የኦነግ ወታደራዊ ዩኒፎም ተያዘ እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው!

በወልዲያ የፍተሻ ጣቢያ ላይ የተያዘው ወታደራዊ ዩኒፎርም መሰል አልባሳት የእኔ ነው ሲል የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ መነሻዉን መቐለ ያደረገ አይሱዙ ወልዲያ የፍተሻ ጣቢያ ላይ ሲደርስ በፍተሸ ጣቢያ ሰራተኞች ተይዞ ፍተሻ እየተደረገበት ይገኛል፡፡ምክንያቱ ደግሞ የጫነዉ አልባሳትን ምንነት ለማረጋገጥ ነዉ ተብሏል፡፡

የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ሰለሞን ወርቁ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት፤ መኪናዉን ጭኖ ሲንቀሳቀስ የነበረዉ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ቁጥጥርና ጥበቃ ሰራተኞች /ስካዉት/ የሚለብሱት ዩኒፎርም ነበር ብለዉናል፡፡ መኪናዉም 3 ሺህ የዩኒፎርም አልባሳትና 170 ጃኬቶችን ጭኖ ከመቀሌ አልመዳ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ እንደነበረም ነዉ የተናገሩት፡፡

አልባሳቱ #የተጫነዉ በግል መኪና መሆኑና አልባሳቱ የኛ መሆኑን የሚያመለክት ደብዳቤ በአሽከርካሪዉ እጅ አለመገኘቱ ለጥርጣሬዉ መነሻ እንደሆነም አቶ ሰለሞን ገልጸዋል፡፡ አሁን ላይ ከሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ተነጋግረን ማረጋገጫ ደብዳቤ እንድንጽፍ በጠየቁን መሰረት ደብዳቤ ጽፈናል፤በነገዉ እለትም መኪናዉ ወደ አዲስ አበባ ይንቃቀሳል ብለን እንጠብቃልን ነዉ ያሉት፡፡

ከዚህ ባሻገር ግን አልባሳቱ የኦነግ ነዉ ተብሎ በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰዉ ወሬ #ከእዉነት_የራቀ_ነዉ፤ አልባሳቱ የኛ ነዉ፤ ለዱር እንስሳት ጥበቃ ለመተማሩ ሰራተኞች የተዘጋጀ ዩኒፎርም ነው ብለዋል፡፡ በኢትዮጵያ በፌደራል ደረጃ በሚተዳደሩ 13 ብሄራዊ ፓርኮች 790 ስካዉቶች በስራ ላይ ተሰማርተዉ ይገኛሉ፡፡

Via #ETHIOFM
@tsegabwolde @tikvahethiopia