#Afar

የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ (ICRC) ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር በመሆን ከትግራይ ክልል ተፈናቅለው በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ ላይ ለተጠለሉ 9,000 ሰዎች የምግብ ድጋፍ አድርጓል፡፡

ድጋፉ የስንዴ ዱቄት ፣ አተር ክክ ፣ የማዕድ ጨው እና የምግብ ዘይትን ያካተተ ነው፡፡

በሌላ በኩል ፤ ዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ በአፋር ክልል ከ500,000 በላይ እንስሳትን ከአደገኛ በሽታዎች ለመከላከል የሚረዳ የክትባት ዘመቻ እያከናወነ ይገኛል፡፡

ይህም በግጭት የተጎዱ በክልሉ የሚገኙ አርብቶ አደር ማህበረሰቦች መተዳደሪያ ዘላቂነትን ለማረጋገጥ ይረዳል ተብሏል።

#ICRC

@tikvahethiopia