TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የተስተካከለ

የHIV/AIDS ስርጭርት መጠን አሁንም አልቀነሰም!

በደቡብ ክልል የኤች አይ ቪ አድስ ስርጭርትን መቀነስ አልተቻለም፡፡ የበሽታው ስርጭት በከፍተኛ መጠን ከሚታይባቸው የአገሪቱ አካባቢዎች አንዱ የሆነው የደቡብ ክልል የቫይረሱ ስርጭት መጠን ለመቀነስ የተለያዩ ስራዎችን ቢሰራም የስርጭት መጠኑን መቀነስ እንዳልተቻለ የክልሉ ጤና ቢሮ ተናግሯል፡፡

የክልሉ ጤና ቢሮ የፕላንና ፕሮግራም ዳሬክተር አቶ ፍስሃ ለዕመንጎ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት በክልሉ የነበረው የሰላም መደፍረስም ለቫይረሱ ስርጭት በተወሰኑ ቦታዎች ላይ እንዲያንሰራራ ምክንያት ሆኗል ነው ያሉት፡፡

ከ2011 ዓመታዊ ሪፖርት ስንመለከትም የስርጭት መጠኑ 4% ወይም ከመቶ ሰዎች ውስጥ አራቱ ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል።

ከዚህ ወስጥ የወንዶች የስርጭት መጠን 0.17 በመቶ፤ የሴቶች 0.25 በመቶ ሆኖ መመዝገቡን አቶ ፍስሐ ተናግረዋል፡፡ ምንም አንኳን የክልሉ ኤች አይ ቪ አድስ የስርጭት መጠን 0.4 በመቶ ቢሆንም በክልሉ በሚገኙ እንደንድ አከባቢዎች ላይ የስርጭት መጠኑ ወደ 1.9 በመቶ ከፍ ማለቱ ተነግሯል፡፡

የክልሉ ርእሰ መዲና በሆነችው #ሃዋሳን ጨምሮ በክልሉ የተለያዩ አካበቢዎች ታላላቅ ፕሮጀክቶች በሚካሄድባቸው ፋብሪካዎችና ከኢንዱስትሪ ፓርኮች መስፋፋት ጋር ተያይዞ የበሽታው ተጋላጭነት #እየሰፋ መምጣቱን ይናገራሉ፡፡

Via #ኢትዮኤፍኤም

🏷ማስተካከያውን ለTIKVAH-ETHIOPIA የሰጡት የክልሉ ጤና ቢሮ የፕላንና ፕሮግራም ዳሬክተር አቶ #ፍስሃ_ለዕመንጎ ናቸው። ለኢትዮኤፍኤምም ማስተካከያውን ይድረስ ተብለናል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአ/አ የሁለት ሰው ህይወት አለፈ!

አዲስ አበባ በፌደራል ፖሊስ አባላት መካከል በተፈጠረ አለመግባባት የ2 ሰዎች ህይወት አለፈ። የፌደራል ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ጀይላን አብዲ እንደነገሩን ከሆነ ዛሬ ረፋድ ላይ በፌደራል ፖሊስ ከሚጠበቁ ተቋማት መካከል አንዱ በሆነው የፌደራል ማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ ግቢ ውስጥ በተፈጠረ አለመግባባት የ2 ሰው ህይወት አልፏል።

ክስተቱ የተፈጠረው ኤጀንሲውን ከሚጠብቁ የፖሊስ አባላት መካከል አንዱ ለተመሳሳይ #ጥበቃ ስራ ወደ ሌላ ተቋም መቀየሩ የተነገረው የፌደራል ፖሊስ አባል እና በሃላፊው የተሰጠውን ትዕዛዝ ባለመቀበል ምክንያት የተጀመረ ውይይት ወደ አለመግባባት አምርቶ ፖሊሱ የስራ ሃላፊውንና በስራ ላይ በነበረ አንድ አባል ላይ ግድያ መፈጸሙ ተገልጿል። ድርጊቱን የፈጸመው የፌደራል ፖሊስ በህግ ቁጥጥር ስር መዋሉን አቶ ጄይላን ተናግረዋል።

Via #ኢትዮኤፍኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"መረጃው ሀሰት ነው" የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር

የቀድሞው የሶማሌ ክልል ፕሬዘዳንትን #ለማስመለጥ የሞከሩ ሰዎች ተያዙ ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ሃሰት መሆኑን የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር አስታወቀ።

በፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር የህዝብ ግንኙነት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ገረመው አያሌው እንዳሉት ዘገባው ትክክል እንዳልሆነ ተናግረዋል። አቶ ገረመው የተፈጠረውን ነገር እንዲህ ሲሉ አስረድተዋል፦

"ባሳለፍነው ሰኞ እለት የአዲስ አበባ ፖሊስ በአካባቢው በወንጀል የሚፈልገውን አንድ ተጠርጣሪ ለመያዝ ባደረገው ጥረት በስፍራው ተጠርጣሪው እጅ ላለመስጠት ሽጉጥ ወደ ፖሊሶቹ በመተኮሱ ምክንያት የተፈጠረ ግርግር ነበር እንጂ ከቀድሞው የሶማሊ ክልል ፕሬዘዳንት መሃመድ ኡመር ጉዳይ ጋር አይገናኝም" ብለዋል።

ምንጭ፦ #ኢትዮኤፍኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዛሬ ወይም ነገ ከሰዓት ይለቀቃል!

የ12ኛ ክፍል #መልቀቂያ ወይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ፈተና ውጤት ዛሬ ወይም ነገ ከሰዓት በኋላ ይፋ እንደሚሆን ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አስታውቋል። የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ አርአያ ገብረእግዚያብሄር ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት ፈተናዎቹ ዓለም አቀፍ ተወዳሪነታቸው በተመሰከረላቸው ዘመናዊ አዳዲስ የማረሚያ ማሽኖችን በመጠቀም በጥራት የታረሙ መሆናቸውም ተነግሯል። ይሁንና በማህበራዊ ብዙሃን መገናኛዎች የ12ኛ ከፍል ውጤት ተለቋል ተብሎ የሚናፈሰው መረጃ ሃሰት ነው ብለዋል። የእርማቱ ስራ የተጠነቀቀቀ በመሆኑ ኤጀንሲው ዛሬ ወይም ነገ በኤጀንሲው ድረ-ገጽ በመግባት ተማሪዎች ውጤቶቻቸውን ማየት እንደሚችሉ ተገልጿል።

Via #ኢትዮኤፍኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አረርቲ

በ50 ሚሊዮን ዶላር የተገነባዉ #አረርቲ_የሴራሚክስ ፋብሪካ ምርቱን ለገበያ ማቅረብ ጀመረ። በግዙፋ የቻይና የኮንስትራክሽን ኩባንያ ሲሲ-ሲሲ የተገነባዉ የሴራሚክስ ፋብሪካ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ምንጃር ሸንኮራ አረርቲ ከተማ የተገነባ ሲሆን፤ ግንባታዉም ሁለት አመታትን ወስዷል፡፡

ምንጭ፦ #ኢትዮኤፍኤም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አቶ ዮሃንስ ቧያለው ሹመቱን አልቀበልም ብለዋል!

አቶ ዮሃንስ ቧያለው የመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ ፕሬዘዳንትነት ሹመትን እንደማይቀበሉት አስታወቁ።

የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽህፈት ቤት በትናንትነው ዕለት አቶ ዮሃንስ ቧያለውን የመለስ ስራ አመራር አካዳሚ ፕሬዘዳንት እንዲሆኑ መሾሙ ይታወሳል።

ይሁንና አቶ ዮሃንስ ከአማራ መገናኛ ብዙሃን ድርጅት ጋር ባደረጉት ቆይታ ሹመቱን እንደማይቀበሉት አስታውቀዋል።

#ኢትዮኤፍኤም #አብመድ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UPDATE ዛሬ ክሳቸው ከተቋረጠላቸው 63 ግለሰቦች መካከል የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊው ክርስቲያን ታደለ፤ ኮሎኔል ቢኒያም ተወልደ እና ኤርሚያስ ጠቅል አመልጋ ይገኙበታል፡፡ [አሐዱ ቴሌቪዥን] @tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኤርሚያስ አመልጋ ከእስር አልተፈቱም!

[ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8]

መንግስት ክሳቸው አንዲቋረጥ ካደረገላቸው 63 ተከሳሾች ውስጥ እስካሁን ያልተፈታው ኤርሚያስ አመልጋ ብቻ መሆኑ ተገለጸ።

ክሳቸው ከተቋረጠላቸው ሰዎች ውስጥ እስካሁን 62ቱ ከእስር መለቀቃቸውን የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 አስታውቋል። ኤርሚያስ አመልጋ ምህረት ከተደረገላቸው ሰዎች መካከል አንዱ ቢሆኑም እስካሁን ከእስር አልተፈቱም።

ያልተፈቱበት ምክንያት ደግሞ የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ ለቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ኤርሚያስ አመልጋ ከአስር እንዲፈቱ ደብዳቤ ባለመጻፉ ምክንያት መሆኑን በፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ገረመው አያሌው ተናግረዋል።

የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ዝናቡ ቱኑ በበኩላቸው የአቶ ኤርሚያስ አመልጋ ጉዳይ በመንግስት በኩል ለውጥ የለም፣ ይፈታሉ ብሏል ደብዳቤውም ለማረሚያ ቤቱ ይላካል እስካሁንም የዘገየው የሚጣሩ ጉዳዮች ስላሉ ብቻ ነው እንጂ መፈታታቸው አይቀርም ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

#ኢትዮኤፍኤም #ሳሙኤልአባተ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ItsMyDam #NAMA #GERD

ታላቁ የህዳሴ ግድብ የዓለም አቀፍ ድጋፍ እና እርዳታን ለማግኘት ማስያዣ መሆን እንደሌለበት አብን አስታወቀ።

የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አብን የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ጣሂር መሃመድ ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 እንዳሉት ግብጽ እስካሁንም የ1929ኙና የ1959ኙ ኢትዮጵያን ያገለለዉ ስምምነት እንዲመለስ ነዉ የምትፈልገዉ ያሉ ሲሆን የኢትዮጵያ መንግስት ጠንካራ አቋም ሊኖረዉ ይገባል ብለዋል።

ይህ የሉዓላዊነት ጉዳይ በመሆኑ መንግስት ከህዝቡ ጋር መምከርና ቀደም ሲል በነበረበት አቋም ጸንቶ ነዉ መቀጠል ያለበት ብለዋል፡፡

ንቅናቄዉ አሁን ላይ በተለይም ከአረቡ ዓለም ጋር መስመር የሳቱ የሚመስሉ ግንኙነቶች አሉ ብሎ እንደሚያምን ገልጾ በፖለቲካ ዓለም ዉስጥ ፍጹም ታማኝ ወዳጅ ባለመኖሩ ግንኙነታችን ግልጽ መስመር ሊኖረዉ ይገባል ብሏል፡፡

#ኢትዮኤፍኤም #ሙሉቀንአሰፋ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

ኬኒያ ከሰሜን ጣሊያን ወደ ሃገሯ የሚደረጉ በረራዎችን አገደች፡፡ የሃገሪቷ ባለስልጣናት ዛሬ እንዳስታወቁት በጣሊያን በተለይም ሰሜናዊ የሃገሪቷ ክፍል ቬሮና እና ሚላን እየጨመረ በመጣው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት ምክንያት በረራዎችን አግዳለች፡፡

ውሳኔው የተላለፈው በኬኒያ የጣሊያን ኤምባሲ የሰጠውን የአደጋ ጊዜ ማስጠንቀቂያ ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል፡፡ ኬኒያ ወረርሽኙ አሳሳቢ ወደሆነባቸው ሃገራት የምታደርገውን በረራ ከማቋረጥ በተጨማሪ ከጣሊያን፣ደቡብ ኮሪያና ኢራን ወደ ሃገሯ የሚገቡ ሰዎችን ለ14 ቀናት በለይቶ ማከሚያ ክፍል ውስጥ እንዲቆዩ እያደረገች መሆኑን ሲጂቲኤን ዘግቧል፡፡

#ኢትዮኤፍኤም #አባይነሽሽባባው
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባ!

በነገራችን ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በነገው ዕለት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባ ያካሂዳል።

ምክር ቤቱ ከሚወያይባቸው አጀንዳዎች መካከልም በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ አቅራቢነት የሚኒስትሮች ሹመት አንዱ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወይም የመንግስት ተጠሪ ለምክር ቤቱ የጎደሉ ሚኒስትሮች ሹመትን እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።

ለምክር ቤቱ ከሚቀርቡ ሹመቶች መካከል የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፣የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ እና የሌሎች ተቋማት ሹመቶች ዋነኞቹ ናቸው።

#ኢትዮኤፍኤም #ሳሙኤልአባተ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#PressBriefing

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር ፤ በመግለጫቸው ያነሷቸው ነጥቦች እና ተጠይቀው ከመለሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ጥቂቶቹ ፦

- በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ተፈጸሙ በተባሉ ጥሰቶች ላይ ተመድ [UN] ሊያደርገው ያቀደው ተጨማሪ ምርመራ ተቀባይነት የለውም ብለዋል። በኢሰማኮ እና በተመድ የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር የጋራ ሪፖርት ላይ የተመላከቱ ምክረ ሀሳቦችን ለመተግበር መንግስት ዝግጁ ነው ብለዋል። ነገር ግን በተመድ በኩል ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ የሚደረገው አካሄድ ተቀባይነት የለውም ብለዋል።

- ያልተገደበ የሰብአዊ ድጋፍ ተደራሽነት ተጠናክሮ መቀጠሉን፣ አገራዊ ምክክሩ በሂደት ላይ መሆኑ እና ሰላምን የማስፈን ጥረቶች ተጠናክረው መቀጠላቸውንም ተናግረዋል።

- ኢትዮጵያ በበርበራ ወደብ 19 በመቶ ድርሻዋን እንዳጣች በሚመለከት ይፋ የሆነውን መረጃ በተመለከተ መንግስት መረጃውን እያጣራ ይገኛል ብለዋል።

- መንግስት ሱዳን የያዘችው የኢትዮጰያ መሬት በሌሎች የኢትዮጰያን መረጋጋት በማይፈልጉ አገራት ግፊት የወሰነችው ውሳኔ አድርጎ እንደሚወስደው ገልፀዋል። አሁንም ቢሆን መንግስት ሱዳን ከያዘችው የኢትዮጵያ ግዛት ያለ ግጭት ለቃ እንደምትወጣ ተስፋ አለው ብለዋል።

- ከሰሞኑ ገንዘብ ሚኒስቴር የ2015 ዓ.ም በጀትን ለክልሎች ሲደለድል #የትግራይ_ክልልንም አካቷል ፤ የበጀት ድልድሉ #ድርድር ስለመጀመሩ አመላካች ነው ወይ ? ተብሎ ለተነሳ ጥያቄ አምባዳደር ዲና ሙፍቲ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

Credit ፦ #ኤፍቢሲ #አሀዱሬድዮ #ኢትዮኤፍኤም

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ አሰቃቂ የግድያ ወንጀል መፈፀሙን ፖሊስ ገልጿል።

በአዲስ አበባ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ቦሌ አራብሳ ኮምዶሚኒየም በሁለት ህፃናት ላይ እጅግ አሰቃቂ ግድያ መፈፀሙን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ከጠዋቱ አራት ሰዓት ላይ ሲሆን ፤ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ የምትሰራ አንዲት ግለሰብ ክርስቲያን መላኩና ወንጌላዊት መላኩ የተባሉ የሁለት ዓመትና የሶስት አመት ህፃናትን ህይወት አጥፍታለች።

የአዲስ አበባ ፓሊስ ኮምሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ም/ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ፦

" ቦታው ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ነው፤ ወረዳ አራት አራብሳ ኮንዶሚኒየም እዛ አካባቢ ነው።

ወንጀሉ ተፈፀመው አራት ሰዓት አካባቢ ነው። ግለሰቧ እጅግ ዘግናኝ የሆነ ወንጀል ነው የፈፀመችው።

የሁለት ዓመት እና የሶስት ዓመት (ክርስቲያን መላኩ እና ጊዮናዊት መላኩ) ህፃናትን ነፍስ ነው ያጠፋችው።

ምክንያቱ ገና እየተጣራ ነው ወንጀል ፈፃሚዋ ግን በቁጥጥር ስር ውላለች። እስካሁን ባለን መረጃ ከአሰሪዎቿ ጋር በተፈጠረ ፀብ ነው የሚባለው።

የአገዳደል ሁኔታው እየተጣራ ነው። በምንድነው የገደለችው እንዴት ነው የገደለችው የሚለው ነገር ... ግማሹ አርዳነው ያላል ግማሹ አንቃ ነው ይላል እየተጣራ ነው ዞሮ ዞሮ ግን የህፃናቱ ህይወት አልፏል ይሄ ነው አሁን ላይ በተጨባጭ ሊገለፅ የሚገባው።

ወንጀሉ እጅግ ዘግናኝ ስለሆነ ፖሊስ መስራት የሚገባውን ሰርቶ ለሚመለከተው የፍትህ አካል ያቀርባል ህብረተሰቡ መረጋጋት አለበት። "

#ኢትዮኤፍኤም

@tikvahethiopia