TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ETHIOPIA

👩‍⚕️👨‍⚕️የጤና አገልግሎት ሰራተኞች
🏥 የጤና አገልግሎት ተቋማት እና
🚑 የህክምና መጓጓዣዎች በሁሉም ሁኔታ ውስጥ መከበር አለባቸው።

አምቡላንሶችን 🚑 አያዘግዩ። የጦር መሳሪያዎችን በጤና አገልግሎት ተቋማት ውስጥ ይዘው አይግቡ። የጤና አገልግሎት ተቋማት መጠቃት / መዘረፍ የለባቸውም። የጤና አገልግሎት ሰራተኞች በፍፁም ጥቃት ሊደርስባቸው አይገባም።

#ያስተውሉ 👉 የጤና አገልግሎት ሰራተኞች ለየትኛውም አካል አይወግኑም። ስራቸው ህይወት ይታደጋል ፤ ስራቸውን ያከናውኑ !

#ICRC

@tikvahethiopia
#Amhara , #Dessise 📍

ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (አይሲአርሲ) የደሴ አካል ተሃድሶ ማዕከልን ስራ ለማስጀመር የሚያግዙ መሰረታዊ ቁሳቁሶች እና ማሽነሪ ድጋፍ አድርጓል፡፡

ማዕከሉ ያሉበትን ክፍተቶች ለመሙላት እና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች የሚሰጠውን ድጋፍ እንዲቀጥል ለማገዝ ከግጭቱ በኋላ ማዕከሉ የሚገኝበትን ሁኔታ ላይ ዳሰሳ አድርጓል፡፡

#ICRC

@tikvahethiopia
#Tigray

ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ እ.ኤ.አ ከጥር 2021 እስከ ጥር 2022 ባለው ጊዜ ውስጥ በትግራይ ክልል ከቤተሰቦቻቸው እና ወዳጆቻቸው ለተነጣጠሉ 41,326 ሰዎች ነጻ የስልክ ማስደወል አገልግሎት መስጠቱን ገልጿል።

#ICRC

@tikvahethiopia
#Afar

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር በመሆን ከትግራይ ክልል ተፈናቅለው በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ላይ ለተጠለሉ 9,000 ሰዎች የምግብ ድጋፍ አድርጓል፡፡

ድጋፉ የስንዴ ዱቄት ፣ አተር ክክ ፣ የማዕድ ጨው እና የምግብ ዘይትን ያካተተ ነው፡፡

በሌላ በኩል ፤ ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በአፋር ክልል ከ500,000 በላይ እንስሳትን ከአደገኛ በሽታዎች ለመከላከል የሚረዳ የክትባት ዘመቻ እያከናወነ ይገኛል፡፡

ይህም በግጭት የተጎዱ በክልሉ የሚገኙ አርብቶ አደር ማህበረሰቦች መተዳደሪያ ዘላቂነትን ለማረጋገጥ ይረዳል ተብሏል።

#ICRC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ የህክምና፣ ምግብ እና የውሃ ማጣሪያ ግብዓቶችን ያካተተ ድጋፍ ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2014 ዓ.ም ትግራይ ክልል ደርሷል፡፡ ይህም እ.ኤ.አ ከመስከረም 2021 በኋላ በየብስ ትራንስፖርት ወደ ክልሉ የደረሰ የመጀመሪያው የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ድጋፍ ነው፡፡ https://www.icrc.org/en/document/ethiopia-icrc-resumes-aid…
#Tigray , #Mekelle📍

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በዚህ ወር ለሁለተኛ ጊዜ ፦
👉 የህክምና ቁሳቁሶችን ፣
👉 አስቸኳይ የምግብ ድጋፎችን ፣
👉 የውሃ ማጣሪያ ግብዓቶችን እና አስፈላጊ የቤት ውስጥ ቁሳቁሶችን የያዘ ቡድን ዛሬ ሚያዝያ 6 ቀን 2014 ዓ.ም የትግራይ ክልል መዲና መቐለ ገብቷል።

በተጨማሪም ድጋፉ ለአካል ተሃድሶ ማዕከል አስፈላጊ የሆኑ የህክምና ቁሳቁሶችን ያካተተ ነው።

#ICRC

@tikvahethiopia
#ICRC #Oromia #Afar

ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሀረርጌ ዞን፣ ኩምቢ ለሚገኙ 5000 አባወራዎች የእንስሳት መኖ እያከፋፈለ ይገኛል።

ስርጭቱ በአካባቢው ለተከሰተው ድርቅ ምላሽ ሲሆን በዚህ ኦፕሬሽን እስከ 150,000 እንስሳት ይመገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ድርጅቱ አስታውቋል።

በሌላ በኩል ድርጅቱ ፤ ባሳለፍነው ሳምንት በአፋር ክልል ሲልሳ ለሚገኙ 9,000 የተፈናቀሉ ሰዎች መሰረታዊ የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶችን ማለትም ሶላር የእጅ ባትሪዎችን፣ ጀሪካኖችን፣ የማዕድ ቤት እቃዎችን፣ ምንጣፍ እና መጠለያ ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል።

@tikvahethiopia
#Oromia #ICRC

በግጭት ምክንያት ተፈናቅለው የነበሩ እና በቅርቡ በምስራቅ ወለጋ፣ ጉቶ ጊዳ ወረዳ፣ አለልቱ ቀበሌ ወደሚገኘው መኖሪያ ስፍራቸው ለተመለሱ 800 ግለሰቦች መሰረታዊ የቤት ውስጥ መገልገያ ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጉን የዓለም ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) አስታውቋል።

ድጋፍ ከተደረጉት ቁሳቁሶች መካከል ሶላር የእጅ ባትሪዎች ፣ ጀሪካኖች ፣ የማዕድ ቤት እቃዎች ፣ ምንጣፎች ፣ የንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁሶች እና መጠለያ እንደሚገኙበት ከድርጅቱ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#ICRC

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚያካሂደውን የሰብል ምርጥ ዘር ስርጭት በመቀጠል በግጭቱ ለተጎዱ 15,000 አርሶ አደር አባወራዎች ድጋፍ አቅርቧል።

አርሶ አደሮቹ በላዕላይ ማይጨው ከሚገኙ 8 ቀበሌዎች እና በማዕከላዊ ትግራይ ዞን በአድዋ ወረዳ ከሚገኙ 4 ቀበሌዎች የመጡ ናቸው። ኮሚቴው ለእያንዳንዱ ቤተሰብ 10 ኪሎ ግራም የጤፍ ዘር እና 2.5 ኪሎ ግራም የማሽላ ዘር ድጋፍ አድርጓል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
#ICRC

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ፤ ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሰዎች አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ማግኘት ህይወታቸውን እንደሚታደግ ገልጾ ፦ በሐይቅ፣ ደሴ፣ ወልድያ፣ መርሳ፣ ኮምቦልቻ፣ አይደር፣ ማይጨው፣ ዓዲግራት፣ መሆኒ፣ ሽሬ፣ ኣክሱም፣ ላሊበላ፣ ሰቆጣ፣ ዋድላ፣ ባህር ዳር፣ ደባርቅ፣ ጎንደር፣ ነቀምት፣ ጊምቢ እና ደምቢዶሎ ሆስፒታሎች ያሉትን የአንድ መስኮት የአገልግሎት ማዕከላትን በመደገፍ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።

በሌላ በኩል ኮሚቴው በጤና ድንገተኛ አደጋዎች ፈጣን እና ውጤታማ የሆነ ምላሽ ለመስጠት ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ጋር በቅርበት በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልጾ ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ለሚገኙ 14 የክልል እና ዞን የኢቀመማ ቅርንጫፎች የመጀመሪያ እርዳታ መስጫ መሳሪያዎችን እና የአምቡላንስ አቅርቦቶችን ድጋፍ ማድረጉ አሳውቋል።

ከዚህም በተጨማሪ ፤ ጦርነት በተካሄደባቸው አካባቢዎች #ተቀብረው_ሳይፈነዱ_የሚቀሩ ፈንጂዎች በሰዎች አካል ላይ የሚያደርሱት ጉዳት ከፍተኛ እንደሆነ የሚገልፀው የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ተጎጂዎችን ለመርዳት በኢትዮጵያ ውስጥ በባህር ዳር፣ ደሴ፣ አሶሳ፣ አሰላ፣ ነቀምት፣ አርባምንጭ፣ መናገሻ፣ ጅግጅጋ፣ ድሬዳዋ፣ መቐለ እና ኪዩር ሆስፒታል የአካል ማገገሚያ ማዕከላትን በማጠናከር ላይ እንደሆነ ገልጿል።

#ICRCEthiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ICRC የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ፤ ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሰዎች አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ማግኘት ህይወታቸውን እንደሚታደግ ገልጾ ፦ በሐይቅ፣ ደሴ፣ ወልድያ፣ መርሳ፣ ኮምቦልቻ፣ አይደር፣ ማይጨው፣ ዓዲግራት፣ መሆኒ፣ ሽሬ፣ ኣክሱም፣ ላሊበላ፣ ሰቆጣ፣ ዋድላ፣ ባህር ዳር፣ ደባርቅ፣ ጎንደር፣ ነቀምት፣ ጊምቢ እና ደምቢዶሎ ሆስፒታሎች ያሉትን የአንድ መስኮት የአገልግሎት ማዕከላትን በመደገፍ…
#ICRC #Tigray

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) በተለያዩ ክልሎች በግጭት ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ማድረጉን ቀጥሏል።

ኮሚቴው #በትግራይ_ክልል በግጭት የተጎዱ አርሶ አደሮችን ምርታማነት ለማሳደግ ፦

👉 በማዕከላዊ፣
👉 በምስራቅ ፣
👉 በደቡብ ምስራቅ እና በደቡብ ዞኖች ለሚገኙ ለ20,000 አባውራዎች (120,000 ግለሰቦች) የአፈር ማዳበሪያ በማከፋፈል ላይ እንደሚገኝ ዛሬ አሳውቋል።

ICRC ፤ ከሰሞኑን በትግራይ፣ አማራ እንዲሁም ኦሮሚያ ክልል ከተሞች ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ እና ጦርነት በተካሄደባቸው አካባቢዎች ተቀብረው ሳይፈነዱ ሚቀሩ ፈንጂዎች በሰዎች አካል ላይ የሚያደረሱትን ጉዳት ተንተርሶ ተጎጂዎችን ለመርዳት በተለያዩ ከተሞች የአካል ማገገሚያ ማዕከላትን በማጠናከር ላይ እንደሆነ መግለፁ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ICRC #Tigray የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) በተለያዩ ክልሎች በግጭት ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ማድረጉን ቀጥሏል። ኮሚቴው #በትግራይ_ክልል በግጭት የተጎዱ አርሶ አደሮችን ምርታማነት ለማሳደግ ፦ 👉 በማዕከላዊ፣ 👉 በምስራቅ ፣ 👉 በደቡብ ምስራቅ እና በደቡብ ዞኖች ለሚገኙ ለ20,000 አባውራዎች (120,000 ግለሰቦች) የአፈር ማዳበሪያ በማከፋፈል ላይ እንደሚገኝ ዛሬ አሳውቋል።…
#ICRC

ICRC ለተፈናቃይ አባወራዎች የገንዘብ ድጋፍ አደረገ።

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ በግጭት የተፈናቀሉ አብዛኛዎቹ ሰዎች በሕይወት ለመቆየት በሰብአዊ እርዳታ ላይ ጥገኛ መሆናቸውን አመልክቷል።

በመጠለያ ካምፖች ውስጥ ያሉ ተፈናቃይ ሰዎች ደግሞ ምንም አይነት አስተማማኝ የኢኮኖሚ ምንጭ የላቸውም ሲል ገልጿል።

በዚህም ምክንያት በአማራ ክልል ፦ ሰሜን ወሎ ዞን፣ ሃብሩ ወረዳ፣ ጃራ የተፈናቃዮች መጠለያ ካምፕ ለሚገኙ 3,674 #ተፈናቃይ_አባወራዎች (22,044 ግለሰቦች) መሰረታዊ ፍላጎቶችን ለማሟላት የሚያግዝ የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን አሳውቋል።

@tikvahethiopia