TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Ethiopia🇪🇹 vs #SouthAfrica🇿🇦

ነገ የሀገራችን ኢትዮጵያ 🇪🇹 ብሄራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ከደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን ጋር ይፋለማል።

ጨዋታው በውቢቷ ባህርዳር ከተማ ነው የሚካሄደው።

ለዚሁ ጨዋታ የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን አባላት ዛሬ 28/01/2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ሲል ባህርዳር ደርሰዋል።

የሀገራችን ብሄራዊ ቡድን አባላት ዛሬ ከረፋዱ 3:30 ጀምሮ የመጨረሻ ልምምድ በባህር ዳር አለም አቀፍ ስታዲየም አድርገዋል።

ከነገው ጨዋታ ጋር በተያያዘ የብሄራዊ ቡድናችን አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ዛሬ አመሻሽ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሠጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

በቲክቫህ ኢትዮጵያ (ስፖርት) በኩል ደግሞ ተጨማሪ መረጃዎች ማግኘት ትችላላችሁ : https://publielectoral.lat/joinchat/VvwzStMNcNHmhK0x

#ምንጊዜም_ኢትዮጵያ❤️

@tikvahethsport @tikvahethiopia
የድሬዳዋ አስተዳደር ለነዋሪዎች ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።

በድሬዳዋ ዴልታ በመባል የሚታወቀውና በዓለማችን ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ያለው የኮቪድ ዝርያ እንዲሁም ደንጊ ፣ ቺክንጉኒያ እና ወባ #አሳሳቢ በሚባል ደረጃ በመከሰቱ ነዋሪዎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የከተማው አስተዳደር አስጠንቅቋል።

ከዚህ ተደራራቢ ችግር ሊወጣ የሚቻለው ማህበረሰቡ አሁን ያለንበትን ሁኔታ ተረድቶ እንደ አንድ በመሆን እርምጃዎች ሲወስድ ብቻ ነው ብሏል አስተዳደሩ።

ማህበረሰቡ ሊወስድ ይገባቸዋል ያላቸው እርምጃዎችም ፦

1ኛ. ሁሉም ሰው ከቤት ውጪ ሲንቀቀስ የአፍን እና አፍንጫ መሸፈኛ (ማስክ) ማድረግ ፣ አካላዊ እርቀትን መጠበቅና የእጆችን ንፅህና መጠበቅ።

2ኛ. ዘወትር አካባቢን ማጽዳት፣ ንፅህናዉን በሚገባ መጠበቅና ውሃ ያቆሩ ቦታዎችን ማፍሰስ።

3ኛ. ከትንኝ ንድፊያ የሚመጡ በሽታዎችን ለመከላከል በጸረ ትንኝ መድሃኒት የተነከሩ አጎበሮችን መጠቀም የሚሉት ናቸው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING የዘንድሮው የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) ሆኗል። #NobelPeacePrize2020 @tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize2021

የዘንድሮው የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊዎች ታወቁ።

የፊሊፒንስ ጋዜጠኛዋ ማሪያ ሪሳ እና ሩስያዊው ጋዜጠኛ ዲሚትሪ ሙራቶቭ የዘንድሮው የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊዎች መሆናቸውን የሽልማት ኮሚቴው ከደቂቃዎች በፊት አስታውቋል።

የሽልማት ኮሚቴው ጋዜጠኞቹ ሽልማቱን ያገኙት "የመናገር ነፃነት እንዲከበር ላረጉት አስተዋፅኦ" እንደሆነ አስታውቋል። ኮሚቴው አክሎም "የመናገር ነፃነት ለዴሞክራሲ እና ለዘላቂ ሰላም ወሳኝ ነው" ብሏል።

ማሪያ ራፕለር የተባለው ሚድያ ስራ አስኪያጅ ስትሆን ዲሚትሪ ደግሞ ኖቫያ ጋዜቴ የተባለ የሩስያ ጋዜጣ አርታኢ ነው። ሁለቱም ከሽልማቱ ጋር የ1.1 ሚልዮን ዶላር ሽልማት ያገኛሉ።

ሽልማቱን አምና የአለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) እንዲሁም ካቻምና ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ማግኘታቸው ይታወሳል።

Credit : Journalist Elias Mesert

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#SemiraMohammed ከሰሞኑን በአንድ ቪድዮ ላይ ልጇ ፊት በፖሊስ አባላት ስትደበብ የተመለከትናት ሰሚራ መሐመድ የስራ ዕድል እንደተፈጠረላት ከንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ተሰምቷል። ግለሰቧ በልመና ላይ ተሰማርታ በነበረበት ወቅት በፖሊስ አባላት በርካቶችን ያስቆጣ ኢሰብዓዊ ድርጊት ከተፈፀመባት በኃላ የከተማ አስተዳደሩ በከንቲባ አዳነች አቤቤ አማካኝነት ለግለሰቧ የስራ እድል እንደሚመቻች አሳውቆ…
ሰሚራ መሀመድ መኖሪያ ቤት ተሰጣት።

በፖሊስ አባላት ድብደባ የተፈፀመባት ሰሚራ መሀመድ ከቀናት በፊት በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የስራ ዕድል እንደተፈጠረላት ይታወሳል።

በዛሬው ዕለት ደግሞ የመኖሪያ ቤት ተሰጥቷታል።

ሰሚራ መሀመድ ቤተሰቦች፤ አመራሮችና የአስተዳደር ሰራተኞች በተገኙበት የቁልፍ ርክክብ ስነስርዓት ተከናውኗል።

የመኖሪያ ቤት ቁልፋን በስፍራው በመገኘት ያስረከቡት የንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ነጻነት ዳባ ሲሆኑ ፤ አስተዳደሩ ለሰሚራ የሚያደርገውን ሁሉን አቀፍ ድጋፍ አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ምንጭ፦ የአ/አ ፕሬስ ሴክሬተሪያት

@tikvahethiopia
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የ "እንኳን ደስ አለዎት! " መልዕክት አስተላለፉ።

ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቱን ዶ/ር አቢይ አህመድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው መሰየማቸውን ተከትሎ የ "እንኳን ደስ አለዎት" ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው ፥ የሩሲያ እና የኢትዮጵያ ግንኙነት በመልካም የወዳጅነት እና እርስ በርስ መከባበር ላይ የተመሠረተ ነው ብለዋል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ በቀጣይም ለኢትዮጵያ የሚያደርጉት አስተዋጽኦ የበለጠ እንደሚጨምር "አምናለሁ" ሲሉ ገልፀዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም የሩሲያ እና ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ትብብርን በተለያዩ ዘርፎች በማዳበር "ለህዝቦቻችን" ጥቅም እንሰራለን ብለዋል።

ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ባስተላለፉት መልዕክት ለጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ መልካም እና ስኬታማ የስራ ዘመን ተመኝተዋል።

Credit : Russia in Ethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ሹመታቸው የፀደቀላቸው የካቢኔ አባላት በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈፅመዋል። አዲስ የተሾሙት ሚኒስትሮች ዝርዝር ፦ 1. አቶ ደመቀ መኮንን - የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር 2. ዶ/ር አብርሃም በላይ - የሃገር መከላከያ ሚኒስትር 3. አቶ አህመድ ሽዴ - የገንዘብ ሚኒስትር 4. ወ/ሮ ሙፈሪያት ካሚል - የስራና ክህሎት ሚኒስትር 5. አቶ ኡመር…
አቶ ቀጀላ መርዳሳ የሥራ ርክክብ አደረጉ፡፡

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት አቶ ቀጀላ መርዳሳ ከቀድሞው የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ጋር የሥራ ርክክብ አድርገዋል፡፡

ለአዲሱ ሚኒስትርም የቀድሞዋ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር የነበሩት ዶ.ር ኂሩት ካሳው እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

በርክክቡ ወቅትም ለሚኒስትሩ ስለ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አደረጃጀትና እየተሠሩ ስላሉ ሥራዎች እንዲሁም ለወደፊት የታቀዱ እቅዶች በዶ.ር ኂሩት ካሳው ማብራሪያ ተደርጎላቸዋል፡፡

አቶ ቀጀላ መርዳሳ ፥ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሆነው በመመደባቸው የተሰማቸውን ደስታ የገለፁ ሲሆን የኢትዮጵያን ገፅታ ሊቀይር የሚችል ሥራን ለመሥራት የተጣለባቸውን ሀገራዊ ኃላፊነት ካለው አመራርና ሠራተኛ ጋር በመወያየት እንደሚወጡ ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ ፥ የሚኒስቴሩ አመራሮች ላደረጉላቸው አቀባበል አመስግነዋል፡፡

ምንጭ፦ ባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
" ባንክ ኦፍ አዲስ / Bank of Addis "

በ10 ቢሊዮን ብር በተመዘገበ ካፒታል አዲስ ብድርና ቁጠባ ተቋም ወደ ባንክ ማደጉ ተገለፀ።

አዲስ ብድር እና ቁጠባ ተቋም በ3.7 ቢሊዮን የተከፈለ እና በ10 ቢሊዮን ብር በተመዘገበ ካፒታል " ባንክ ኦፍ አዲስ " በሚል ወደ ባንክ ማደጉን የተቋሙ ማኔጅንግ ዳይሬክተር አቶ ዳምጠው አለማየሁ አስታውቀዋል።

የተቋሙ አመራሮችና ባለአክሲዮኖች ትላንት ጉባኤ ያካሄዱ ሲሆን የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት በማድረግ ወደ ባንክ እንዲሸጋገር መወሰናቸው ተገልጿል።

ወደ ባንክ የተሸጋገረው ተቋሙ ከሌሎች ባንኮች በተለየ ሁኔታ ጣምራ አገልግሎትን ለህብረተሰቡ ለመስጠት ያስችላል ተብሏል።

የአዲስ ብድር እና ቁጠባ ተቋም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ከመደበኛ ባንኮች የፋይናንስ አገልግሎት ማግኘት ለማይችሉ የህብረተሰብ ክፍሎች አዲስ አበባ ከተማ የስራ እድል ፈጠራ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ተብሎ በ1988 ዓ.ም በ5 አክሲዮኖች በ517 ሺህ ብር የተከፈለ ካፒታል እና ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ በተመዘገበ ካፒታል ነበር የተመሰረተው።

Credit : AAPS

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የስራ ርክክብ አደረጉ፡፡ በአዲሱ የመንግስት ምስረታ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ሆነው የተሾሙት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከቀድሞ የትምህርት ሚኒስትር ጋር የስራ ርክክብ አድርገዋል፡፡ ለአዲሱ ሚኒስትር የቀድሞ የትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን መኩሪያ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡ በርክክቡ ወቅትም…
የትምህርት ሚኒስትሩ ከሰራተኞች ጋር ውይይት አካሄዱ።

በዛሬው ዕለት የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከሚኒስቴሩ አጠቃላይ ሰራተኞች ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተገልጿል።

ውይይቱ በቀጣይ በትኩረት ሊሰሩ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር ተብሏል።

ሰራተኞቹ በትምህርት ሚኒስቴር ውስጥ አሉ ያለቱን የአሰራር ፣ የመልካም አስተዳደር እና የአደረጃጀት ችግሮች ለሚኒስትሩ አሳውቀዋል።

በቀጣይም ሚኒስትሩ በተቋም ውስጥ ያሉትን ችግሮች በመፈተሽ መፍትሄ የመስጠት እና የትምህርት ሴክተሩን ከፓለቲካ እና ከንግድ ነፃ ለማድረግ ሊሰሩ እንደሚገባ ሰራተኞቹ ገልፀዋል።

ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ፥ በሰራተኞች የተነሱትን ሀሳቦች እንደ ግብዓት በመውሰድ እና መፍትሄ በመስጠት በቅንጅት የተሻለ ስራዎችን ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ፥ " የትምህርት ሴክተሩ የፓለቲካ መስሪያ ቤት ሳይሆን ህዝብን ለማገልገል የተቋቋመ ሴክተር በመሆኑ የፓሊቲካ አመለካከታችንን ትተን ስራዎች ላይ ትኩረት ማድረግ ይገባል " ሲሉ ተናግረዋል።

አክለውም፥ "ሚኒስቴሩ የተሻለ ትውልድ ለመፍጠር ከፍተኛ ሀላፊነት ያለበት ተቋም በመሆኑ የተሻለ ስራ መስራት ይጠበቅበታል " ብለዋል።

መረጃው ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
ሹመት !

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በዛሬው ዕለት አቶ አብርሃም አለኸኝን በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ዘርፍ አስተባባሪ አድርገው ሾመዋቸዋል።

#PMOEthiopia

@tikvahethiopia
የጥቅምት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ የመሸጫ ዋጋ በመስከረም ወር ሲሸጥበት በነበረው ዋጋ እንዲቀጥል ንግድና ኢዱስትሪ ሚኒስቴር አሳውቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የ "እንኳን ደስ አለዎት! " መልዕክት አስተላለፉ። ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቱን ዶ/ር አቢይ አህመድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው መሰየማቸውን ተከትሎ የ "እንኳን ደስ አለዎት" ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል። ፕሬዝዳንቱ በመልዕክታቸው ፥ የሩሲያ እና የኢትዮጵያ ግንኙነት በመልካም የወዳጅነት እና እርስ በርስ መከባበር ላይ የተመሠረተ…
#DrAbiyAhmed

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለቀጣይ 5 ዓመታት ኢትዮጵያን እንዲመሩ ከተሾሙ በኃላ የተለያዩ ሀገራት የደስታ መግለጫ እያስተላለፉ ይገኛሉ።

ኬንያ፣ ሱማሊያ ፣ ዩጋንዳ፣ ደ/ሱዳን፣ ጁቡቲ ፣ ናይጄሪያ፣ ሴኔጋል ፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፣ አልጄሪያ መሪዎቻቸው እና ከፍተኛ ባለስልጣኖቻቸው እዚህ ኢትዮጵያ ተገኝተው መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል።

የኤርትራ በፕሬዘዳንቷ ፣ የዩኤኢ መሪዎች ፣ ቬትናምም በጠቅለይ ሚኒስትሯ የመልካም ምኞት መግለጫቸውን የላኩ ሲሆን ዛሬም ሩሲያ በፕሬዜዳንቷ ለ5 ዓመታት የኢትዮጵያ መሪ እንዲሆኑ ለተሾሙት ዶ/ር ዐቢይ "እንኳን ደስ አልዎት" መልዕክት ልካለች።

ማምሻውን ደግሞ የኳታር አሚር ሼክ ታሚም ቢን ሃማድ አልታኒ ጨምሮ የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት የእንኳን ደስ አልዎት መልዕክት አስተላልፈዋል።

@tikvahethiopia