TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Update ብርጋዴር ጀነራል #ክንፈ_ዳኘው በቁጥጥር ስር የዋሉት #በትግራይ ክልል ልዩ ፖሊስ ነው።

via-etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አክሱም🔝

የአየርላንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊዮ ቫራድካር #በትግራይ_ክልል ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ አክሱም ገብተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክሱም ሲደርሱ የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር እና ከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሀላፊ ዶክተር አብረሃም ተከስተን ጨምሮ ከፍተኛ የክልሉ መንግስት ባለስልጣናት አቀባበል አድርገውላቸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትግራይ ክልል ቆይታቸው በዓየርላንድ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ይጎበኛሉ ተብሎ ነው የሚጠበቀው። በተጨማሪም በሽረ እንደስላሴ የሚገኝ የስደተኛ ጣቢያንም ይጎበኛሉ ተብሎ ነው የሚጠበቀው።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ኢሰመኮ

EHRC / ኢሰመኮ #በትግራይ_ክልል ከቀጠለው ግጭት ጋር ተያይዞ በሲቪል ሰዎች ላይ እንግልት እና እስር ፣ የንግድ ቤት መዘጋት ፣ ብሎም በሲቪል ሰዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት መከሰቱንና ሕይወት መጥፋቱን፣ እንዲሁም በታሳሪዎችና በምርኮኞች ላይ የሚደርስ ኢሰብአዊ አያያዝ፣ በስደተኞች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችና ሕጻናትን ለውትድርና መጠቀም የሚያመላክቱ መረጃዎች እጅግ የሚያሳስበው መሆኑን ገልጿል።

* ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ICRC የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ፤ ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሰዎች አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ማግኘት ህይወታቸውን እንደሚታደግ ገልጾ ፦ በሐይቅ፣ ደሴ፣ ወልድያ፣ መርሳ፣ ኮምቦልቻ፣ አይደር፣ ማይጨው፣ ዓዲግራት፣ መሆኒ፣ ሽሬ፣ ኣክሱም፣ ላሊበላ፣ ሰቆጣ፣ ዋድላ፣ ባህር ዳር፣ ደባርቅ፣ ጎንደር፣ ነቀምት፣ ጊምቢ እና ደምቢዶሎ ሆስፒታሎች ያሉትን የአንድ መስኮት የአገልግሎት ማዕከላትን በመደገፍ…
#ICRC #Tigray

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) በተለያዩ ክልሎች በግጭት ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ማድረጉን ቀጥሏል።

ኮሚቴው #በትግራይ_ክልል በግጭት የተጎዱ አርሶ አደሮችን ምርታማነት ለማሳደግ ፦

👉 በማዕከላዊ፣
👉 በምስራቅ ፣
👉 በደቡብ ምስራቅ እና በደቡብ ዞኖች ለሚገኙ ለ20,000 አባውራዎች (120,000 ግለሰቦች) የአፈር ማዳበሪያ በማከፋፈል ላይ እንደሚገኝ ዛሬ አሳውቋል።

ICRC ፤ ከሰሞኑን በትግራይ፣ አማራ እንዲሁም ኦሮሚያ ክልል ከተሞች ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ እና ጦርነት በተካሄደባቸው አካባቢዎች ተቀብረው ሳይፈነዱ ሚቀሩ ፈንጂዎች በሰዎች አካል ላይ የሚያደረሱትን ጉዳት ተንተርሶ ተጎጂዎችን ለመርዳት በተለያዩ ከተሞች የአካል ማገገሚያ ማዕከላትን በማጠናከር ላይ እንደሆነ መግለፁ ይታወሳል።

@tikvahethiopia