TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#UhuruKenyatta 

በኬንያ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 343 ደረሱ!

ፕሬዘዳንት ኡሁሩ ኬንያታ መግለጫ እየሰጡ ይገኛሉ፤ በኬንያ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች 343 መድረሱን አሳውቀዋል። ትላንት 336 እንደነበር ይታወሳል።

በሌላ በኩል ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ዘጠና ስምንት (98) መድረሳቸውን ፕሬዘዳንቱ በመግለጫቸው ተናግረዋል፤ በትላንትናው ሪፖርት ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች 94 እንደነበሩ አይዘነጋም።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጅቡቲ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 1,008 ደረሱ!

ባለፉት 24 ሰዓት በጅቡቲ 341 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 9 ተጨማሪ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

በሌላ በኩል 43 ተጨማሪ ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸውን ተከትሎ አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 373 ደርሷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር መረጃዎች ፦

- በኳታር ተጨማሪ 833 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋግጧል (ይህ እስካሁን በሀገሪቱ ውስጥ ከተመዘገቡት የአንድ ቀን ኬዞች ከፍተኛው ነው) ፤በኳታር አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 9,358 ደርሷል።

- በኢራን ባለፉት 24 ሰዓት 1,134 በኮሮና ቫይረስ ሲያዙ 76 ተጨማሪ ሰዎች ሞተዋል።

- በቤልጂየም ባለፉት 24 ሰዓት 1,032 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 241 ሰዎች ሞተዋል።

- የዓለም ጤና ድርጅት ከኮሮና ቫይረስ በሽታ ያገገሙ ሰዎች ድጋሚ በቫይረሱ ስላለመያዛቸው የሚያረጋግጥ ማስረጃ እንደሌለ አሳውቋል።

- በሲንጋፖር በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች እየጨመረ ነው፤ ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ 618 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል።

- ደቡብ ኮሪያ ለ7ኛ ተከታታይ ቀን ከ15 በታች ኬዝ ሪፖርት አድርጋለች፤ ባለፈት 24 ሰዓት በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 10 ናቸው፤ አራቱ ከውጭ የገቡ እንደሆኑ ተሰምቷል።

- ቻይና 12 ኬዝ ሪፖርት አድርጋለች፤ 11 ከውጭ የገቡ ናቸው።

- በሳዑዲ አረቢያ ተጨማሪ 9 ሰዎች መሞታቸውን ተከትሎ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 136 ደርሷል።

- በስፔን የሟቾች ቁጥር 22,905 ደርሷል። ባለፉት 24 ሰዓት 381 ሰዎች ሞተዋል።

- በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ከ925,000 በልጧል፤ ከ52,000 በላይ ሰዎች ሞተዋል፤ በ110,000 በላይ ሰዎች አገግመዋል።

- በማዳጋስካር አንድ ተጨማሪ ሰው በኮሮና ቫይረስ መያዙን ተከትሎ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 123 ደርሰዋል። በሌላ በኩል አንድ ተጨማሪ ሰው አገግሟል።

- ኬንያ የኮሮና ቫይረስ መስፋፋትን ለመቆጣጠር ጥላ የነበረውን የሰዓት እላፊ ገደብ ለቀጣዮቹ 3 ሳምንታት አራዝማለች።

- በመላው ዓለም ከኮቪድ-19 ያገገሙ ሰዎች ከ810,000 በልጠዋል።

@tikvahethiopia
#DrLiaTadesse

በሀገራችን የኮሮና ቫይረስ ሁኔታ መግለጫ ፦

• አጠቃላይ የተከናወነ የላብራቶሪ ምርመራ - 12,688
• በ24 ሰዓት የተከናወነ ላብራቶሪ ምርመራ - 1,019
• ዛሬ በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠ - 5
• በቫይረሱ ተይዘው በለይቶ ህክምና ውስጥ ያሉ - 88
• በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ - 0
• አዲስ ያገገሙ - 4
• አጠቃላይ ያገገሙ - 29
• በበሽታው ህይወታቸው ያለፈ - 3
• ወደሀገራቸው የተመለሱ - 2
• እስካሁን በበሽታው የተያዙ - 122

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DonaldTrump #DrAbiyAhemed

“ከኢትዮጵያው ጠ/ሚ አብይ አህመድ ጋር ተወያይተናል ፤ ኢትዮጵያ #ቬንቲሌተሮች (የመተንፈሻ መሳሪያ) ያስፈልጓታል አሜሪካም ድጋፍ ለማድረግ በጥሩ አቋም ላይ ትገኛለች፤ ይህንንም እናደርጋለን!” - ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትረምፕ
.
.
"ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር የኢትዮ - አሜሪካንን ግንኙነት የበለጠ በማጠናከር ዙሪያ አበረታች የስልክ ውይይት አድርገናል፡፡ የCOVID-19 መከላከል እና ቅነሳ ጥረቶች እንዲሁም በበረሃ አንበጣ ቁጥጥር ላይ የሚደረገውን ድጋፍ ለማድነቅ እወዳለሁ፡፡" - ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በሱዳን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 213 ደረሱ!

በሱዳን ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 39 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 213 ደርሷል። በተጨማሪ አንድ ሰው መሞቱን ተከትሎ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 17 ደርሷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በሱማሊያ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 390 ደረሱ!

በሱማሊያ ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 62 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 390 ደርሷል።

በተጨማሪ ሁለት (2) ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል፤ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 18 ደርሷል። በሌላ በኩል ሁለት (2) ተጨማሪ ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል፤ አጠቃላይ ያገገሙ ሰዎች ብዛት 10 ደርሷል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር መረጃዎች፦

- በጣልያን የሟቾች ቁጥር ቀንሷል። ባለፉት 24 ሰዓት 415 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል። በተጨማሪ 2,357 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል።

- ባለፉት 24 ሰዓት በፈረንሳይ 369 ሰዎች ሲሞቱ 1,660 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።

- በዩናይትድ ኪንግደም የሟቾች ቁጥር ትላንት ከተመዘገበው ጨምሯል። ባለፉት 24 ሰዓት 813 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተድርጓል። በሀገሪቱ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 20,319 ደርሷል።

- በግብፅ የሟቾች ቁጥር 307 ደርሷል፤ ባለፉት 24 ሰዓት የ13 ሰዎች ሞት ሪፖርት ተደርጓል፤ ከዚህ በተጨማሪ 227 ሰዎች በቫይሩ መያዛቸውን ተከትሎ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 4,319 ደርሷል።

- በዓለም አቀፍ ደረጃ የሟቾች ቁጥር ከ201,501 ደርሷል፤ 824,905 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል፤ 2,891,073 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#BGIEthiopia #FightCOVID19

የፌዴራል ስፓርት ኮሚሽን ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደረሽን እና እግር ኳስ ፌደረሽን ከቢጂአይ ኢትዮጵያ እና ከሌሎች አጋር ግለሰቦች ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ስታዲየም ዙሪያ ያሉ የጎዳና ተዳዳሪዎችን የሚደግፍ የአንድ (1) ወር የምገባ ፕሮግራም ዛሬ አስጀምረዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"በክትባት ፍለጋው ላይ ዓለም አቀፍ ርብርብ ሊደረግ ይገባል" - አንቶኒዮ ጉተሬዝ (የተመድ ዋና ፀሃፊ)

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመግታት ክትባት ፍለጋው ላይ በሚደረግ ጥረት አለማቀፍ ርብርብ እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።

«በመላው ዓለም መንግሥታት በአንድ በኩል ኢኮኖሚያቸውን ከውድቀት ለመታደግ ብርቱ ትግል ያደርጋሉ ፤ በሌላ በኩል በወረርሽኙ የተጠቁ ሰዎች ከ2,8 ሚሊዮን በላይ ሆነው ብርቱ ፈተና ከፊት ተጋርጧል» ብሏል ድርጅቱ።

የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በፍጥነት መዛመት ክትባት ፍለጋው ላይ የሚደረገው ጥረትም የዚያኑ ያህል ፈጣን ካልሆነ ዋጋ ሊያስከፍል እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ አስጠንቅቀዋል። በክትባት ፍለጋው ላይ ዓለም አቀፍ ርብርብ ሊደረግበት ይገባልም ብለዋል።

እስካሁን እየተደረጉ የነበሩ ጥረቶች ከተስፋ የዘለለ ተጨባጭ ውጤት አልተገኘም ያሉት ዋና ጸሐፊው ምናልባትም ረዘም ያለ ጊዜ ሊጠይቅ እንደሚችል ስጋታቸውን ገልጸዋል።

'ከእስከ ዛሬው ሁሉ የሰው ልጅ የተለየ ጠላት ነው የገጠመው' ያሉት አንቶኒዮ ጉተሬዝ ክትባቱን ለማግኘት በሚደረግ ጥረት የአለም መሪዎች ከግሉ ዘርፍ ጋር በመቀናጀት መስራት ይጠበቅባቸዋል በማለት አሳስበዋል።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ሬድዮ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በሩዋንዳ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 183 ደርሱ!

በሩዋንዳ ባለፉት 24 ሰዓት 1,275 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ ሰባት (7) ተጨማሪ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። በሌላ በኩል አንድ ተጨማሪ ሰው ማገገሙን ተከትሎ አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች 88 ደርሰዋል። በሩዋንዳ እስካሁን ሞት አልተመዘገበም።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"ምንም ነገር #እናቶችን ከሞት ለመታደግ የሚያቆመን የለም!" - ባህር ዳር ደም ባንክ

በባህር ዳር ከተማ የደም ልገሳ እየተካሄደ ይገኛል። ዛሬ ብቻ 255 የባህር ዳር ነዋሪዎች ደማቸውን ለወገናቸው ለግሰዋል።

ደም ከለገሱ መካከል ፦

- የባህር ዳር ከነማ ደጋፊዋች
- ጥበበ ግዮን ሆስፒታል የጤና ባለሙያዋች
- አፊላስ ሆስፒታል የጤና ባለሙያዋች
- ኢዜማ የፖለቲካ ድርጅት አባሎች
- ሮትራክት ባህር ዳር
- የባህር ዳር lion security አባላት
- ዶ/ር ሙሉነሽ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ
- ዶ/ር ፍሬው የባህር ዳር ዮንቨርስቲ ፕሬዘዳንት ከእነ ሴት ልጃቸው
- አቶ ክንድይሁን የክልሉ ጤና ቢሮ ምክትል ሀላፊ ይገኙበታል።

ከባህር ዳር ደም ባንክ በተላከልን መልዕክት ይህ የደም ልገሳ መርሃ ግብር ነገም ከጥዋት 3:00 ጀምሮ ይቀጥላል። ይህን መልዕክት የምታነቡ የባህር ዳር ነዋሪዎች ደም በመለገስ የወገናችሁን ህይወት እንድትታደጉ ጥሪ ቀርቦላችኃል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"ከቁጥር እዳንጎድል ቁጥሩን ሳይሆን ቫይረሱን በእውቀት እንቆጣጠረው"

(በዶክተር ያቤፅ ከበደ-የህብረተሰብ ጤና ተመራማሪ)

ከሠሞኑን እየታየ ያለው አዳዲስ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር መቀነስ በህብረተሰቡ ላይ የሚያሳድረው ግምት ምንድን ነው ?

ሀገራችን ኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ ቫይረሱን የመመርመር አቅሟን እየጨመረች ሲሆን ሠሞኑን እየታየ ካለው በቫይረሱ የተያዙ ሰዋች ቁጥር መቀነስ ህዝቡን እንዳያዘናጋ የሚያሰጋ ነው።

የቫይረሱ አሰራር ገና እርግጠኛ ባልሆንበት ጊዜ፣ ባህሪውን በሚለዋውጥበት ወቅት፤ ህዝባችን የተያዘውን ሰው ቁጥር ሳይሆን ገና እርግጠኛ የሆነ ክትባትም ሆነ መድኃኒት ያልተገኘለትን የኮሮና ቫይረስን በአግባቡ መጠንቀቅና እዲሁም በትጋት ሲያደርገው የነበረውን መከላከል እዳያቆም እላለሁ።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሀምሌ 4 ተማሪዎችን አስመርቃለሁ ብሏል!

በኮቪድ 19 ምክንያት ተማሪዎቹን ወደየቤታቸው የሸኘው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች ተጠቅሜ የምሰጠው ትምህርት በጥሩ ሁኔታ ቀጥሏል አለ፡፡

ተማሪዎቹን በያሉበት ሆነው የምርቃት መርሀ ግብራቸው እንደሚካሄድም አሳውቋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ለቅድመ መደበኛ እና ድህረ መደበኛ ተማሪዎች የሁለተኛ ሴሚስተር ትምህርትን በኢሜል ፥ በድረ ገጽ እና ሌሎች መንገዶችን እየሰጠ እንደሆነ ያሳወቀ ሲሆን የዘንድሮ ተመራቂዎችም የመመረቂያ ጽሁፋቸውን በቪዲዮ ታግዘው ካሉበት ሆነው እንደሚያቀርቡ ገልጿል፡፡

ጎግል ሀንግ አውት እና ማይክሮሶፍት ሚት ለዚህ አገልግሎት እንደሚጠቀምም አሳውቋል፡፡የምርቃት መርሀ ግብሩም በተመሳሳይ የመገናኛ ዘዴዎች ታግዞ እና በመገናኛ ብዙሃን እየተላለፈ ሀምሌ 4 ቀም እንደሚካሄድ ዩኒቨርሲቲው ይፋ አድርጓል፡፡

ምንጭ፦ AAU, ADDIS LESAN
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
(በተሾመ ሃይሉ)

የሐረማያ ዩኒቨርስቲ በአካባቢው ለሚገኙና ዝቅተኛ የሆነ ገቢ ላላቸው ከ170 በላይ ነዋሪዎች ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ለአንድ ወር የሚሆን የምግብ ድጋፍ አደረገ።

ዩኒቨርስቲው በሚገኝበት ሐረማያ ከተማ ባቴ ቀበሌ ነዋሪ ለሆኑና በቀን ስራና በሌሎች አነስተኛ ስራዎች ተሰማርተው ለሚኖሩ ዝቅተኛ በሆነ ገቢ ለሚተዳደሩና በኮሮና ቫይረስ ስርጭት ሳቢያ ለችግር ለተጋለጡ 178 ነዋሪዎች ነው የምግብ ድጋፉ የተደረገው።

ድጋፍ ለተደረገላቸው ለእያንዳንዳቸው ለአንድ ውር ሊሆን የሚችል ቀለብ ሲሆን በዚህም 15 ኪሎ ጤፍ፣ 40 ኪሎ በቆሎ፣ 20 ኪሎ ማሽላ፣ 25 ኪሎ ማካሮኒ፣ ማሽላ፣ ቦሎቄ፣ የምግብ ዘይትና ሌሎች አልሚ ምግቦችና የንፅህና መጠበቂያ ተሰጥቷቸዋል።

በአጠቃላይ በተሰጠው የምግብ ድጋፍ ለእያንዳንዳቸው ከ3 ሺህ ብር በላይ ሲሆን በአጠበቃላይ 688 ሺህ 860 ብር ወጪ እንደተደረገበት የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጀማል ዩሱፍ የገለፁ ሲሆን አሁን የተደረገው የምግብ ድጋፍ የመጀመሪያው ዙር እንደሆነና ቀጣይነት እንደሚኖረው አስታውቀዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ETABSoapFactory

ሀዋሳ ከተማ የሚገኘው ኢታብ ሳሙና ፋብሪካ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት እየተደረገ የሚገኘውን ጥረት ለማገዝ የተለያዩ እገዛዎችን ማድረጉን አሳውቆናል። የድርጅቱ ም/ዋና ስራ አስኪያጅ እጩ ዶክተር ሳምሶን ታደሰ በላኩልን ደብዳቤ የተደረጉት የድጋፍ አይነቶች በዝርዝር ተገልፀዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ADAMA

በአዳማ ከተማ በንግድ ስራ ላይ የተሰማሩት እና የኤፍራታ ጁስ እና ፒዛ ድርጅት መስራች እና ባለቤት የሆኑት አማኑኤል አለሙ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ–19) ወረርሽኝ ለመግታት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ በቅርቡ ለድርጅቱ ቅርጫፍነት አስገንብተው የጨረሱትን ባለ አራት(4) ፎቅ ህንፃ ለለይቶ ማቆያ እንዲሆን ለመንግስት አስረክበዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#NEKEMTE

የስም ዝርዝራቸው በምስሉ ላይ የተገለፀ ግለሰቦች በነቀምት ከተማ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመግታት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ አንድ ላይ በመሆን 416,000 ብር በማዋጣት 200 ኩንታል የስንዴ ዱቄት ገዝተው አበርክተዋል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia