TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም ውሳኔ አሳለፈ። መንግስት ባወጣው መግለጫ ፤ በአሁኑ ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ክልል ነዋሪዎች የሰብዓዊ እርዳታን ፍለጋ ወደአጎራባች ክልሎች እየተጓዙ መሆኑን አመልክቷል። እነዚህ ዜጎች የሰብዓዊ እርዳታው ከቀያቸው ሳፈናቀሉ ባሉበት እንዲርሳቸው ቢደረግ እንግልታቸውን እንደሚቀንስ በጽኑ እንደሚያምን አሳውቋል። በመሆኑም በከፍተኛ…
#UK

ዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ መንግሥት ያሳለፈውን ውሳኔ በደስታ እንደምትቀበል እና መንግስት የሰብዓዊ ድጋፍ ፍላጎት ምላሹን ለማሳደግ የሚያደርገውን ጥረት ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን አስታውቃለች።

ዩናይትድ ኪንግደም ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት አዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲዋ ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም መወሰኑን እና ያልተገደበ ሰብዓዊ እርዳታ ወደ ትግራይ እንዲደርስ ያሳለፈውን ውሳኔ በደስታ እንደምትቀበል ገልፃለች።

የትግራይ ባለሥልጣናትም ምላሽ እንዲሰጡ ጠይቃለች።

ዩናይትድ ኪንግደም ፤ መንግስት የሰብዓዊ ድጋፍ ፍላጎት ምላሹን ለማሳደግ የሚያደርገውን ጥረት ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን አስታውቃለች።

የኢትዮጵያ መንግስት ዛሬ ከሰዓት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ማቆሙን ማብሰሩ እና ዓለም አቀፍ ለጋሾች እያቀረቡ ያለውን ድጋፍ እና እርዳታ #በከፍተኛ_መጠን_እንዲጨምሩ ጥሪ ማቅረቡ ይታወቃል።

እስካሁን በትግራይ ክልል በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም።

@tikvahethiopia