TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሀሰተኛ_ዜና

"በአባቴ ህይወት ላይ አታሟርቱ፤ አባቴ አልሞተም" - ጃጋማ ዋሚ

በኖሩበት የምድር ህይወት ፣ እያንዳንዱን ያደረጉትን ተግባር ፣ በቀን ፣ በአመተ ምህረት ፣ በሰዓት ሳያዛንፉ የሚናገሩት ጀግናዉ አትሌት ዋሚ ቢራቱ ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል የተባለዉ ዉሸት ነዉ።

እባካቹህ መረጃ ሳታረጋግጡ ሰዉን አታሳስቱ።

Via መኳንንት በርሄ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#ሀሰተኛ_መረጃ

የመቐለ ጊዜያዊ ከንቲባ የነበሩት አቶ አታኽልቲ አዲስ ሹመት እንደተሰጣቸው ተደርጎ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው ዜና ሀሰተኛ መሆኑን አዲስ ዘይቤ ዘግቧል።

አቶ አታኽልቲ ኃይለስላሴ ፥ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ሥራ አስፈጻሚ በመሆን አዲስ ሹመት ስለማግኘታቸው የተሰራጨው ዜና #ሀሰት መሆኑን ተናግረዋል።

የቀድሞው ጊዜያዊ ከንቲባ ፥ "አሁን የመቐለ ነዋሪ ብቻ ነኝ ሲሉ" አስረድተዋል።

ምንጭ፦ www.addiszeyeb.com

@tikvahethiopia
#TiffanyHaddish

የ41 ዓመቷ አሜሪካዊት ተዋናይትና ኮሜዲያን ቲፋኒ ሀዲሽ በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ስላለው ግጭት በሰጠቻቸው አስተያየቶች/በምታጋራው መልዕክቶ ምክንያት ከፍተኛ ተቃውሞ እየቀረበባት ነው።

የምታጋራው መልዕክቶች በርካታ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን አስቆጥቷል።

ቲፍኒ ሀዲሽ ፥ "በትግራይ ላይ የሚፈፀውን የንፁሃን ግድያ ፣ የሴቶች መደፈር፣ የህፃናት ሞት ክዳለች ፣ በትግራይ ጉዳይ ጦሯን ላሰማራቸው #ኤርትራ በተለይም አምባገነን ለሆነው የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ድጋፍ ትሰጣለች" በሚል ነው ከፍተኛ ተቃውሞ እያስተናገደች የምትገኘው።

ቲፍኒ ሀዲሽ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በትግራይ ስላለው ሁኔታ በትዊተር ገጿ የተለያዩ መልዕክቶችን እያስተላለፈች ሲሆን ከነዚህ ውስጥ አንዱ ከትግራይ ጦርነት ጋር በተያያዘ የሚሰራጩ #ሀሰተኛ መረጃዎች የሚመለከት ነው።

በተጨማሪ፥ በአንድ ሪትዊት ላይ የቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዜዳንት ዶ/ር ደብረፅዮን "ጦርነቱ የህዝብ መሆኑን ህፃናትም የዚህ አካል ስለመሆናቸው" ተናግረውበታል የተባለውን የእሳቸውን ንግግር አጋርታለች።

ከተቃዋሚዎቹ በተቃራኒው ደግሞ የምታጋራቸውን መልዕክቶች ትክክል እንደሆኑ የሚገልፁ በርካታ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ታይተዋል።

ቲፍኒ ሀዲሽ በ1979 እ.አ.አ. በሎስ አንጀለስ የተወለደች ሲሆን አባቷ ፀሃዬ ረዳ ሀድሽ በወቅቱ የኢትዮጵያ አካል የነበረችውን ኤርትራን ጥለው የተሰደዱ ስደተኛ ነበሩ።

ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ቲፋኒ ሀዲሽ ከኤርትራና ከመሪዋ ኢሳያስ አፍወርቂ ጋር ጥሩ የሚባል ወዳጅነትንና ቅርርብ ስለመፍጠራቸው ይነገራል።

ለመጀመሪያ ጊዜ ኤርትራን የጎበኘችው እ.ኤ.አ. በ2018 ሲሆን በወቅቱ የአባቷን ህልፈት ተከትሎ በእሳቸውን የቀብር ስነስርዓት ላይ ለመገኘት ነበር።

@tikvahethiopia
#MoSHE

የኢፌዴሪ ሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ የሚገኘው ደብዳቤ #ሀሰተኛ ነው አለ።

ዛሬ በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶ ለደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ እንደተጻፈ የሚገልጽ ደብዳቤ በማህበራዊ ሚዲያዎች እየተዘዋወረ ነው።

ደብዳቤው “የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ስለመስጠት” የሚል አርዕስት ያለው ሲሆን ደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ የአማራ ተወላጅ ተማሪዎችን ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እውቅና ውጭ ምደባ ማካሄዱን እንዲያቆም የሚያስጠነቅቅ ይዘት አለው።

በዚህ ጉዳይ ላይ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶን ለ "ኢትዮጵያ ቼክ" በሰጡት ቃል ደብዳቤው ሀሰተኛ መሆኑ ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ ፥ ደብዳቤው ተጻፈ በተባለበት የታሕሳስ ወር የ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ገና መሰጠት አልተጀመረም ነበር ብለዋል።

በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ወደዚህ ዓመት የተሸጋገረው የ2012 ዓ.ም ፈተና ከካቲት 19 ጀምሮ እስከ መጋቢት 2 ቀን 2013 ዓ.ም የተሰጠ ሲሆን ውጤቱ ይፋ የተደረገው በመጋቢት ወር አጋማሽ እንደነበር አስታውሰዋል።

ሚኒስትሩ ፥ የተማሪዎች የዩኒቨርስቲ ምደባ በሚያዚያ ወር የተከነወነ መሆኑ በመግለፅ ደብዳቤው ተጻፈ በተባለበት ታሕሳስ ወር ምንም አይነት የተማሪዎች ምደባ እንዳልነበር አስረድተዋል።

ዶ/ር ሳሙኤል ደብዳቤውን እርሳቸው እንዳልጻፉት ገልጸዋል።

ዶ/ር ሳሙኤል በታህሳስ ወር የተማሪዎችን ምደባ የተመለከተ ደብዳቤ ሊጻፍ እንደማይችል አክለዋል።

ደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ማምሻው በፌስቡክ ገጹ በለጠፈው አጠር ያለ መልዕክት “ዩኒቨርስቲያችንን በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጩ ወሬዎች አሳሳችና የውሸት መሆናቸውን እንገልጻለን” ብሏል።

#ኢትዮጵያቼክ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ምርጫ2013 ውድ የቲክቫህ ቤተሰቦች በዛሬው ዕለት "የምርጫ ወቅት እና ሀሰተኛ የመረጃ ስርጭት" ላይ ትኩረቱት ያደረገ አጭር ገለፃ በቀጥታ በቴሌግራም Voice Chat ይኖረናል። ገለፃው በዋነኝነት በዚህ ለሀገሪቱ ወሳኝ በሆነ ወቅት ላይ በሀሰተኛ የመረጃ ስርጭት ሊፈጠር የሚችለውን ችግር በማስቀረቱ ረገድ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለን እንጠብቃለን። አቅራቢዎቹ : ከመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል…
Audio
AudioLab
#ሀሰተኛ_መረጃ_እና_ምርጫ2013

"የምርጫ ወቅት ላይ ስለሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች እና እንዴት እነዚህን ሀሰተኛ መረጃዎችን መከላከል እንችላለን" በሚለው ጉዳይ ዛሬ በቀጥታ Voice Chat ለቲክቫህ ቤተሰቦች ገለፃ ተደርጓል/ለጥያቄዎችም ምላሽ ተሰጥቷል።

ገለፃና ለጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ከCARD በፍቃዱ ኃይሉ ፤ ከኢትዮጵያ ቼክ ደግሞ ኤልያስ መሰረት ነበሩ።

ምናልባት በቀጥታ በVoice Chat ገለፃውን ማዳመጥ ሳትችሉ የቀራችሁ ቤተሰቦቻችን ከላይ የድምፅ ቅጂው ተያይዟል፤ አዳምጡት።

@tikvahethiopia
#እጅግ_ከፍተኛ_ጥንቃቄ

በየምርጫ ጣቢያዎቹ ውጤት እየተለጠፈ ይገኛል፤ ነገር ግን በርካታ #ሀሰተኛ መረጃዎች እየተሰራጩ ነው።

ውድ አባላት ይፋዊና ቦርዱ ማህተም ያላረፈባቸውን ፤ በተለም ደግሞ በዘፈቀደ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩ መረጃዎችን #በጥንቃቄ እንድትከታተሉ ይሁን።

ከምርጫ በኃላ ችግር የሚፈጥረው እንዲህ አይነት ጉዳይ ስለሆነ ሰላማዊ ሂደቱ እንዲጠበቅ አስተዋጽኦ አድርጉ።

@tikvahethiopia
#Update

"በደሴ 10 በሚሆኑ ምርጫ ጣቢያዎች የድምፅ መስጫ ሳጥኖች ተሞልተው ተገኙ" ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው መረጃ ሀሰት መሆኑን ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ አሳውቀዋል።

በ10ሩ የምርጫ ጣቢያዎች የተፈጠረውን ጉዳይም ዛሬ በነበራቸው መግለጫ አስረድተዋል።

በምርጫ ጣቢያ ደረጃ የውጤት አገላለፅ እንዲሁም የውጤት አመዘጋገብ በትክክለኛው መንገድ ስለመፈፁ የሚረጋገጥበት የራሱ ደረጃ አለው ይህም በስልጣና ላይ ተሰጥቷል ብለዋል።

ከእንዚህ ደረጃዎች/ሂደቶች መካከል ፦
- የመጀመሪያው በዚያ ጣቢያ ስንት ሰው ነው የሚመዘገበው ?
- በዕለቱ መጥቶ መዝገብ ላይ ፈርሞ ድምፅ የሰጡ ብዛት ስንት ናቸው ? ፊርማቸው ተቆጥሮ መመዝገብ አለበት።
- የመጡት ሰዎች ተመዝግበዋል ከተባሉት ሰዎች ቁጥራቸው መበላለጥ ስለሌለበት ይህም ይረጋገጣል።
- የደረሰው የድምፅ መስጫ ወረቀት ብዛት ስንት ነው ?
- ሳጥን ውስጥ የተገኘው ምን ያህል ነው ?
- የተበላሸ የድምፅ መስጫ ወረቀት ስንት ነው ? የሚሉት ይገኙበታል።

ደሴ የተገኙት 10 ምርጫ ጣቢያዎች ትክክለኛነቱን የሚያረጋግጡ አካሄዶችን ሳይፈፅሙ ፣ ሂሳቡንም በትክክል ሳይሰሩ በመላካቸው በምርጫ ክልል ደረጃ እንደገና መታየት ስላለበት / ድምፅ ቆጠራው መደገም ስላለበት የምርጫ ክልሉ ለጊዜው ኳራንታይን አድርጎ አስቀምጦታል።

ይህ ሁኔታ ነው የማይሆን ትርጉም ተሰጥቶት #ሀሰተኛ_መረጃ እንዲሰራጭ ምክንያት የሆነው ሲሉ ወ/ሪት ብርቱካን ሚዴቅሳ ገልፀዋል።

@tikvahethiopia
ይህ ገፅ የዓሲምባ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ዓዴፓ) ገፅ ነው ?

ፌስቡክ ላይ ዓሲምባ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ - ዓዴፓ Assimba Democratic party-ADP በሚል ስም የተከፈተ እና ከ20 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት ገፅ #ሀሰተኛ ነው።

ከትላትን ጀምሮ ይህን ገፅ ዋቢ አድርገው የተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲሁም አንድ ዓለም አቀፍ ሚዲያ (ዶቼ ቨለ) መረጃዎችን ሲያጋሩ ተመልክተናል።

የፓርቲው ሊቀመንበር ከመታሰራቸው ከወራት በፊት ገፁ ሀሰተኛ ስለመሆኑ አሳውቀው ነበር።

የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ ዶሪ አስገዶም "ገፁ ሀሰተኛ መሆኑን ፣ በዚሁ ሀሰተኛ ገፅ ላይ የሚወጡ መረጃዎች እና መግለጫዎች ዓሲምባ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ዓዴፓ)ን የማይወክሉ እንደሆነ" በተደጋጋሚ ገልፀው ነበር።

አቶ ዶሪ አስገዶም ከትግራይ ጦርነት ጋር በተያያዘ በኢሮብ ወረዳ የኤርትራ ወታደሮች ወረራ እየፈጸሙ ነው በማለታቸው ሳቢያ ለእስር ስለመዳረጋቸው ነው ከፓርቲው የተገኘው መረጃ የሚያመለክተው።

አቶ ዶሪ ታስረው የሚገኙት አዲስ አበባ ውስጥ ነው።

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

#ሐምሌ_19 የቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ይከበራል።

ከመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም (ቤተመንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል) በደረሰን መልዕክት የፊታችን ሐምሌ 19 የቅዱስ ገብርኤል በዓል በደመቀ መልኩ ይከበራል።

"በዓመት 2 ጊዜ ታህሳስ እና ሐምሌ 19 ብቻ" እንደሚነግስ የተገለፀልን ሲሆን የዛሬ ዓመት በኮሮና ወረርሽኝ እና በአንዳንድ ወቅታዊ ጉዳዮች ምክንያት ለምዕመናን ውስን ሆኖ ነበር የተከበረው።

በዚህ ዓመት ግን ምዕመናን ራሳቸውን ጠብቀው ከተሟላ ፓርኪንግ ጋር እንዲሁም መንገዱም ስለተከፈተ መጥተው ማክበር ይችላሉ ተብሏል።

በዚህ አጋጣሚ አንዳንድ ገዳሙ እንደተዘጋ ተደርጎ የሚናፈሱ መረጃዎች ፍፁም #ሀሰተኛ ናቸው።

የ124 ዘመን እድሜ ያለው የመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በዳግማዊ ንጉሰ ነገሥት አፄ ምንሊክ መታነጹ ይነገራል።

አድራሻ ፦ ታላቁ ቤተመንግሥት (አንድነት ፓርክ) ጎን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ኢትዮጵያ ሱዳንን አላጠቃችም " - ጄነራል ብርሃኑ ጁላ የሱዳን ጦር በድንበር አካባቢ በርካታ ወታደሮቼ የኢትዮጵያ ወታደሮች በፈጸሙት ጥቃት ተገደሉብኝ ሲል ክስ አሰምቷል። የሱዳን ጦር ትላንት ባወጣው መግለጫ ፤ “በአል-ፋሻቃ የሚገኘውን የመኸር ምርትን ለመጠበቅ ኃላፊነት የተሰጣቸው ሃይሎቻችን… በኢትዮጵያ ጦር ሃይሎች እና ሚሊሻዎች በቡድን ጥቃት ተፈጽሞባቸዋል፣ ገበሬዎችን ለማስፈራራት እና የመኸር…
" የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የትኛውም ሉአላዊ ሀገር ላይ ጥቃት የመፈፀም አጀንዳ የለውም " - ዶ/ር ለገሰ ቱሉ

የኢትዮጵያን መከላከያ ሰራዊት በሱዳን ጦር ላይ ጥቃት ሰነዘረ እየተባለ የሚነዛው ወሬ #ሀሰተኛ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ መንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ አስታወቁ።

ሚኒስትሩ ይህን ያሳወቁት ለብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃል ነው።

ዶ/ር ለገሰ ፥ " አሸባሪው ኃይል በተለያየ መልኩ ሱዳን ውስጥ የሚያሰለጥናቸውን ሰርጎ ገቦች በተለያየ ቦታ በተለይም በመተማ አካባቢዎች በተለያየ ጊዜያት ያስገባል ፤ በተለያየ ጊዜ ኢትዮጵያን የሚተናኮሉ ሰርጎ ገቦች ይገባሉ፤ በዚህ መሰረት በርካታ ቁጥር ያላቸው ሰርጎ ገቦች ፣ ሽፍታዎች እና አሸባሪዎች በዛ መስመር ገብተው ነበር በዛ መስመር የገባውን ኃይል የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እና የአካባቢው ሚሊሻ መቷቸዋል ፤ ደምስሷቸዋል " ብለዋል።

የተለያዩ ሚዲያዎች እንደሚነዙት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የሱዳን ጦር ላይ ጥቃት ፈፅሟል የሚለው መሰረተቢስ ነው ሲሉ አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የትኛውም ሉአላዊ ሀገር ላይ ጥቃት የመፈፀም አጀንዳ የለውም ያሉት ዶ/ር ለገሰ ፥ " ቢኖረው ኖሮ የሱዳን ኃይሎች ወረው በግድ የያዙት መሬት አለ ፤ ይሄንንም በሰላማዊ ሁኔታ በውይይት እና በድርድር እንፈተለን ብሎ የተቀመጠ ነው የኢትዮጵያ መንግስት ፤ አዲስ የመጣ የተከሰተ ነገር የለም " ሲሉ ተናግረዋል።

ነገር ግን የህወሓትን ተልዕኮ ለማስፈፀም እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የነበሩ ሽፍታዎችን ደምስሰናቸዋል ሲሉ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
#ጥንቃቄ

‘ US Embassy Addis Ababa ’ በሚል ስም ከ127 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት የቴሌግራም ቻነል " አሜሪካ ኤምባሲ በጦርነት የተጎዳዉን የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ለመደገፍና ከክፍለዘመን የዘለቀዉን የአሜሪካና የኢትዮጵያን ወዳጅነት ለማጠናከር ለ20 ሺህ ኢትዮጵያዉያን በአሜሪካ የስራ ዕድል ፈጥሯል " ብሎ መረጃ አጋርቷል።

የዕድለኞች የትራንስፖርት ፤ የመኖሪያ ቤትና የመኪና ወጪ በኤምባሲዉ እንደሚሸፈንም ጽፏል።

ስለዚህም የዕድሉ ተጠቃሚ መሆን የሚፈልጉ ኢትዮጵያዉያን በቴሌግራም ቻነሉ አማካኝነት እንዲመዘገቡና ተመዝጋቢዎችም ሙሉ ስማቸዉን፤ ስልክ ቁጥራቸዉን እንዲሁም አድራሻና መሰል ግላዊ መረጃዎቻቸዉን እንዲልኩም ይጠይቃል።

ይህን በተመለከተ በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ እየተሰራጨ ያለድ መረጃ ሀሰተኛ እና ሰዎችን ለማጭበርበር እንደሆነ ገልጿል።

ኤምባሲዉ ለኢትዮጵያ ቼክ የመረጃ አጣሪ ድረገፅ በሰጠው ቃል፤ በአሜሪካ የስራና የቪዛ ዕድሎችን በተመለከተ በተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ገጾች #ሀሰተኛ መረጃዎች እየተጋሩ መሆኑን አስታዉቋል።

" የአሜሪካ መንግስት በኢሜይል፤ ፌስቡክ ሚሴንጀር፤ ቴሌግራም ወይም ሌላ ማህበራዊ ትስስር ገጾች አማካኝነት ግላዊ መረጃዎችን አይጠይቅም " ሲል ኤምባሲው አስረድቷል

ትክክለኛ የስራ ዕድሎችን በድረ-ገጹ ላይ እንደሚለጥፍና ሰዎች ለአጭበርባሪዎች እንዳይጋለጡ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ኤምባሲዉ ጠይቋል።

Via Ethiopia Check

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #Gambella የጋምቤላ ክልል ፤ ጋምቤላ ከተማን ማረጋጋት መቻሉን አሳወቀ። ክልሉ ፥ " ተኩስ ከፍተው በነበሩ የሸኔና የጋምቤላ ነፃነት ግንባር ላይ በፀጥታ አካላት በተወሰደ ጠንካራ እርምጃ ከተማዉን ማረጋጋት ተችሏል " ሲል አሳውቋል። አክሎም በተወሰደዉ እርምጃ በታጣቂ ቡድኑ ላይ ከፍተኛ ሰበአዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሷል ሲል አመልክቷል። ክልሉ የከተማው ህብረተሰብ ከቤት ባለመውጣት ለፀጥታ…
#Update #Gambella

የጋምቤላ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ኡሞድ ኡጁሉ በጋምቤላ ከተማ ተከስቶ የነበረው የፀጥታ ችግር ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር መቻሉን ገለፁ።

ፕሬዝዳንቱ ይህን የገለፁት የከተማውን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው።

" በክልሉ የሚገኙ የፀጥታ ሀይሎች ባካሄዱት ቅንጅታዊ ማጥቃት ከተማውን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር ተችሏል " ያሉት አቶ ኡሞድ " በጥቃቱ በጠላት በኩል ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሷል ፤ ከወገን ጦር በኩልም መጠነኛ ጉዳት ደርሷል " ሲሉ ገልፀዋል።

አቶ ኡሞድ ፤ በጋምቤላ ከተማ በሚገኙ የመንግስት ተቋማት ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱን ገልፀው በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የርዕሰ መስተዳድሩን ጽህፈት ቤት ተቆጣጥረዋል [ ታጣቂዎቹን ማለታቸው ነው ] በሚል የተናፈሰው ወሬ #ሀሰተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ ሊገነዘብ ይገባል ብለዋል።

" ነዋሪዎች በአሁኑ ሰዓት በከተማው በአንዳንድ አካባቢ ተደብቆ የሚገኝ የጠላት ሀይል ካለ በአቅራቢያቸው ለሚገኝ የፀጥታ ሀይል ጥቆማ ይስጡ " ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ህብረተሰቡ አካባቢውን ነቅቶ እንዲጠብቅ በተለይም #ከምሽቱ_2_ሰዓት ጀምሮ በቤቱ በመቀመጥ ለሠላሙ ተባባሪ መሆን ይኖርበታልም ብለዋል።

የጋምቤላ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ኡሞድ ኡጁሉ " በጥቃቱ ህይወታቸውን ላጡና ጉዳት ለደረሰባቸው አካላት በክልሉ መንግስት እና ህዝብ ስም መጽናናትን እመኛለሁ " ማለታቸውን ከክልሉ ፕሬስ ሴክሬተሪያት የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የቤጂንግ እና የዋሽንግቶን ውጥረት ? አሜሪካ እና ቻይናን ውጥረት ውስጥ የከተታቸው የታይዋን ጉዳይ ነው። ቻይና ታይዋን #ወደ_እናት_አገሯ መመለስ ያለባት አፈንጋጭ ግዛቷ እንደሆነች ነው የምታስበው ይህንንም ለማሳካት ወደፊት ቤይጂንግ ኃይል መጠቀምን እንደ አንድ አማራጭ ታየዋለች።  አሜሪካ ደግሞ ከቻይና ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላት ሲሆን፣ ከታይዋን ጋር ግን “ይፋዊ ያልሆ ጠንካራ” ዲፕሎማሲያዊ…
" ሀሰተኛ ዜና ነው " - ታይዋን

የታይዋን መከላከያ የቻይና የጦር ጄቶች PLA Su-35 " የታይዋንን አየር ክልል ጥሰው ገቡ " ተብሎ በኦንላይን ሚዲያዎች የሚሰራጨው መረጃ #ሀሰተኛ_ዜና ነው አለ።

በታይዋን ያለውን ጉዳይ የሚከታተሉ ትክክለኛው የመከላከያ ድረገፅ ብቻ እንዲጠቀሙ መልዕክት አስተለልፏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ነዋሪዎች በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩትን ሀሰተኛ መረጃዎች ለሌሎች እንዳያጋሩ አሳስቦ " ይህን እኩይ ተግባር በጽኑ እናወግዛለን " ብሏል።

CGTNን ጨምሮ ሌሎችም ሚዲያዎች የቻይና Su-35 ተዋጊ ጄቶች " የታይዋንን አየር ክልል ጥሰው ገቡ " ሲሉ ዘገባዎችን አውጥተው ነበር።

ቻይና " ታይዋን " #ወደ_እናት_ሀገሯ መመለስ አለባት ብላ ታምናለች ፤ ታይዋንን የሚደግፉ ሁሉ በሀገር አንድነት ላይ አደጋ ያመጡ አድርጋ ነው የምትወስዳቸው።

ለዛም ነው በአሜሪካ የስልጣን እርከን ሶስተኛዋ ሰው ፔሎሲ ታይዋን መግባታቸው ያስቆጣት እና እርምጃ እንደምትወስድ በተደጋጋሚ እየዛተች የምትገኘው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አንጋፋው የኢትዮጵያ አርቲስት ክቡር ዶ/ር አሊ ቢራ #በህይወት አለ። በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ አንጋፋው የሀገራችን አርቲስት ክቡር ዶክተር አሊ ቢራ " አረፈ / ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ " እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው። ክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ ባጋጠመው የጤና እክል የተነሳ በአዳማ ጄነራል ሆስፒታል ለላፉት ቀናት #የሕክምና_ክትትል እየተደረገለት ይገኛል። የ75 ዓመቱ አርቲስት አሊ…
" መሰል ሀሰተኛ መረጃ ሲነዛ በዚህ ወር ብቻ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው "

ዛሬ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች አንጋፋው የኢትዮጵያ አርቲስት ክቡር ዶ/ር አሊ ቢራ " ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ " እየተባለ ሲናፈስ የነበረው መረጃ #ሀሰተኛ ነው።

በክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ ላይ መሰል ሀሰተኛ መረጃ ሲነዛ በዚህ ወር ብቻ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው።

ከወራት በፊት ተመሳሳይ ሀሰተኛ ወሬ መሰራጨቱ እና ቤተሰቦቹን እጅጉን መጉዳቱና ማሳዘኑ የሚዘናጋ አይደለም።

ክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ ባጋጠመው የጤና እክል የተነሳ በአዳማ ጄነራል ሆስፒታል የሕክምና ክትትል እየተደረገለት ይገኛል።

እንዲህ ያለው ነውር በሀገራችን የማህበራዊ ሚዲያ ላይ እጅግ እየተደጋገመ ሲሆን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች የሚከተሏቸው ትልልቅ የማህበራዊ ሚዲያዎችም ሰለባ እየሆኑ ነው።

አንዳንድ ጊዜ " ፈጥነን መረጃ አደረስን " ለማለት ያህል ፤ እንዲሁም የዩትዩብ ብር ለማግኘት / ላይክ ለመሰብሰብ ሲባል የሰዎችን ህይወት መረበሽ እና መበጥበጥ ከህሊና ያፈነገጠ ተግባር ነው።

@tikvahethiopia
ሀሰተኛ የትምህርት መረጃ ...

(በዳውሮ ዞን)

በዳውሮ ዞን ፤  ከጪ በተባለው ወረዳ ለመጀመሪያ ዙር በተደረገ ማጣራት ከ264 የትምህርት መረጃ 127 #ሀሰተኛ ሆኖ መገኘቱ ተሰምቷል።

ሀሰተኛ ሆኖ ከተገኘው የትምህርት መረጃ መካከል 6ቱ #የአመራርና ቀሪው #የመንግስት_ሰራተኞች ነው።

የሁለተኛ ዙሪ የማጥራት ስራ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

በዚሁ ዞን ፤ ቶጫ በተባለው ወረዳ በመጀመሪያ ዙር ከተደረገው ማጣራት ከ565 የትምህርት መረጃ የ218 ሰዎች #ሀሰተኛ ሆኖ ተገኝቷል።

መረጃቸው ወደ ግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተልኮ ከተጣራው ከ565 የመንግስት ሰራተኞች መካካል የ210 ባለሙያዎችና የ8 #አመራሮች የትምህርት መረጃ ነው ሀሰተኛ ሆኖ የተገኘው።

ይኸው የማጣራት ስራ ይቀጥላል ተብሏል።

መረጃው ከዳውሮ ኮሚኒኬሽን የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 20 ሺህ ሰራተኞችን ሊቀጥር ነው ?

ከሀሰተኛ መረጃ ተጠንቀቁ !

በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በማህበራዊ ትስስር ገፁ 20 ሺህ #ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን መቅጠር እንደሚፈልግ አስታወቀ ፤ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን የሚቀጥረው ትግራይ ፣ አፋር፣ ሶማሌ ክልሎችን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች የቴሌኮም አገልግሎቱን ለማስፋፋት በማቀድ ነው ፤ የስራ ቅጥሩ ዲግሪ አይጠይቅም 10ኛ እና 12ኛ ክፍል ያጠናቀቁ ማመልከት ይችላሉ " እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ፍፁም #ሀሰተኛ መሆኑን ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ገልጾልናል።

ከጥዋት አንስቶ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የተሰራጨውን የ20 ሺህ ሰራተኞች ቅጥር መረጃ በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለሚመለከተው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ክፍል " በየትኛው የማህበራዊ ትስስር ገፃችሁ ላይ ነው ይህ ያሳወቃችሁት ? መረጃው እውነት ከሆነስ በየትኛው መንገድ ነው ማመልከት የሚቻለው ? " ስንል ጥያቄ ያቀረብን ሲሆን መረጃው #ሀሰተኛ ነው የሚል ምላሽ ተሰጥቶናል።

" እኛ 20 ሺህ ሰራተኞች ለመቅጠር በየትኛውም የማህበራዊ ትስስር ገፃችን ላይ ጥሪ አላቀረብንም ፤ መሰል ሀሰተኛ መረጃዎች የሚሰራጩት ሆን ተብሎ ተመሳስለው በተከፈቱ #ሀሰተኛ_ገፆች ነው " ሲል የሚመለከተው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ክፍል ገልጾልናል።

በመሆኑም " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 20 ሺህ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞችን ሊቀጥር ነው " በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው።

@tikvahethiopia
" የትኛው ፖሊስ ጋር ነው ያመለከቱት ? ፌክ ኒውስ በጣም በብዛት እያሰራጩ ነው " - የፌዴራል ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጄይላን አብዲ

በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በታጣቂዎች እገታዎች ተፈፅመው በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እንደሚጠየቅ በተደጋጋሚ መገለፁ ይታወቃል።

በቅርቡ አንድ ሰዓሊ ከጓደኛው ጋር ሶደሬ አካባቢ ከታገተ በኃላ ቤተሰቦቹ ጋር ተደውሎ ገንዘብ ከተጠየቁ በኃላ ለመነጋገር ድጋሚ ሲደውሉ " በእሱ ጉዳይ አትደውሉልን አፈር አልብሰነዋል " የሚል መርዶ ተነግሯቸው ሀዘን ላይ እንደነበሩ ፤ ጓደኛው ግን 500 ሺህ ብር ከፍሎ ከእገታ መውጣቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ማሳወቁ ይታወሳል።

ከዚህ ክስተት በፊትም የሰዴን ሶዶ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ በቀለ ቃቻ ፤ ከመኖሪያ ቤታቸው በታጣቂዎች ታፍነው ከተወሰዱ ከሁለት ቀን በኃላ ተገድለው መገኘታቸውን መግለፃችን ይታወሳል።

እኚህን ባለስልጣን ያገቷቸው ታጣቂዎች 10 ሚሊዮን ብር መጠየቃቸው መነገሩም አይዘነጋም።

ወደ ጎጃም መስመር " ዓሊዶሮ " ላይም 30 ሹፌሮች እና ረዳቶች በታጣቂዎች መታገታቸውን ቤተሰቦቻቸው መግለፃቸው ፤ ከታገቱት ውስጥም 500 ሺህ እና 1 ሚሊዮን ብር ቤተሰቦቻቸው ከፍለው የተለቀቁ ስለመኖራቸው መግለፃችን የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው።

እንደውም ከቀናት በፊት ልጃቸውን ከእገታ ለማስለቀቅ 1 ሚሊዮን ብር የከፈሉ አሳዛኝ መምህር ታሪክ መሰራጨቱ ይታወሳል።

ወራትን ወደኃላ ብንጓዝ በርካቶች እየታገቱ ገንዘብ ተጠይቆባቸው ለአጋቾች ተከፍሎ ተለቀዋል ፤ በርካታ ሚዲያ ላይ ያልቀረቡ መሰል ክስተቶች አሉ።

ከታጋች ቤተሰቦች እንደሚሰማው ጉዳዩን ወደ ፖሊስ ቢወስዱት አጋቾች የያዙትን ሰው ህይወት ያጠፋሉ የሚል ስጋት አለ ፤ ከዛ ውጭ ግን ጉዳዩን ሀገር ያወቀው ፀሀይ የሞቀው ጉዳይ ነው።

ዛሬ በነበረው የፓርላማ ውሎም የምክር ቤት አባላት የእገታ ጉዳይን አንስተው አሳሳቢነቱን ገልጸዋል። ለጠ/ሚኒስትሩም ጥያቄ አቅርበዋል።

ይህንን የእገታ ጉዳይ በተመለከተ ዶቼ ቨለ ሬድዮ አንድ አጭር ዘገባ አሰራጭቶ የተመለከትን ሲሆን በዚሁ ዘገባ ላይ የነዋሪዎች / አሽከርካሪዎች እና የፌዴራል ፖሊስ ቃል ይገኝበታል።

አንድ ቃላቸውን የሰጡ አሽከርካሪ ፤ ጅቡቲ ኮሪደር ላይ እስካሁን ከነበረው አሁን ላይ መሻሻል እንዳለ፤ መንግሥት ከፍተኛ ሰራዊት መድቦ ከወለንጪቲ እስከ መተሃራ በፌዴራል እና መከላከያ የሚጠበቅ ቀጠና መሆኑን ገልጸዋል። አሁን ትልቁ ችግር ያለው ከፍቼ - ጎሃ ፂዮን ያለው ቀጠና ነው ብለዋል።

አንድ የአ/አ ነዋሪ ደግሞ ከእገታ ጋር በተያያዘ 3 ዓይነት ሰዎች አሉ ፤ እራሳቸው ሳይታገቱ " ታግተናል " በሚል ለፖለቲካም ሆነ ለሌላ አላማ የሚጠቀሙ ፣ የገንዘብ ፍላጎት ኖሯቸው የሚንቀሳቀሱ አሉ እነዚህ ገንዘብ ያላቸውን ፣ ቢዝነስ ውስጥ ያሉ ሰዎችን አጥንተው የሚንቀሳቀሱ ናቸው ፤ በረሃ ላይ አሸከርካሪዎችን የሚያግቱም አሉ እነዚህም ገንዘብ ይጠይቃሉ ሲሉ አስረድተዋል።

ልጅም " ታገትኩ " ብሎ አባቱን ገንዘብ የሚያስጠይቅም አለ እውነቱን ለማወቅ አቸጋሪ ጊዜ ነው ነገሩ ሁሉ ውስብስብ ነው ሲሉ አክለዋል።

የፌዴራል ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጄይላን አብዲ ግን የሚሰራጨው #ሀሰተኛ_መረጃ መሆኑን ገልጸው አሽከርካሪዎችም ሆኑ ሌሎች ከታገቱ የት ፖሊስ ጣቢያ ሄደው እንዳመለከቱ መረጃ ሊጣራ ይገባል ብለዋል።

አቶ ጄይላን ፤ " የትኛው ፖሊስ ጋር ነው ያመለከቱት ? ፌክ ኒውስ በጣም በብዛት እያሰራጩ ነው ፤ ፌዴራል ፖሊስ መንገድ ላይ እዛው አመልክተዋል ወይ ? ሆን ተብሎ ፌክኒውስ ሀገሪቱ ላይ ሰላም እንደሌለ ለማስመሰል ፤ፌክኒውስ እየተሰራጨ ነው ያለው ሰው ታግቷል ተብሎ " ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ለጦርነት እየተዘጋጀ ነው ?

" ለጦርነት የሚዘጋጅ ኃይል ሰራዊቱን አይቀንስም ፤ ዝግጅታችን ለሰላም ብቻ ነው " - አቶ ረዳኢ ሓለፎም

" ትግራይ ለጦርነት እየተዘጋጀች ነው " በሚል እየተሰራጩ ያሉ መረጃዎች #ሀሰተኛ ናቸው ሲል ክልሉ ገለጸ።

ከሰሞኑን ክልሉ " ለጦርነት ዝግጅት እያደረገ ነው ፤ በኃይል ተይዘውብኛል የሚላቸውን የክልሉ አካባቢዎች ነፃ ለማድረግ ወደ ኃይል እርምጃ ሊገባ ነው " የሚሉ የተለያዩ መረጃዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ እየተሰራጨ ይገኛል።

" ትግራይ ለጦርነት እየተዘጋጀች ነው " በሚል ስለሚሰራጨው መረጃ የክልሉ ጊዜያዊ መንግሥት ቃል አቀባይ ረዳኢ ሓለፎም " ይህ ውሸት ነው ፤ 24 ሰዓት ሙሉ ክልሉ እየሰራ ያለው ሰላሙን ዘላቂ ለማድረግ ነው ፤ ጉዟችን ሁሉ ለሰላም ነው " ብለዋል።

አቶ ረዳኢ ፤ " ሰላሙ እንዲጠከር ስለምንፈልግ ነው ታጣቂ ኃይሉን እየቀነስን ያለነው ፤ ከአሁን ቀደም ከትግራይ በኩል ማውረድ የነበረብንን ትጥቅ በየጊዜው እያስረከብን መጥተናል በተፈራረምነው የሰላም ስምምነት ከትግራይ የሚጠበቁትን እያደረግን ነው ቀረ የሚባል ነገር ያለ አይመስለኝም ፤ በቀጣይነትም ይህን አጠናክረን ወደ ተሟላ ሰላም ለመሄድ የትግራይ በሮች ክፍት ናቸው " ብለዋል።

" ጊዜያዊ አስተዳደሩ 24 ሰዓት እየሰራ ያለው ሰላሙን ለማፅናት ነው፤ ዘላቂ እንዲሆን ነው " ያሉት አቶ ራዳኢ ፤ " እኛ በራሳችን ማድረግ የሚገባንን እያደረግን ነው በሌላው ወገን ያልተተገበሩ ነገሮች አሉ የአማራ ታጣቂዎች በትግራይ ምድር ላይ ነው ያሉት፣ የሻዕቢያ ሰራዊት አሁንም በትግራይ ነው ያለው ፤ ያ በመሆኑ ተፈናቃዮቻችን አሁንም በስቃይ ነው እየኖሩ ያሉት ስለዚህ ይህ መፈታት አለበት ፤ እነዚህ ኃይሎች መውጣት አለባቸው ተፈናቃዮችም ወደ ቄያቸው መመለስ አለባቸው " ብለዋል።

" ይህ እየሆነ ያለው ግን እኛ ያልፈፀምነው ነገር ስላለ አይደለም የሚጠበቅብንን ሁሉ እያደረግን ነው " ሲሉ አክለዋል።

አቶ ረዳኢ ፤ " ለጦርነት የሚዘጋጅ ኃይል ሰራዊቱን አይቀንስም ፤ በቅርቡ እራሱ ከ50 ሺህ በላይ ሰው Demobilize እያደረግን ያለነው ፤ አጠቃላይ ጉዟችንም ቢሆን የሰላም ነው ፤ ሰላሙ እንዲፀና ነው የምንፈልገው፤ ድሮም ቢሆን እንዳልነው ተገደን የገባንበት እንጂ መርጠን የገባንበት አይደለም ፤ በዚህ የሚመጣው ክስ (ጦርነት ሊጀምሩ ነው) ከተግባራችን ጋር የማይሄድ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

ይህንን እያስወሩ ያሉት " ምኞታቸውን ነው " የሚሉት አቶ ረዳኢ ሓለፎም ፤ " ትግራይ ወደ ሰላም መግባት የለባትም የሚል አቋም የያዙ አካላትና ኃይሎች ናቸው ሰላሟን እንዲታወክ ስለሚፈልጉ ሆን ብለው በየቀኑ አጀንዳ ያመጣሉ " ሲሉ ወቅሰዋል።

" ከጦርነት በፊትም ኮሽ ባለ ቁጥር የወያኔ እጅ አለበት ፤ የትግራይ እጅ አለበት ፣ ሶስተኛ ወገን አለበት እያሉ ነበር ህዝቡን ሲያጦዙት የነበረው ፤ በሌለ ነገር አዲስ ስሜት ፈጥረው ቀስቅሰው በትግራይ ተወላጆች ላይ ታሪክ ይቅር የማይለውን ስህተት እና ክህደት የፈፀሙት ፤ አሁንም ይህን የማስቀጠል ነገር ነው ዓላማቸው ፤ በትግራይ በኩል ለጦርነት የሚዘጋጅበት ምንም ነገር የለም ፤ እየተዘጋጀ አይደለም ፤ የትግራይ ህዝብም መስተዳደርም ዝግጅቱ ለሰላም ብቻ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
ጅግጅጋ የሆነው ምንድነው ?

ከሰሞኑን በጅግጅጋ ከተማ እጅግ አሰቃቂ የተባለ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ተፈፅሟል።

የአስገድዶ መድፈር ወንጀሉ የተፈፀመባት የ9 ዓመት ህፃን ልጅ ስትሆን ይህ ድርጊት ከተፈፀመባት በኃላ የድርጊቱ ፈፃሚዎች የደፈሯትን ልጅ ገድለዋታል።

ከዚህ አሰቃቂ ድርጊት በኃላ ወንጀሉን የፈፀሙ 4 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ሊውሉ እንደቻሉ ተገልጿል።

ነገር ግን ከዚህ የወንጀል ድርጊት ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪዎችን በመያዙ ሂደት ላይ ሰዎችን ለይቶ በአፈሳ የማሰር ድርጊት እንደነበር ቃላቸውን የሰጡ የጅግጅጋ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

አንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የጅግጅጋ ነዋሪ በሰጡት ቃል ፤ ከህፃኗ መደፈር ድርጊት ጋር በተያያዘ ሰኞ 4 ተጠርጣሪዎች ቢያዙም በከተማው ሰፊ አፈሳ ሲደረግ ነበር ብለዋል።

በተለይም ከደቡብ አካባቢ የመጡ ልጆች በድርጊቱ ላይ በመጠርጠራቸው ይህን መሰረት ያደረገ እስር ሲፈፀም እንደነበር ገልጸዋል። ድርጊቱ እስከ ትላንት ድረስ መቀጠሉን ጠቁመዋል።

አንድ ሌላ ነዋሪ ድርጊቱ እጅግ በጣም አሰቃቂና አስደንጋጭ እንደነበር ገልጸው ከተጠርጣሪዎች አያያዝ ጋር በተያያዘ በፀጥታ ኃይሎች የተፈፀመው ድርጊት ተገቢ አይደለም ብለዋል።

" ተጠርጣሪዎችን በልዩነት ማሰር እየተቻለ ሰዎች በአፈሳ ወደ ማቆያ ሲገቡ ነበር ይህ ተገቢ ያልሆነ አካሄድ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

ሌላ አንድ ነዋሪ ደግሞ ፤ " እሁድ እለት አንድ ልጅ ተደፈራ ከተገደለች በኃላ ድርጊቱን የፈፀሙ ግለሰቦች ተይዘው ለህግ ቀርበዋል " ብለዋል።

" ይሄ ጥሩ ነው " ያሉት እኚሁ ነዋሪ ነገር ግን ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት የለላቸውን ሰዎች ፓሊስ በጅምላ በማፈስ ማሰረሱን ፣እና መደብደቡን ጠቁመዋል።

በነበረው ሁኔታ የሰዎች ህይወት ማለፉን እንደሰሙ ገልጸዋል።

በተለይ ከደቡብ የመጡ ወጣቶችን መታወቅያ በማየት እስር ፣ ድብደባ ሲፈፀም ነበር ይህን የሚመለከተው አካል ይወቀው ሲሉ ገልጸዋል።

የሶማሌ ክልል መንግሥት ግን ከአሰቃቂው የወንጀል ድርጊት በኃላ ተፈፅሟል የተባለው ድርጊት #አሉባልታ እና #ሀሰተኛ ነው ብሏል።

የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አብድቃድር ረሽድ ፤ " በሱማሌ ክልል የሌላ ክልል ተወላጆች እየታፈሡ እየታሰሩ ፣እየተገደሉ ነው በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው አሉባልታ ወሬ ነው " ያሉ ሲሆን የሚንገረው ሁሉ ውሸት ነው ብለዋል።

" የሶማሌ ህዝብ ሰፊ ህዝብ ነው አቃፊ ነው ፣ ከየትኛውም ህዝብ ጋር የመኖር ባህል ያለው ማህበረሰብ ነው ፤ የሌላ ኢትዮጵያዊ ተወላጅ የማሳደድ፣ የመግደል ባህል ፈፅሞ የለውም የሚነገረው ሁሉ ውሸት ነው፤ የሶማሌ ህዝብን ስም ለማንቋሸሽ የሚሰራ ፕሮፖጋንዳ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

" የህግ አካላት ቦታው ላይ ሳይደርሱ ሁከት ለመፍጠር ሙከራ ተደርጎ ነበር " ያሉት ኃላፊው የህግ አካላት የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ የወሰዱት እርምጃዎች ነበሩ ብለዋል።

" እነዛም መቆያ አካባቢዎች ለደህንነታቸው ስጋት የቆዩ አካላት በማጣራት ወደመደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ ትላንት በፀጥታ አካላት መመሪያ ተሰጥቷል። " ሲሉ ተናግረዋል።

" በሶማሌ ክልል ምንም ችግር የለም ሰላም ነው ፤ የሶማሌ ህዝብ አቃፊ ነው " ያሉት ኃላፊው የፖለቲካ አጀንዳ በማድረግ ተቃውሞ በመፍጠር ብጥብጥ ለመፍጠር ፣ በክስተቶች ላይ ክስተት በማጋነን ፣ እከሌ ተገደለ፣ እከሌ ዘሩ እንዲህ ነው በማለት ለፖለቲካ የሚጠቀሙ ኃይሎች አሉ " ብለዋል።

" የሶማሌ ክልል ሰላም ነው ፤ ሁሉም ወደ መደበኛው ስራ ተመልሷል " ሲሉ አክለዋል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የተሽከርካሪዎች_ጨረታ_ጉምሩክ_ኮሚሽን_አዳማ_.pdf
ውዝግብ የፈጠረው የበርካታ ተሽከርካሪዎች ጨረታ !

" ' የጉምሩክ ኮሚሽን ' የገንዘብ ሚኒስቴርን ውሳኔ በመጣስ 237 መኪኖችን ለሐራጅ አወጣብን " - ከሰደት ተመላሾችና 10 የሚደርሱ የአገር ውስጥ አስመጪዎች

" በግልፅ ጨረታ ለሽያጭ የቀረቡት ተሽከርካሪዎች ህጋዊ ስርዓቱን በአግባቡ በተከተለ መልኩ ነው። ' ህጋዊ ስርዓቱን አልተከተለም ' በሚል የሚሰራጩት መረጃዎች ሀሰተኛ ናቸው ፤ #ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ አካላትን በህግ አግባብ እንጠይቃለን " - ጉምሩክ ኮሚሽን

ከሰሞኑን የአዳማ ጉምሩክ ኮሚሽን ፅ/ቤት ያወጣው የበርካታ ተሽከርካሪዎች ጨረታ ውዝግብ የፈጠረ ሆኗል።

በዚህ ጉዳይ ላይ ቅሬታ አለን ያሉ ከሰደት ተመላሾችና የአገር ውስጥ አስመጪዎች ፤ " ጉምሩክ ኮሚሽን የገንዘብ ሚኒስቴር ውሳኔን በመጣስ 237 ተሽከርካሪዎች ለሐራጅ አወጣብን " በሚል ከሰዋል።

ጉምሩክ ኮሚሽን በበኩሉ ፤ " ምንም አይነት የህግ ጥሰት አልፈተፈፀም ህጉን እና አሰራሩን በተከተለ መልኩ ነው ተሽከርካሪዎቹ ለጨረታ የቀረቡት " ሲል አሳውቋል።

ያንብቡ 👇 https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-11-24

@tikvahethiopia