TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከፍተኛው ውጤት የተመዘገበው አማራ ክልል ነው!

ዘንድሮ ፈተና ላይ ከተቀመጡት መካከል ከፍተኛው ውጤት 645 ሲሆን አማራ ክልል ከፍተኛው ውጤት የተመዘገበበት ክልል መሆኑ ተገልጿል።

Via #ETHIOFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የ68 ተማሪዎች ውጤት ተሰርዟል!

🏷በአማራ፣ ደቡብ ፣ ቤኒሻንጉል እና ኦሮሚያ ክልሎች 846 ተማሪዎች ከፍተኛና ተመሳሳይ የውጤት መመሳሰል በማምጣታቸው ተጨማሪ #ማጣራት እንዲደረግባቸው ተወስኗል። በፈተናው ወቅት በተፈጸመ የደነብ ጥሰት 68 ተማሪዎች ውጤት #መሰረዙም ተገልጿል።

Via #ETHIOFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለ200ሺህ ዜጎች የስራ እድል የሚፈጥር ፕሮጀክት!

በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ 200 ሺህ ዜጎች የስራ እድል የሚፈጥር ፕሮጀክት ይፋ ሆኗል፡፡ ሊ ዌይ ፕሮግራም የተሰኘዉ ይህ ፕሮጀክት በአዲስ አበባ ያለዉን የስራ አጥነት ችግር ይቀንሳል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል፡፡

የፕሮጀክቱ ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ የሺወርቅ እንዳስታወቁት፤ ፕሮግራሙ ለቀጣይ 5 አመታት የሚቆይ ሲሆን ሴቶች እና ወጣቶች ወደ ንግድ እንዲገቡ ያስችላል ብለዋል፡፡

በአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር የማኅበራዊ ዘርፍ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር እንዳወቅ አብጤ በበኩላቸዉ የፕሮጀክቱ ዋነኛ ተጠቃሚዎቹ ሴቶች እና ወጣቶች መሆናቸዉን ገልፀዉ በተለይም የማህበራዊ ችግር ተጋላጭ ለሆኑ ወገኖች ትኩረት እንደሚደረግባቸው ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የጎዳና ተዳዳሪዎችን በማንሳት የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንሰራለንም ብለዋል፡፡ አሁን ላይ ለሀገሪቱ አሳሳቢ የሆነዉን ስራ አጥነት ለመቀነስም ከመንግስት በተጨማሪ የግሉ ዘርፍም ሊረባረብ እንደሚገባም ተጠቁሟል፡፡

የሊ ዌይ ፕሮጀክት ለቀጣዮች 5 አመታት ተግባራዊ የሚሆን ሲሆን አሁን ላይ ከ2 ሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎችን ወደ ንግዱ ለማሳመራት 20 ሚሊዮን ዶላር መመደቡንም ተሰምቷል።

Via #ETHIOFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እስራኤል አሜሪካዊያኑ ኢልሃን ኦማርና ረሺድ ተሊብ ወደ ሃገሯ እንዳይገቡ ከለከለች። የእስራኤልን መንግስት በመተቸት የሚታወቁት ሁለቱ የአሜሪካ ምክር ቤት አባላት በሚቀጥለው ሳምንት ዌስት ባንክና ምስራቃዊ እየሩሳሌምን ለመጎብኘት እቅድ ነበራቸው፡፡

ሀለቱም እስራኤልን የሚቃወሙ እንቅስቃሴዎችን በመደገፍ የሚታወቁ ሲሆን የሃገሪቷ ህግ ደግሞ ጸረ እስራኤል እንቅስቃሴን የሚደግፉ ሰዎች ላይ የጉዞ ማእቀብ መጣል ይፈቅዳል፡፡

ዶናልድ ትራምፕ ሴቶቹ ወደ እስራኤል መግባት ከቻሉ ይህ ትልቅ ድክመት መኖሩን ያሳያል ሲሉ በትዊተራቸው አስፍረው ነበር፡፡ ፕሬዘዳንቱ አክለውም ሁለቱ ህግ አውጪዎች እስራኤሎችንና መላ አይሁዶችን ይጠላሉ፤ ምንም ነገር ቢደረግ የነሱን አመለካከት መቀየር አይቻልም ብለዋል፡፡

እስራኤል እገዳውን ከማስተላለፏ በፊትም እስራኤል ለምን ልትፈቅድላቸው እንደምትችል ማሰብ አልችልም፤ ከፈለጉ ሊፈቅዱላቸው ይችላሉ እኔ ግን ይህን ማሰብ አልችልም ሲሉ ለሪፖርተሮች ተናግረዋል፡፡ እንስቶቹ ዲሞክራቶች እስራኤልን ይቃወማሉ በሚል ይተቻሉ፡፡ እነሱ ግን ጸረ እስራኤል አቋም የለንም ሲሉ ያስተባብላሉ፡፡

Via #ETHIOFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አፕቲትዩድ

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች ከስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ዉጪ በሌሎች የትምህርት አይነቶች የፈተና አስተራረም ችግር አለመፈጠሩ ተገለጸ።

የሃገር አቀፍ ፈተናና ምዘና ኤጀንሲ ተማሪዎች ቅሬታ ሲቀርብበት የነበረውን የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና የስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ውጤትን መመልከት እንደሚችሉ አስታውቋል።

ኤጀንሲው ከፈተናው የመልስ ቁልፍ ጋር ተያይዞ የነበረው እርማት ተጠናቆ በድረ ገጹ እና በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መመልከት ይችላሉ ብሏል። የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዓርዓያ ገብረእግዚአብሄር እንዳሉት የስኮላስቲክ ፈተናው ኮድ 21 እና 22 ችግር እንደነበረባቸው ጠቅሰዋል።

ዳይሬክተሩ ቀደም ሲል በአጭር የፅሁፍ መልዕክት እና በድረ ገጽ መለቀቁን ጠቅሰው፥ የተለቀቀው ውጤት ያልተስተካከለው እንደነበር ገልጸዋል። ለዚህም ቀደም ሲል በአጭር የፅሁፍ መልዕክት የተለቀቀውን መረጃ ማጥፋት የሌላ አካል ሃላፊነት መሆኑንም አንስተዋል፡፡

ከፈተናው ጋር ተያይዞ ለኤጀንሲው 10ሺህ ያህል ቅሬታዎች መቅረባቸውን ያነሱት ዳይሬክተሩ፥ አሁን ላይም ጉዳዩን የሚከታተል ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ይሁን እንጅ እስካሁን በሌሎች የትምህርት አይነቶች ችግሮች ያለመገኘታቸውን አስረድተዋል። የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት እርማት ሃምሌ 20 ቀን 2011 መጠናቀቁን የተናገሩት ዳይሬክተሩ ፈተናው ይፋ እስከሚደረግ ድረስ ባሉት ጊዜያትም መሰል ችግሮች እንዳይከሰቱ የማጣራት ስራ ሲሰራ እንደነበረም አስታውሰዋል፡፡

Via #ETHIOFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update 2.7 ሚሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው የሶስት ሀገራት የብር ኖቶች በህገወጥ መንገድ ከሀገር ለማስወጣት ሲሞከር በቁጥጥር ስር ዋሉ። ዛሬ በዋለው የምንዛሪ መጠን በድምሩ 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው 11 ሺህ 900 ድርሀም 76ሺህ 230 የአሜሪካን ዶላር እና 66ሺህ 900 የሳውዲ ሪያል በህገ-ወጥ መንገድ ከሀገር ለማስወጣት ሲሞከር በቁጥጥር ስር መዋሉን የገቢዎች ሚኒስቴር ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታውቋል፡፡

የብር ኖቶቹ ከሀገር ለማስወጣት የተሞከረው ባለአምስት ሊትር ጀሪካን ውስጥ በመደበቅ ሲሆን በቶጎጫሌ ሚሊሻና በጉምሩክ አባላት የተቀናጀ ጥረት በቁጥጥር መዋሉ ተገልጿል፡፡ ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር የአገሪቱን ኢኮኖሚ ከማዳከም ባለፈ የህዝብ ሰላምና ጤንነት ፀር የሆኑ የኮንትሮባንድ ምርቶች ለመግዛት የሚውል በመሆኑ ህብረሰተቡ ይህን በመገንዘብ ድርጊቱን ለማስቆም ከዳር እስከ ዳር እንዲረባረብ የገቢዎች ሚኒስቴር ጥሪውን አቅርቧል።

Via #ETHIOFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኦነግ ወታደራዊ ዩኒፎም ተያዘ እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው!

በወልዲያ የፍተሻ ጣቢያ ላይ የተያዘው ወታደራዊ ዩኒፎርም መሰል አልባሳት የእኔ ነው ሲል የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ መነሻዉን መቐለ ያደረገ አይሱዙ ወልዲያ የፍተሻ ጣቢያ ላይ ሲደርስ በፍተሸ ጣቢያ ሰራተኞች ተይዞ ፍተሻ እየተደረገበት ይገኛል፡፡ምክንያቱ ደግሞ የጫነዉ አልባሳትን ምንነት ለማረጋገጥ ነዉ ተብሏል፡፡

የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ሰለሞን ወርቁ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት፤ መኪናዉን ጭኖ ሲንቀሳቀስ የነበረዉ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ቁጥጥርና ጥበቃ ሰራተኞች /ስካዉት/ የሚለብሱት ዩኒፎርም ነበር ብለዉናል፡፡ መኪናዉም 3 ሺህ የዩኒፎርም አልባሳትና 170 ጃኬቶችን ጭኖ ከመቀሌ አልመዳ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ እንደነበረም ነዉ የተናገሩት፡፡

አልባሳቱ #የተጫነዉ በግል መኪና መሆኑና አልባሳቱ የኛ መሆኑን የሚያመለክት ደብዳቤ በአሽከርካሪዉ እጅ አለመገኘቱ ለጥርጣሬዉ መነሻ እንደሆነም አቶ ሰለሞን ገልጸዋል፡፡ አሁን ላይ ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ተነጋግረን ማረጋገጫ ደብዳቤ እንድንጽፍ በጠየቁን መሰረት ደብዳቤ ጽፈናል፤በነገዉ እለትም መኪናዉ ወደ አዲስ አበባ ይንቃቀሳል ብለን እንጠብቃልን ነዉ ያሉት፡፡

ከዚህ ባሻገር ግን አልባሳቱ የኦነግ ነዉ ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰዉ ወሬ #ከእዉነት_የራቀ_ነዉ፤ አልባሳቱ የኛ ነዉ፤ ለዱር እንስሳት ጥበቃ ለመተማሩ ሰራተኞች የተዘጋጀ ዩኒፎርም ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ በፌደራል ደረጃ በሚተዳደሩ 13 ብሄራዊ ፓርኮች 790 ስካዉቶች በስራ ላይ ተሰማርተዉ ይገኛሉ፡፡

Via #ETHIOFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Breaking

ምርጫ ቦርድ #የሲዳማ_የክልልነት ጥያቄ ህዝበ ውስኔ መስጫ ቀንን ይፋ አደረገ። ቦርዱ ዛሬ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቀው የሲዳማ የክልልነት ጥያቄ ህዝበ ውስኔ መስጫ ቀን ህዳር 3 ቀን 2012 ዓ/ም እንዲሆን ተወስኗል።

ቦርዱ ለዚህ ስራም ከነሀሴ 30 ቀን 2011 ዓም አንስቶ 8ሺህ 460 ምርጫ አስፈጻሚዎችን እንዲሁም 1 ሺህ 692 የህዝበ ውሳኔ ደምጽ መስጫ ጣቢያዎችን አደራጃለሁ ብሏል። ለህዝበ ውሳኔው ስራ ማስኬጃ 75 ሚሊዮን 615 ሺህ ብር የሚያስፈልግ ሲሆን ወጪውን የደቡብ ክልል ምክር ቤት ይሸፍናል ተብሏል።

Via #EthioFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በቺክቭ የተጠቁ ሰዎች 20 ሺህ ደርሷል!

በድሬዳዋ በችኩንጉኒያ ወረርሽኝ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር ወደ 20 ሺህ ማሻቀቡ ተገለጸ፡፡ ችኩንጉኒያ ወረርሽኝ ኤደስ በምትባል ትንኝ ንክሻ ወደ ሰው የሚተላለፍ በሽታ ሲሆን ችኩንጉኒያ በሚባል ቫይረስ የሚመጣ ህመም ነው፡፡

የችኩንጉኒያ ወረርሽኝ ከሀምሌ ወር ጀምሮ በድሬዳዋ ከተማ የተከሰቱ ሲሆን የተጠቂዎች ቁጥር ባሳለፍነው ሳምንት ከደረሰበት 15 ሺህ አሁን ላይ ወደ 20 ሺህ ከፍ ማለቱን የኢትዮጵያ ህብረትሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለኢትዮ ኤፍ ኤም አስታውቋል፡፡ በወረሽኙ እስከ አሁን ድረስ የሞተ ሰው አለመኖሩንም ኢንስቲትዩቱ ገልጿል።

እስካሁን በተደረገ የቤት ለቤት አሰሳ 86 በመቶ የሚሆኑት ቤቶች ወረርሽኙን የሚያስተላልፈው ትንኝ እጭ እንደተገኝባቸው ኢንስቲትዩቱ አስታውቃል፡፡ ወረርሽኙን ለመቆጣጠር ከድሬዳዋ አስተዳደር፣ከኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እንዲሁም ከአጋር ድርጅቶች የተውጣጣ ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድን በቦታው በመገኘት የተቀናጀ ምላሽ በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ነው የተገለጸው፡፡

ወረርሽኙን ባጭር ጊዜ ውስጥ ለመቆጣጠር በከንቲባ ፅ/ቤት የሚመራ ግብረሃል ተቋቁሞ በቅንጅት እየተሰራ የሚገኝ ሲሆን ከእነዚህም ዉስጥ የቤት ለቤት ርጭት፣ የቅኝት እና አሰሳ ስራዎች፣ የማህበረሰብ ንቅናቄ፣ የህክምና አገልግሎት በሁሉም ጤና ተቋማቶች እየተከናወኑ እንደሆነ ተገልጿል።

Via #EthioFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአፍሪካ ህብረት በደቡብ አፍሪካ እየተፈፀመ ያለውን ጥቃት አወገዘ፡፡ የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋኪ ማሀማት በደቡብ አፍሪካ በሚገኙ የሌላ ሀገራት ዜጎች ላይ እየተወሰደ ያለውን የሀይል እርምጃ ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው ሲሉ አውግዘዋል።

የዜጎችን ንብረት መዝረፍም ሆነ የማጥፋት አካሄድ በህብረቱ የሚወገዝ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ሊቀ-መንበሩ እንደተናገሩት ቀደም ሲል በታሰሩት የሀገሪቱ ባለስልጣናት እንዲህ አይነቱ ተግባር ይበረታታ እንደነበር ገልፀዋል፡፡

የሰዎችን ሕይወትና ንብረት ለመጠበቅ ተጨማሪ አፋጣኝ እርምጃዎች መወሰድ አለባቸው ያሉት ሊቀመንበሩ የደቡብ አፍሪካ መንግስት ወንጀለኞች ለፈፀሙት ድርጊት ተጠያቂ መሆናቸውን እንዲያረጋግጭ አሳስበዋል። እንዲሁም ኢኮኖሚያዊና ሌሎች ተጨማሪ ውድመት ላጋጠማቸው ሰዎች ትክክለኛ ፍትህ መሰጠት አለበት ብለዋል፡፡

የህብረቱ ሊቀ-መንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት እነዚህን ወንጀለኞች ለመያዝ በሚደረገው ጥረት ህብረቱ ለደቡብ አፍሪካ መንግስት ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል።

Via #EthioFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ትምህርት ሚኒስቴር በ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዙሪያ ዛሬ ከሰዓት መግለጫ ይሰጣል። የትምህርት ሚኒስቴር ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳስታወቀው በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ውጤት፣ዩንቨርሲቲ መግቢያ ውጤትና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ይሰጣል። መግለጫውን የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ጥላዬ ጌቴ እንደሚሰጡ ተገልጿል።

Via #EthioFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የመስከረም 4ቱ ሰልፍ ከኦሮሚያ ቤተክህነት ምስረታ ጋር የተያያዘ አይደለም!

መስከረም 4 ይደረጋል የተባለው ሰላማዊ ሰልፍ ከኦሮሚያ ክልል ቤተክህነት ምስረታ ጋር የተያያዘ #እንዳልሆነ የሰልፉ አስተባባሪ ኮሚቴዎች አስታውቀዋል። ከኦሮሚያ ቤተክህነት ምስረታ ጋር በተያያዘ በጉዳዩ ዙሪያ በቅርቡ ሲኖዶሱ የሰጠው መግለጫ በቂ መሆኑን ገልፀዋል።

Via #ETHIOFM

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ጉምሩክ ከ19 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት አደንዛዥ ዕፅ ተያዘ፡፡ የገቢዎች ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በቦልቪያናዊዉ ናማኒ ቺንቼ ኢቬሊን የፓስፖርት ቁጥር AE57255 ከብራዚል ሳዖ ፖሎ አዲስ አበባ የገባዉ 8 ኪሎ ግራም የኮኬይን አደንዛዥ ዕፅ በቦሌ የጉምሩክ ፈታሾች በቁጥጥር ስር ዉሏል፡፡

ዕፁን ይዞት ይጓዝ በነበረዉ ግለሰብ ላይ ከብራዚል ሳኦ ፖሎ ጀምሮ በጉምሩክ ኮሚሽን ኢንተለጀንስ ቡድን ባደረገዉ የተቀናጀና ጠንካራ ክትትል በቁጥጥር ስር ሊዉል መቻሉ ተገልጿል፡፡

ይህንን አድካሚና የተቀናጀ ስራ በመስራት እፁን መያዝ ለቻሉ የቦሌ አየር ማረፊያ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አመራር አካላትና ሰራተኞች የገቢዎች ሚኒስቴርና የጉምሩክ ኮሚሽን ምስጋና አቅርቧል፡፡ ባለፈዉ ሳምንትም 20 ሚሊየን ብር የሚገመት 10.8 ኪ.ግ የሚመዝን አደንዛዥ ዕፅ መያዙ የሚታወስ ነዉ፡፡

Via #ethiofm
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#EthioTelecom

ኢትዮ - ቴሌኮም [ethiotelecom] የብሮድባንድ ኢንተርኔት የታሪፍ ቅናሽ ማድረጉን አሳውቋል። ማሻሻያውም ለመኖርያ ቤት 69 በመቶ ቅናሽ ፣ ለድርጅቶች 65 በመቶ፣ VPN ደግሞ 72 በመቶ ቅናሽ መደረጉ ተገልጿል።

ማሻሻያው በዋጋ ብቻ ሳይሆን በፍጥነትም ጭምር መሆኑ ተሰምቷል። የኢንተርኔት አገልግሎቱ ለመኖርያ ቤት የ 3 በመቶ ፍጥነት ፣ ለድርጅቶች 4 በመቶ ፍጥነት ይጨምራል።

PHOTO : #TikvahFamily [Andinet]

#ETHIOFM #ሔኖክአስራት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ProsperityParty ብልጽግና ፓርቲ [Prospertity Party] በትግራይ ክልል በሁሉም ወረዳዎች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በቅርቡ እንደሚከፍት የፓርቲው የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙት ኃላፊ ገለጹ፡፡ የብልጽግና ፓርቲ የሕዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አወሉ አብዲ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ብልጽግና አገር አቀፍ ፓርቲ በመሆኑ ከትግራይ ክልል ጋር በሚኖረው ሕገ መንግሥታዊ…
#TPLF #ProsperityParty

ብልጽግና ፓርቲ በትግራይ ክልል በሁሉም ወረዳዎች ቢሮ እንደሚከፍት ያስታወቀ ቢሆንም የክልሉ መንግስት ግን የሚያዉቀዉ ነገር እንደሌለ የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል።

አቶ ጌታቸዉ ረዳ ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የተናገሩት፦

ብልጽግና ፓርቲ ለትግራይ ክልል የተሾሙ ግለሰቦች እንዳሉ ሰምቻለሁ እነማን እንደተሾሙ ግን ወደ ፊት የሚሆነዉን የምናይ ይሆናል፡

ብልጽግና በትግራይ ክልል ብዙ ደጋፊ አለው ብዬ አላምንም፤ ማንኛዉም ፓርቲ ህጋዊ እስከሆነ ድረስ ግን በትግራይ ክልል የመንቀሳቀስ መብት አለዉ።

#EthioFM #አባቱመረቀ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

ከኢትዮጵያ ወደሀገሩ አሜሪካ እንደተመለሰ የተነገረለት አንድ የአሜሪካ የባሕር ኃይል ወታደር በኮሮና ቫይረስ መያዙን Talk Media News ዘግቧል። ለጊዜው ወታደሩ ከኢትዮጵያ መቼ እንደተመለሰ የሰጠው ፍንጭ የለም።

የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር እንዲሁም የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በጉዳዩ ዙሪያ እስካሁን የሰጡት መረጃ የለም። በጉዳዩ ላይ የሚሰጡ መረጃዎች ሲኖሩ እንድታነቡት የምናደርግ ይሆናል።

http://www.talkmedianews.com/featured/2020/03/09/marine-back-from-ethiopia-tests-positive-from-covid-19-at-ft-belvoir-virginia/

#TalkMediaNews #EthioFM
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኮቪድ-19 የሚያዙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ነው!

በአለም አቀፍ ደረጃ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ2,000,000 በላይ ሆኗል። ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 485,304 ሺህ ደሷል። የሞቱ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 126 ሺህ 811 ደርሷል፡፡

- ዩናይትድ ስቴትስ እስካሁን ባለው መረጃ ከ614 ሺህ በላይ የሚሆኑ ዜጎቿ በዚሁ በሽታ ሲያዙ ከ26 ሺህ በላይ ያህሉ ህይወታቸውን አጥተዋል። በትላንትናው እለት ብቻ በአሜሪካ 2 ሺህ 385 ሰዎች በበሽው ሂወታቸው አልፏል፡፡

- በካናዳ የሟቾች ቁጥር ከ900 በልጧል። ባለፉት 24 ሰዓት 123 ሰዎች ሞተዋል። በሀገሪቱ በቫይረሳ የተያዙ ሰዎች ደግሞ ከ27 ሺህ በላይ ሆኖ ተመዝግባል፤ ከዚህ መካከል 1,383 የሚደርሰው ኬዝ በአንድ ቀን የተመዘገበ ነው።

- በቱርክ በቫይረሱ የሚያዙ ሰዎች እየጨመረ ነው። ባልፉት 24 ሰዓት 4,062 አዲስ ኬዝ ሲመዘገብ፤ 107 ሰዎች ሞተዋል።

- በተመሳሳይ በሩሲያም ቫይረሱ በፍጥነት እየተስፋፋ ነው፤ ባለፉት 24 ሰዓት 2,774 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል።

- በአፍሪካ በበሽታው የተያዙ ሰዎች ቁጥር በየቀኑ እየጨመረ ሲሆን እስካሁን ድረስ ከ15 ሺህ በላይ የሚሆኑ ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል፡፡ በአፍሪካ የሟቾች ቁጥር ደግሞ 790 ደርሷል።

#ETHIOFM #BBC #AFP #SKYNEWS
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Ventilators

ደቡብ ሱዳን 5 ምክትል ፕሬዘዳንቶች ያላት ቢሆንም ለ11 ሚሊዮን ህዝብ የሚሆን 4 የኦክስጅን መስጫ ማሽኖች አላት ሲል ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ ዘግቧል፡፡

ምንም እንኳን ለኮሮና ቫይረስ ህመምተኞች ለመተንፈስ የሚያግዛቸው ቬንትሌተር ማሽን በደቡብ ሱዳን ካሉ ምክትል ፕሬዘዳንቶች እኩል ባይሆንም አንድም እንኳን ከሌላት ሱማሊያ በቁጥር ልቆ ታይቷል፡፡ በሱማሊያ ምንም አይነት የመተንፈሻ መሳሪያ እንደሌለ ዘገባው ያስረዳል፡፡

ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ 5 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ሲሆን 3 ቬንትሌተር ብቻ ነው ያላት ፤ ላይቤሪያም በተመሳሳይ ከ6ቱ 3ቱ ብቻ ናቸው የሚሰሩት።

ቡርኪና ፋሶ ለ20 ሚሊየን ህዝብ 11 ነው ያላት ፤ በኬኒያ 257 ፤ በጋና 200 ፤ ሱዳን 80 አላቸው፡፡ በሀገራችንም 575 ቬንትለተሮች እንዳሉ ዘገባው ጠቁሟል፡፡

በአፍሪካ በአሁን ሰዓት በአጠቃላይ 2,000 ቬንትለተሮች ያሉ ሲሆን ከ46 ሺህ በላይ ሰዎች በሞቱባት በአሜሪካ ብቻ 17 ሺህ ቬንትሌተሮች እንዳሉ ነው ዘ ኒዉ ዮርክ ታይምስ በዘገባው ያስረዳው፡፡

#ETHIOFM #DERESEAMARE
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia