#PressBriefing

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር ፤ በመግለጫቸው ያነሷቸው ነጥቦች እና ተጠይቀው ከመለሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ጥቂቶቹ ፦

- በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ተፈጸሙ በተባሉ ጥሰቶች ላይ ተመድ [UN] ሊያደርገው ያቀደው ተጨማሪ ምርመራ ተቀባይነት የለውም ብለዋል። በኢሰማኮ እና በተመድ የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር የጋራ ሪፖርት ላይ የተመላከቱ ምክረ ሀሳቦችን ለመተግበር መንግስት ዝግጁ ነው ብለዋል። ነገር ግን በተመድ በኩል ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ የሚደረገው አካሄድ ተቀባይነት የለውም ብለዋል።

- ያልተገደበ የሰብአዊ ድጋፍ ተደራሽነት ተጠናክሮ መቀጠሉን፣ አገራዊ ምክክሩ በሂደት ላይ መሆኑ እና ሰላምን የማስፈን ጥረቶች ተጠናክረው መቀጠላቸውንም ተናግረዋል።

- ኢትዮጵያ በበርበራ ወደብ 19 በመቶ ድርሻዋን እንዳጣች በሚመለከት ይፋ የሆነውን መረጃ በተመለከተ መንግስት መረጃውን እያጣራ ይገኛል ብለዋል።

- መንግስት ሱዳን የያዘችው የኢትዮጰያ መሬት በሌሎች የኢትዮጰያን መረጋጋት በማይፈልጉ አገራት ግፊት የወሰነችው ውሳኔ አድርጎ እንደሚወስደው ገልፀዋል። አሁንም ቢሆን መንግስት ሱዳን ከያዘችው የኢትዮጵያ ግዛት ያለ ግጭት ለቃ እንደምትወጣ ተስፋ አለው ብለዋል።

- ከሰሞኑ ገንዘብ ሚኒስቴር የ2015 ዓ.ም በጀትን ለክልሎች ሲደለድል #የትግራይ_ክልልንም አካቷል ፤ የበጀት ድልድሉ #ድርድር ስለመጀመሩ አመላካች ነው ወይ ? ተብሎ ለተነሳ ጥያቄ አምባዳደር ዲና ሙፍቲ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

Credit ፦ #ኤፍቢሲ #አሀዱሬድዮ #ኢትዮኤፍኤም

@tikvahethiopia