TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Congratulations ወደበኃላ ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ምርቃት ጋር የተያያዙ ዝርዝር መረጃዎችን አቀርባለሁ!

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Congratulations

የመከላከያ አዛዥነት ስታፍ ኮሌጅ ለ13ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን 100 ከፍተኛ መኮንኖች አስመረቀ። ዛሬ በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት በተከናወነ ስነ ስርዓት የተመረቁት 100 ከፍተኛ መኮንኖች ውስጥ 92 ፖስት ስታፍ እና ስምንት የሁለተኛ ድግሪያቸውን የተከታተሉ ናቸው።

ከእነዚህ ውስጥም 21 ተመራቂዎች ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ መሆናቸው በምረቃው ስነ ስርዓት ላይ ተገልጿል። እነዚህ ተመራቂዎችም ከጅቡቲ፣ ሶማሊያ እና ደቡብ ሱዳን የተውጣጡ መሆናቸው ነው የተመለከተው።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዶክተር አብይ አህመድም ለተመራቂዎች ዲፕሎማ ከሰጡ በኋላ የስራ መመሪያ ሰጥተዋል። ተመራቂዎች በስነ ምግባር፣ በወታደራዊ ጥበብ፣ በሙያዊ ብቃት እና በላቀ ዝግጅት የሰራዊት አባላትን ለመምራት እና ለድል ለማብቃት የሚያስችላቸውን እውቀት እና ከህሎት ለማግኘት ለአንድ ዓመት ትምህርታቸውን መከታተላቸውን አንስተዋል።

በመሆኑም በትምህርት የገበዩትን እውቀት ከዚህ በፊት ካገኙት ልምድ፣ በንባብ ከሚያገኙት እና በተፈጥሮ ከያዙት እውቀት ጋር በማዋሃድ በትጋት ሀገራቸውን እንዲያገለግሉ ነው ያሳሰቡት።

ወታደራዊ ተቋማት በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ እና በፈጠራ መሪዎች፣ በስነ ምግባር አርኣያዎች፣ ሀገርን እና ወገንን በመጠበቅ አኩሪዎች፣ ህግና ስርዓትን በማክበር እና በማስከበር ተምሳሌት እንዲሆኑም ያስፈልጋል ብለዋል።

Via #FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Congratulations

ASTU 1859 ተማሪዎችን አስመረቀ!

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ/ASTU/ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያስተማራቸውን 353 ሴት ተማሪዎችን ጨምሮ 1859 ተማሪዎችን አስመረቀ፡፡ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በመልዕክታቸውም በዩኒቨርስቲ የሚታዩ #በዘርኝነት የሚከሰቱ #መጠፋፋቶች ኋላ ቀር አስተሳሰብ በመሆናቸው ይህ ትውልድ መፍቀድ የለበትም ብለዋል፡፡ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ሂሩት ወልደ ማርያም በበኩላቸው ተማሪዎች በተማሩበት መስክ ጠንካራ ሰራተኛ በመሆን የአገልጋይነት ስሜት በመላበስ የተጣለባቸውን አደራ እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ ከ25 አመታ በፊት የተቋቋመው ዩኒቨርስቲው በልዩ የመግቢያ ፈተና በዓመት 5ሺህ የሚሆኑ ለፈተና ቢቀርቡም 1500 ብቻ ናቸው ዕድሉን የሚያገኙት ተብሏል፡፡ ዩኒቨርስቲው የምርምር እና የጥናት የልህቀት ስራዎችን የሚያካሂድበት 8 የልህቀት ማዕክል አሉት፡፡

በዩኒቨስቲው የሚገኘው ላብቶሪ ለዩኒቨርስቲ ለተማሪዎች ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ጭምር አገልግሎቱን እንደሚሰጥ ተነግሯል፡፡ ሙህራን በዘርፉ ላይ ምርምር እና ጥናት ሊያካሂዱበት የሚችል በአይነቱ ለየት ያለ የምርምር ማዕከል በዩኒቨርስቲው ውስጥ እየተገነባ እንደሚገኝም ተነግሯል፡፡

Via #ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Congratulations #Somaliland Military Officers graduate from #Ethiopian Military Academy, Won medals!

Via Horn
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Congratulations የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ካምፓስ በዛሬው ዕለት ተማሪዎችን በማስመረቅ ላይ ይገኛል። ለመላው ተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ!!

ፎቶ📸AMANI
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Congratulations

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም የሕክምና ኮሌጅ የሕክምና ባለሙያዎችን በስካይ ላይት ሆቴል እያስመረቀ ነው፡፡ ኮሌጁ በቅድመ- እና ድህረ-ምረቃ መርሃ-ግብር ያሰለጠናቸውን የሕክምና ባለሙያዎችን ነው በማስመረቅ ላይ ያለው፡፡

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴና የጤና ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን ተገኝተው ንግግር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡ በጤናው ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋፅዖ ላበረከቱም የክብር ዶክትሬቶች ይሰጣሉም ተብሏል፡፡

Via #EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Congratulations ናሽናል ኮሌጅ በዲግሪና ቲኢቪቲ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በኦሮሚያ ባህል ማዕከል እያስመረቀ ይገኛል።

ፎቶ📸እዩኤል/TIKVAH-ETH/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Congratulations ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም የሕክምና ኮሌጅ 365 የሕክምና ባለሙያዎችን አስመርቋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Congratulations የዲላ ዩኒቨርስቲ በክረምት ወራት ያሰለጠናቸውን 2ሽህ 286 ተማሪዎች ዛሬ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ አስመረቀ። ዩኒቨርሲቲው ካስመረቃቸው ተማሪዎች ውስጥ 504 ሴቶች ይገኙበታል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Congratulations

በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኦቶና ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በነርሲንግና በህክምና ዶክትሬት ድግሪ ያሰለጠናቸውን 63 ዕጩ ምሩቃንን በዛሬው ዕለት አስመርቋል፡፡

በምረቃ ሥነስርዓቱ የተገኙት የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ወንድሙ ወልዴ በህክምናው ዘርፍ በሰው ሃይል ልማት ላይ መስክ ዩኒቨርሲቲው አበረታች ሥራ እየሰራ መሆኑን አውስተዋል፡፡

የህክምና ሳይንስ ጥልቅ ዕውቀትን እና ሙያዊ ታማኝነትን የሚሻ በመሆኑ ምሩቃን ወደስራ ሲገቡ እያንዳንዱን የማህበረሰብ ክፍል በታማኝነት እና በቅንነት ማገልገል እንዳለባቸው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Via WSU
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Congratulations

የቅዱስ አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከጎንደር ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በተቀናጀ የክሊኒካልና ህብረተሰብ አቀፍ የአእምሮ ጤና በሁለተኛ ዲግሪ ያስመረቃቸውን 25 ተማሪዎች አስመረቀ፡፡ ሆስፒታሉ በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ተማሪዎቹን ሲያስመርቅ የዘንድሮው ለአስረኛ ግዜ ሲሆን፤ ከ25ቱ ተመራቂ ተማሪዎች መካከል ሶስቱ ሴቶች ናቸው። ሆስፒታሉ ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ ከጎንደር ዩንቨርስቲ ጋር በመተባበር በተቀናጀ የክሊኒካልና ህብረተሰብ አቀፍ ጤና ትምህርት ዘርፍ ተማሪዎችን ሲያስመርቅ የቆየ ሲሆን፤ የዘንድሮዎቹን ጨምሮ የተመራቂዎችን ቁጥር ወደ 245 ከፍ እንደሚያደርገው ተገልጿል፡፡

Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#CONGRATULATIONS

በአሁን ሰዓት "ጎንደር ዩኒቨርስቲ" የህክምና ተማሪዎቹን በደማቅ ሁኔታ እያስመረቀ ይገኛል፡፡ በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የተማሪ ወላጆች፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

#ቲክቫህ_ኢትዮጵያ

@tikvahethmagazine
#congratulations

ጎንደር ዩንቨርሲቲ በዛሬው ዕለት 251 የህክምና ዶክተሮችን አስመርቋል። ተመራቂዎች እና የተመራቂ ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ!

(ፎቶ-ቴዎድሮስ-ቲክቫህ ቤተሰብ ጎንደር)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Congratulations

የኢትዮጵያ አየር መንገድ "አቪዬሽን አካዳሚ" በተለያዩ የትምህርት ዘርፎት ያሰለጠናቸውን 384 ተማሪዎች አስመርቋል። ከተመረቁት 384 ተማሪዎች ውስጥም 67 የአውሮፕላን አብራሪዎች፣ 70 የአውሮፕላን ቴክኒሻኖች፣ 109 የበረራ አስተናጋጆች፣ 90 የሽያጭና 48 የምግብ ዝግጅት አገልግሎት ባለሙያዎች መሆናቸው ተገልጿል።

(FBC)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Congratulations - አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲው ለ 6ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን 140 የሕክምና ዶክተሮች ትላንት ታኅሣሥ 11/2012 ዓ/ም በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል፡፡ ከእነዚህም መካከል 37ቱ ሴቶች መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#CONGRATULATIONS

#MEKELLE #HARAMAYA

- በሃረማያ ዩኒቨርሲቲ የሐረር የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጁ ያሰለጥናቸውን 239 የህክምና ዶክተሮች ዛሬ አስመርቋል፡፡ ኮሌጁ ለ7ኛ ዙር ያስመረቀ ሲሆን ከተመራቂዎቹ 56ቱ ሴቶች ናቸው፡፡ በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የሃረሪ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር አቶ ኦርዲን በድሪን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋና ሌሎች የክልልና የፌዴራል የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተው ነበር።

- በመቐለ ዩንቨርስቲ የአይደር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለ11ኛ ጊዜ 390 የህክምና ዶክተሮችን አስመርቋል። ከተመራቂዎቹ መካከል በጥርስ የህክምና ሙያ የተማሩ ይገኙበታል። በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የፌዴራል የጤና ጥበቃ እና የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የስራ ኃላፊዎች ተገኝተው ነበር።

(EBC)
@tikvahethmagazine
#Congratulations

በዛሬው ዕለት ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ 221 የህክምና ዶክተሮችና ስፔሻሊስቶችን አስመርቋል። ከተመራቂዎቹ መካከል 192 የህክምና ዶክተሮች ሲሆኑ 29 ስፔሻሊስት ዶክተሮች ናቸው። ከዛሬዎቹ 221 ተመራቂዎች ውስጥ 22 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውንም ተጠቁሟል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Congratulations

የአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ በአጠቃላይ እና የጥርስ ሕክምና ያሰለጠናቸውን 301 ባለሙያዎች አስመረቀ። ከተመራቂዎቹ መካከል 292ቱ በአጠቃላይ ሕክምና፣ 9ኙ ደግሞ በጥርስ ሕክምና ሙያ የሰለጠኑ ናቸው። ከተመራቂዎቹ መካከል 30 በመቶው ሴቶች ሲሆኑ 170 የሚደርሱት ደግሞ የላቀ ውጤት አስመዝግበዋል።

PHOTO : Tikvah Family
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#TikvahFamilyMekelle

ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በስልክ ያገኘናቸው የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች የሆኑ የቲክቫህ አባላት ከብዙ ውጣ ውረድ በኃላ ለዚህ ቀን በመብቃታቸው ደስ እንደተሰኙ ገልፀውልናል።

እጅግ በጣም ፈታኝ እና አስቸጋሪ በነበሩ ወቅቶች የመቐለ ነዋሪዎች አብሯቸው ስለነበሩ ፣ አይዞአችሁ እኛ አለንላችሁ ስላሏቸው ፣ ለእራሳቸው እየተቸገሩ ከሚበሉት ላይ ቀንሰው ስላካፈሏቸው ፣ ከሚጠጡት ቀንሰው ስላጠጧቸው፣ ፍቅር ስላስተናገዷቸው ፣ እንደልጆቹ ስለተንከባከባቸው ምስጋና እንድናደርስላቸው ጠይቀውናል።

እኛም ምንም እንኳን የመቐለ ነዋሪዎች በኢንተርኔት መቋረጥ ይህንን መልዕክት ባያዩትም ምስጋናውን አድርሰናል።

#Congratulations

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia