋፍ ወደ ትግራይ እንዲደርስ ለማድረግ ያሳየውን ቁርጠኝነት አጥብቀው እንደሚደግፉ አሳውቀዋል።

ቪኪ ፎርድ ፥ የትግራይ ባለስልጣናት ተኩስ በማቆም እና ከአፋር በመውጣት ምላሽ መስጠት አለባቸው ብለዋል።

የታየው ቁርጠኝነት በተግባር ሰብዓዊ እርዳታ ወደመላክ መተርጎም አለበት ያሉት ሚኒስትሯ ይህንንም የዩናይትድ ኪንግደም መንግሥት ለመደገፍ ዝግጁ ነው ሲሉ አብስረዋል።

ህወሓት ባወጣው መግለጫ የሰብዓዊ እርዳታ ትግራይ የሚደርስ ከሆነ ግጭት ለማቆም ዝግጁ መሆኑን የገለፀ ሲሆን ከያዛቸው የአጎራባች ክልል አካባቢዎች ለቆ ስለመውጣት ያለው ነገር የለም።

@tikvahethiopia
#UK

አሜሪካ #በጥብቅ የምትፈልገው የ " ዊኪሊክስ " መስራች ጁሊያን አሳንጅ ለአሜሪካ ተላፎ እንዲሰጥ የብሪታኒያ ፍርድ ቤት ዛሬ ወስኗል።

አሳንጅ ለአሜሪካ ፍርድ ቤት ተላልፎ እንዲሰጥ ፍርድ ቤቱ ያሳለፈው ውሳኔ ተፈጻሚ የሚሆነው የብሪታኒያ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ሲያጸድቀው ነው ተብሏል።

አሳንጅ የአሜሪካን ወታደራዊ መረጃዎች አውጥቷል ፤ አትሟል ፤ ወታደራዊ ሚስጥሮችን የያዙ ሰነዶች ለውጭ ኃይሎች አሳለፎ ሰጥቷል በሚል እና በሌሎችም ጉዳዮች ነው አሜሪካ የምትፈልገው።

18 በሚሆኑ ክሶችም ዋና ተፈላጊ ሰው ነው።

የ50 ዓመቱ አሳንጅ በአሜሪካ የቀረበለትን ክስ ውድቅ ቢያደረግም፤ አድርጎታል ከተባለ ድርጊት ጋር በተያያዘ ለ7 ዓመታት በለንደን በሚገኘው የኢኳዶር ኤምባሲ፤ እንዲሁም እንደፈረንጆቹ ከ2019 አንስቶ አስካሁን ድረስ በደቡብ ምስራቅ ለንደን በሚገኘው ቤልማርሽ እስር ቤት እንዲታሰር አድርጎታል።

መረጃው የአል ዓይን ኒውስ ነው።

@tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ ፦

#ሳዑዲ_አረቢያ ፦ ሳዑዲ አረቢያ የሃጅ ተጓዦችን እየተቀበለች ትገኛለች። ከቀናት በፊት የመጀመሪያው የሃጅ ተጓዦች ቡድን ከኢንዶኔዥያ ወደ ሳዑዲ መግባቱ ይታወሳል። ዛሬ ባገኘነው መረጃ እስከ ትላንት እሁድ ድረስ ከተለያዩ ሀገራት ለሃጅ ጉዞ ሳዑዲ የገቡ ተጓዦች 955 ደርሰዋል። ሳዑዲ አረቢያ ዘንድሮ ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ 1 ሚሊዮን የሃጅ ተጓዦችን እንደምታስተናግድ ይታወቃል።

#ጀርመን ፦ የጀርመኑ መኪና አምራች ኩባንያ መርሴዲስ-ቤንዝ 1 ሚሊዮን ገደማ አሮጌ መኪናዎችን ለጥገና ጠርቷል። ኩባንያው እኚህ መኪናዎች ፍሬናቸው ችግር አለባቸውና ጠግኜ ልመልስላችሁ ብሏል። ኩባንያው መኪኖቹ ከፍተኛ በሆነ ዝገት ምክንያት የፍሬን ሰርዓታቸው ተገቢውን ሥራ ላይሰራ ይችላል ብሏል። ጀርመን ያሉ 70 ሺህ መኪናዎችን ጨምሮ ከ993 ሺህ በላይ መኪናዎች መጠገን አለባቸው።

#UK ፦ ዩናይትድ ኪንግደም ለመጀመርያ ጊዜ ኤም 270 የተባሉ ረዥም ርቀት ተወንጫፊ ሚሳኤሎችን ለዩክሬን ልትሰጥ ነው። እነዚህን እጅግ ዘመናዊ ሮኬት ማስወንጨፍያ መሣሪያዎች መቼ እና በምን ያህል መጠን ወደ ዩክሬን እንደምትልክ አልገለጸችም።

#ሩስያ ፦ የሩስያ ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለአሜሪካ ማስጠንቀቂያ ልከዋል። ሀገሪቱ ለዩክሬን የጦር መሣሪያ ልገሳ እንድታቆም ያስጠነቀቁ ሲሆን ይህ የማይሆን ከሆነ ሩሲያ በዩክሬን የምታደርሰው ጥቃት መጠኑ እየሰፋ እንደሚመጣ ገልፀዋል። አሜሪካ ባለፈው ሳምንት ዘመናዊ ተወንጫፊ ሚሳኤል ሲስተምን ወደ ዩክሬን ልካለች። አሜሪካ መሣሪያውን ብትሰጥም ዩክሬን ይህን መሣሪያ ወደ ሩሲያ ግዛት እንዳትተኩስ አሳስባ ነው።

#ቢቢሲ #ሳዑዲጋዜቴ #ኤፒ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UK አሜሪካ #በጥብቅ የምትፈልገው የ " ዊኪሊክስ " መስራች ጁሊያን አሳንጅ ለአሜሪካ ተላፎ እንዲሰጥ የብሪታኒያ ፍርድ ቤት ዛሬ ወስኗል። አሳንጅ ለአሜሪካ ፍርድ ቤት ተላልፎ እንዲሰጥ ፍርድ ቤቱ ያሳለፈው ውሳኔ ተፈጻሚ የሚሆነው የብሪታኒያ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ሲያጸድቀው ነው ተብሏል። አሳንጅ የአሜሪካን ወታደራዊ መረጃዎች አውጥቷል ፤ አትሟል ፤ ወታደራዊ ሚስጥሮችን የያዙ ሰነዶች ለውጭ ኃይሎች…
#UK #USA

አሜሪካ በጥብቅ የምትፈልገው ጁሊያን አሳንጅ ተላልፎ ሊሰጥ ይችላል ተብሏን።

የዊክሊክስ መስራች ጁሊያን አሳንጄ ለአሜሪካ ተላልፎ የመሰጠቱ ጉዳይ በUK የሃገር ውስጥ ሚኒስትር ፕሪቲ ፓቴል ተቀባይነት እንዳገኘ ቢቢሲ ዘግቧል።

ጁሊያን አሳንጄ ውሳኔውን ይግባኝ ለማለት 14 ቀናት እንዳለውም የዩናይትድ ኪንግደም ሃገር ውስጥ ፅህፈት ቤት አስታውቋል።

ፍርድ ቤቶች ጁሊያን አሳንጄን አሳልፎ የመስጠት ጉዳይ " ከሰብዓዊ መብቱ ጋር የማይጣጣም " መሆኑን ቢገነዘቡም በአሜሪካ ውስጥ " በተገቢው ሁኔታ እንደሚስተናገድ " ማረጋገጣቸውን ገልጿል።

ጁሊያን አሳንጄ በአውሮፓውያኑ 2010 እና 2011 አሹልኮ ባወጣቸው ሰነዶች ምክንያት በአሜሪካ ባለስልጣናት ይፈለጋል።

በዊክሊክስ የታተሙት እነዚህ ሾልከው የወጡት ሰነዶች ከኢራቅና አፍጋኒስታን ጦርነት ጋር የተያያዙ ናቸው።

የአውስትራሊያ ዜግነት ያለው ጁሊያን አሳንጅ በለንደን ቤልማርሽ እስር ቤት የሚገኝ ሲሆን ተላልፎ ላለመሰጠትም ከፍተኛ ትግል እያደረገ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ዳግም የተቀሰቀሰው ግጭት አሜሪካን ስጋት እንዳጫረባት ገልፀዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ዘላቂ የሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እና በመጨረሻም ግጭቱን በዘላቂነት ለማስቆም ጥረታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል። ብሊንከን ፤ ላለፉት 5 ወራት የነበረው የተኩስ አቁም የበርካቶችን ሕይወት መታደጉንና…
#Turkiye #UK

ተርኪዬ ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ ማርች 24 /2022 በፌዴራል መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል የተኩስ አቁም ከታወጀ በኃላ ዳግም ግጭት መቀስቀሱን የሚገልፁ ሪፖርቶችን በሀዘን እና ስጋት ውስጥ ሆና እየተከታተለች እንደምትገኝ ገልፃለች።

ሁሉም ወገኖች ግጭት በዘላቂነት እንዲቆም ለማድረግ እና በሀገሪቱ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ወደ ንግግር እንዲመለሱ ጋብዛለች።

ለዚህ አላማ ደግሞ ሁሉንም አይነት ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን በድጋሚ አረጋግጣለች።

ተርኪዬ በኢትዮጵያ ሰላምን እና መረጋጋትን ለማስፈን ባሚደረገውን ጥረት ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልፃለች።

በሌላ በኩል ፤ ዩናይትድ ኪንግደም በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ግጭት መቀስቀሱን የሚገልፁ ሪፖርቶች እንደሚያሳስባት ገልፃለች።

ይህ ሁኔታ ቀድሞም አስከፊ የነበረውን የሰብዓዊ ሁኔታ ይበልጥ ያባብሰዋል ብላለች።

ዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ግጭት እንዲያቆሙና የፖለቲካ መፍትሄ እንዲመጣ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንዲመጡ አሳስባለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Germany • ጀርመን ከWFP መጋዘን ህወሓት የፈፀመውን በኃይል የነዳጅ ክምችት የመውሰድ ድርጊት " አፀያፊ " ስትል አወገዘች። የጀርመን መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያ ለ5 ወራት የዘለቀው የተኩስ አቁም ስምምነት መጣሱና ጦርነቱ እንደገና መጀመሩ በእጅጉ እንዳሳዘነው ገልጿል። በግጭቱ ውስጥ ያሉ ሁሉም አካላት አሁኑኑ መሳሪያቸውን አስቀምጠው ወደ ተኩስ አቁም በፍጥነት መመለስ አለባቸው ብሏል። " ግጭቱ…
#UK

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ፤ በመቐለ ያለው ነዳጅ ክምችቱ በኃይል በህወሓት (TPLF) መዘረፉን ካሳወቀ በኃላ ተቋማትና ሀገራት ድርጊቱን ማውገዛቸውን ቀጥለዋል።

ዩናይትድ ኪንግደም ፤ ትግራይ ክልል ከሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ህወሓት በኃይል ነዳጅ መውሰዱ ተቀባይነት የሌለው ነው ብላለች።

በተጨማሪ ድርጊቱ የሚሰሩትን የሰብዓዊ ድጋፍ ስራዎች በእጅጉ እንደሚጎዳው ገልፃለች።

ሁሉም ወገኖች በሰሜን ኢትዮጵያ በከፋ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ድጋፍ ለሚጠባበቁ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ድጋፍ መድረሱን ማረጋገጥ አለባቸው ብላለች።

ለሰብዓዊነት ተብሎ ታውጆ የነበረው ተኩስ አቁም በአስቸኳይ ወደቦታው እንዲመለስም ጥሪ አቅርባለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ንግስት ኤልዛቤት ዳግማዊት ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። የ96 ዓመቷ ዩናይትድ ኪንግደም እና የኮመን ዌልዝ አገራት ንግሥት ኤልዛቤት ዳግማዊት  በ96 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። የንግስቷን ህልፈት ባኪንግሃም ቤተ-መንግሥት አሳውቋል። @tikvahethiopia
#UK

የሀገራችን ኢትዮጵያ ፕሬዜዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ፤ የጎረቤታችን ኬንያ፣ ሶማሊያ ፣ ሱዳን መሪዎች ለንግስት ኤልዛቤት ዳግማዊት ስርዓተ ቀብር ወደ ዩናይትድ ኪንግደም መጓዛቸው ተሰምቷል።

ፕሬዚዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴ በንግስቷ ህልፈት በኢትዮጵያ ህዝብ ስም ሀዘናቸውን ለመግለፅ ለንደን የገቡ ሲሆን ለንግሥቲቱ በተዘጋጀ የሀዘን መግለጫ መዝገብ ላይም ሀዘናቸውን ገልፀዋል።

የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ፤ ዛሬ ለንግስት ኤልዛቤት ዳግማዊት ስርዓተ ቀብር ወደ ለንደን በረዋል። ፕሬዜዳንቱ በስርዓተ ቀብሩ ላይ ከታደሙ በኃላ ወደ ኒውዮርክ በማቅናት 77ኛው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እንደሚታደሙና ከዓለም መሪዎች ጋር እንደሚቀለቀሉ ገልፀዋል።

በንግስት ኤልዛቤት ዳግማዊት ህልፈት #ኬንያ የ3 ቀን ብሄራዊ ሀዘን አውጃ እንደነበር ይታወሳል። በንግስቷ ሞት በኬንያ ሀዘን መታወጁ በቅኝ ግዛት ወቅት ከተፈፀሙ ግፎች ጋር በተያያዘ በርካቶች ሲቃወሙ ነበር።

በሌላ በኩል የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ለንግስት ኤልዛቤት ዳግማዊት ድርዓተ ቀብር ዛሬ ለንደን ገብተዋል። ለንግሥቲቱ በተዘጋጀ የሀዘን መግለጫ መዝገብ ላይም ሀዘናቸውን እንደገለፁ ተሰምቷል።

የሱዳን ጦር አዛዥ እና የሃገሪቱ ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌ/ጄ አብዱል ፈታህ አል ቡርሃንም ወደ ለንደን አቅንተዋል።

@tikvahethiopia @officialtikvahethiopiaBOT
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የቦሪስ ጆንሰን ተተኪ ተመረጡ። የብሪታንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ሊዝ ትረስ አዲሷ የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተመርጠዋል። ትረስ እድሜያቸው 47 ሲሆን የቦሪስ ጆንሰን ተተኪ ሆነዋል። ሶስተኛዋ የሀገሪቱ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትርም እንደሆኑ ተገልጿል። ትረስ ተፎካካሪያቸው የነበሩት ሪሺ ሱናክን ሲሆኑ ያሸነፉት 57.4% ድምፅ በማግኘት እንደሆነ ዶቼ ቨለ ዘግቧል። @tikvahethiopia
#UK #China

ሪሺ ሱናክ የዩናይትድ ኪንግደም ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊሆኑ ነው።

ሊዝ ትረስ በተሾሙ በሰባት ሳምንት ስልጣን በቃኝ ያሉ ሲሆን እሳቸውን ለመተካት በተደረገው ውድድር ሪሺ ሱናክ አሸናፊ ሆነዋል።

ሱናክ ፤ የዩናይትድ ኪንግደም #የመጀመሪያው " እስያዊ " ዝርያ ያላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናሉ።

ጠ/ሚ ቦሪስ ጆንሰንን ለመተካት ከሰባት ሳምንታት በፊት በተደረገ ፉክክር ሪሺ ሱናክ ተወዳድረው የነበረ ቢሆንም በሊዝ ትረስ ሊሸነፉ ችለዋል።

ሊዝ ትረስ ' ግብር እቀንሳለሁ፤ ንግድን አሳልጣለሁ " ያሉት አዲስ ፖሊሲ ፍጹም ያልተጠበቀ የገበያ ምስቅልቅልና ብሔራዊ ጦስ ይዞባቸው መጥቶ ነው ሥልጣን እንዲለቁ የሆኑት።
 
ለ45 ቀናት ያህል ስልጣን ላይ የቆዩት ሊዝ ትረስ በዩናይትድ ኪንግደም ታሪክ ለአጭር ጊዜ የቆዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተመዝግበዋል። 

በሌላ መረጃ ፥  የቻይና ገዥ የሆነው ኮሚኒስት ፓርቲ ትላንት ባደረገው ጉባኤ ዢ ዢንፒንግን ዋና ጸሓፊ አድርጎ መምረጡን ተከትሎ ለ3ኛ ጊዜ ስልጣናቸው ተራዝሟል።

የፓርቲው #ዋና_ጸሃፊ በሃገሪቱ የመሪነት ቦታ የሚያስገኝ ሲሆን መጋቢት በሚደረገው የብሄራዊ ህዝቦች ጉባኤ በይፋ ስልጣናቸው ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ቢቢሲ አስነብቧል።

@tikvahethiopia
#UK

የዩናይትድ ኪንግደም (UK) ጠቅላይ ሚኒስትር ሪሺ ሱናክ እየተጓዘ ባለ መኪና ውስጥ ሳሉ የደህንነት (መቀመጫ) ቀበቶ ባለማሰራቸው ተቀጡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዞ ላይ ባለ መኪና ውስጥ ሆነው ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የሚለጠፍ ቪድዮ እየቀረጹ ሳለ የደህንነት (መቀመጫ) ቀበቷቸውን ባለማሰራቸው መቀጣታቸውን ፖሊስ ገልጿል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ  " ስህተት መሆኑን እናምናለን ይቅርታም እንጠይቃለን " ብሎ ቅጣቱን እንደሚከፍል አክሏል።

ዩናይትድ ኪንግደም ውስጥ የመቀመጫ ቀበቶ ያላደረጉ ሰዎች 100 ፓውንድ ይቀጣሉ።

ጉዳዩ ፍርድ ቤት ከደረሰ ቅጣቱ 500 ፓውንድ ሊደርስ ይችላል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለቅጣት የተዳረጉት ስለ መንግሥታቸው ወጭ የሚገልጽ ቪድዮ መኪና ውስጥ ቀርጸው በኢንስታግራም ገጻቸው ባጋሩበት ወቅት ነው።

ምንጭ፦ ቢቢሲ

@tikvahethiopia
#UK

" ማንም ሰው ወደ #ሩዋንዳ ለመሄድ 3 ሺህ ፓውንድ ለማግኘት ብቻ ወደዚህ ለመምጣት የሚሞክር አይመስለኝም " - የገንዘብ ሚኒስትር ኬቨን ሆሊንራክ

ዩናይትድ ኪንግደም  (ዩኬ) በአገሯ የጥገኝነት ጥያቄያቸው ተቀባይነት ያላገኙ ስደተኞችን እስከ 3 ሺህ ፓውንድ በመክፈል ወደ ሩዋንዳ ልትልክ መሆኑን እንዳስታወቀች ቢቢሲ ዘግቧል።

ይህ አዲስ የስደተኞች ዕቅድ የጥገኝነት ጥያቄያቸው ያልተሳካላቸው ስደተኞች በበጎ ፈቃደኝነት ወደ አገራቸው እንዲመለሱና ለዚህም የሚሆን ገንዘብ ይሰጣቸዋል ተብሏል።

የጥገኝነት ጥያቄያቸው በዩናይትድ ኪንግደም ውድቅ ለተደረገባቸው ለማንኛውም ስደተኞች ክፍት ይሆናል ተብሏል።

ይህ ዕቅድ በተለይም ወደ አገራቸው መመለስ በማይችሉ ስደተኞች ላይ ያነጣጠረ ነው።

የዩናትድ ኪንግደም የገንዘብ ሚኒስትር ኬቨን ሆሊንራክ ምን አሉ ?

- ወደ ሩዋንዳ ለመሄድ ለተስማሙ ስደተኞች የሚከፈለው ክፍያ የህዝብን ገንዘብ በአግባቡ መጠቀም ይሆናል።

- እነዚህን ሰዎች ያለ ምንም ጥቅም እዚህ ማቆየት ከዚያ የበለጠ ገንዘብ ያስወጣናል።

- " እዚህ በህገወጥ መንገድ ከመጣችሁ በዚህች አገር መቆየት አትችሉም " የሚለውን መልዕክት ያስተላልፋል። መሰረታዊ ነጥብ ይህ ነው።

- ማንም ሰው ወደ ሩዋንዳ ለመሄድ 3 ሺህ ፓውንድ ለማግኘት ብቻ ወደዚህ ለመምጣት የሚሞክር አይመስለኝም።

የዩናይትድ ኪንግደም መንግሥት " በህገወጥ መንገድ ገብተዋል " የተባሉ ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ ተልከው ጥያቄያቸው ከዚያ የሚታይበትን የተለየ እቅድም ለመተግበር መንግሥት እየሞከረ ይገኛል ተብሏል።

ይህ እቅድ ከሩዋንዳ የደህንንት ስጋት ጋር በተገናኘ በፍርድ ቤቶች ታግዶ ነበር።

እነዚህን ሙግቶች ለማሸነፍ መንግሥት የምስራቅ አፍሪካዊቷን አገር አስተማማኝ አድርጎ የሚፈርጃት ‘የሩዋንዳ ሴፍቲ ቢል’ (የሩዋንዳ የደህንነት ረቂቅን) ለማጽደቅ እየሞከረ ይገኛል።

አዲሱ ዕቅድ ከዚህ ከነበረው የተለየ እንዲሁም በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ እና በፓርላማው በሚጸድቀው ረቂቅ ላይ የተመሰረተ አለመሆኑንም ቢቢሲ ዘግቧል።

መረጃው የቢቢሲ እና ታይምስ ሬድዮ ነው።

@tikvahethiopia
#Rwanda #UK

ዩናይትድ ኪንግደም (UK) ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ #ሩዋንዳ ለማዛወር የያዘችው እና ከፍ ያለ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የታመነው ዕቅድ የሃገሪቱ ሕግ ሊሆን እንደተቃረበ ቪኦኤ ዘግቧል።

የዕቅዱ ተቃዋሚዎች ደግሞ ስደተኞቹን #በኃይል ከአገር የማስወጣቱን ውጥን ማገድ የሚችል አዲስ የሕግ መቋቋሚያ ለማበጀት እየሰሩ እንደሆነ ተነግሯል።

የጠቅላይ ፍርድ ቤቱን እገዳ ተጽዕኖ ለማስቀረት እና በላይኛው ምክር የቀረበውን ተቃውሞ ለመቋቋም የታለመው ይህ ሕግ በዚህ ሳምንት በሃገሪቱ ፓርላማ ይድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

‘ የሩዋንዳ ዕቅድ ’ የሚል ቅጽል የተሰጠው ይህ ውጥን ጠቅላይ ሚንስትር ሪሺ ሱናክ ‘ሕገ ወጥ ስደተኞችን ወደዚያች አገር የሚያጓጉዙ ጀልባዎች እንቅስቃሴ’ ለማስቆም ለገቡት ቃል ‘ወሳኝ እርምጃ ነው’ ተብሏል።

የሱናክ ቃል አቀባይ ዴቭ ፓሬስ ምን አሉ ?

" የእንግሊዝ ፓርላማ በያዝነው ሳምንት በሕገ ወጥ አስተላላፊዎች ከፍተኛ እንግልት እና ብዝበዛ የሚፈጽምባቸውን ሰዎች ህይወት የሚታደግ ህግ የማጽደቅ እድል ያገኛል።

አሁን ባለው አካሄድ መቀጠል እንደማንችል ግልፅ ነው። በመሆኑም ይህ ሁኔታ የሚለወጥበት ጊዜው አሁን ነው። " ብለዋል።


በአነስተኛ ጀልባዎች ተጓጉዘው የእንግሊዝ ቻናልን በማቋረጥ ከዚያ የሚደርሱትን ጥገኝነት ጠያቂዎች ወደ ምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ሩዋንዳ ለማዛወር እና በቋሚነትም ኑሯቸውን በዚያ እንዲያደርጉ በማቀድ ሁለቱ አገሮች የተፈራረሙት ስምምነት 2 ዓመታት አስቆጥሯል።

በፍርድ ቤት የታገደው ዕቅድ እንግሊዝን በትንሹ 470 ሚሊዮን ዶላር ሊያስወጣት እንደሚችል ቪኦኤ በዘገባው አስፍሯል። #VOA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የሩዋንዳ እቅድ (ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ መላክ) ገና ከጅምሩ ሞቶ የተቀበረ ነው " - አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር

ከሰሞኑን ዩናይትድ ኪንግደም (UK) አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር አግኝታለች።

አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር የሌበር ፓርቲ መሪ ሰር ኪር ስታርመር ናቸው።

ፓርቲው የሪሹ ሱናክን የወግ አጥባቂ (ኮንሰርቫቲቭ) ፓርቲ በከፍተኛ ብልጫ ነው ዘርሮ ያሸነፈው።

በከፍተኛ ብልጫ የተሸነፉት ሱናክ ፥ " የሕዝቡን ቁጣ ሰምቻለሁ። ለዚህ ሥራ ያለኝን ነገር ሁሉ ሰጥቻለሁ። ይሁን እንጂ የዩናይትድ ኪንግደም (UK) መንግሥት መለወጥ እንዳለበት ግልጽ የሆነ መልዕክታችሁን አስተላልፋችኋል፤ የሚተካኝም ሲገኝ ከፓርቲ መሪነት እለቃለሁ " ብለዋል።

በሌላ በኩል የምርጫ ውጤቱን ተከትሎ ስልጣን የተረከቡት አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪር ስታርመር ዛሬ የመጀመሪያ መግለጫቸውን ሰጥተዋል።

በዚህም ፥ በጥገኝነት ጠያቂዎች / ስደተኞች ጉዳይ የቀድሞው የወግ አጥባቂ መንግሥትን ፖሊሲ እንደማያስቀጥሉ በይፋ አሳውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ " የሩዋንዳ እቅድ (ጥገኝነት ጠያቂዎችን /ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ መላክ) ገና ከጅምሩ ሞቶ የተቀበረ ነው " ብለዋል።

መንግስታቸው ፥ የቀድሞው አገዛዝ በህገወጥ መንገድ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም የገቡ ጥገኝነት ጠያቂዎች / ስደተኞችን ወደ ሩዋንዳ ለመላክ የጀመረውን ስራ እንደማይቀጥሉበት ተናግረዋል።

" ከሩዋንዳ ጋር የተደረሰው ስምምነት አይቀጥልም ውድቅም ይሆናል " ያሉት ጠ/ሚ ስታርመር  በዚህ የስደተኞች ጉዳይ ላይ የቀድሞው መንግስት ፖሊስ አይቀጥልም ብለዋል።

#UK
#Rwandascheme

@tikvahethiopia