#CONGRATULATIONS

#MEKELLE #HARAMAYA

- በሃረማያ ዩኒቨርሲቲ የሐረር የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጁ ያሰለጥናቸውን 239 የህክምና ዶክተሮች ዛሬ አስመርቋል፡፡ ኮሌጁ ለ7ኛ ዙር ያስመረቀ ሲሆን ከተመራቂዎቹ 56ቱ ሴቶች ናቸው፡፡ በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የሃረሪ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር አቶ ኦርዲን በድሪን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ኢንጂነር ሃብታሙ ኢተፋና ሌሎች የክልልና የፌዴራል የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተው ነበር።

- በመቐለ ዩንቨርስቲ የአይደር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለ11ኛ ጊዜ 390 የህክምና ዶክተሮችን አስመርቋል። ከተመራቂዎቹ መካከል በጥርስ የህክምና ሙያ የተማሩ ይገኙበታል። በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የፌዴራል የጤና ጥበቃ እና የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የስራ ኃላፊዎች ተገኝተው ነበር።

(EBC)
@tikvahethmagazine