TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#EZEMA

ብልጽግና ፓርቲ የህዝብና የመንግስት ሃብትን ለምርጫ ቅስቀሳ እየተጠቀመ መሆኑን የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ኢዜማ አስታወቀ። የፓርቲው መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በወቅታዊ እና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ በአዲስ አበባ መግለጫ በመስጠት ላይ ናቸው።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ በዚህ ጊዜ እንደተናገሩት ብልጽግና ፓርቲ የህዝብን እና የመንግስትን ገንዘብ ለምርጫ ቅስቀሳ እያዋለ ነው ብለዋል።

በመሆኑም የብልጽግና ፓርቲ ድርጊት ሌሎች ፓርቲዎችን ወደ አላስፈላጊ መንገድ የሚመራ ከማድረጉ በተጨማሪ የአገሪቱን የዲሞክራሲ ግንባታ ስለሚጎዳ ከዚህ ድርጊቱ እንዲታቀብ አሳስቧል። ምርጫ ቦርድም ይሄንን ህገወጥ እንቅስቃሴ እንዲያስቆም ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጠይቀዋል።

#ኢትዮኤፍኤም107.8 #ሔኖክአስራት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#EthioTelecom

ኢትዮ - ቴሌኮም [ethiotelecom] የብሮድባንድ ኢንተርኔት የታሪፍ ቅናሽ ማድረጉን አሳውቋል። ማሻሻያውም ለመኖርያ ቤት 69 በመቶ ቅናሽ ፣ ለድርጅቶች 65 በመቶ፣ VPN ደግሞ 72 በመቶ ቅናሽ መደረጉ ተገልጿል።

ማሻሻያው በዋጋ ብቻ ሳይሆን በፍጥነትም ጭምር መሆኑ ተሰምቷል። የኢንተርኔት አገልግሎቱ ለመኖርያ ቤት የ 3 በመቶ ፍጥነት ፣ ለድርጅቶች 4 በመቶ ፍጥነት ይጨምራል።

PHOTO : #TikvahFamily [Andinet]

#ETHIOFM #ሔኖክአስራት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia