TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አቶ #ልደቱ_አያሌው ስለቅንጅት ለአንድነት እና ለዴሞክራሲ ፓርቲ መፍረስ በግልጽ ከፕሮፌሰር #ብርሃኑ_ነጋ ጋር ፊት ለፊት ቀርበው መወያየት እንደሚፈልጉ አስታወቁ፡፡ አቶ ልደቱ አያሌው ለአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት እንዳስታወቁት የ1997 ዓ.ም የምርጫ ሂደትና የቅንጅት መፍረስን አስመልክቶ #በግልጽ በሕዝብ ፊት አልያም በተናጠል ሕዝቡ ያውቀው ዘንድ ከፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጋር ፊት ለፊት ቀርበው መነጋገር እንደሚፈልጉ አስታውቀዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ባህር ዳር⬆️

‹ለአንቺ ነው ኢትዮጵያ › በሚል ርዕስ አቀባበል እንደሚደረግ የአቀባበል ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ዳዊት ሞላ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

የንቅናቄው ከፍተኛ አመራሮች ፕሮፌሰር #ብርሃኑ_ነጋ እና #አንዳርጋቸው_ፅጌን ጨምሮ ሌሎች የግንቦት ሰባት አባሎች አርብ ማታ ባሕር ዳር ይገባሉ፡፡

አርበኞቹ ለነፃነት ሲባል ላበረከቱት አስተዋፅኦ የክብር አቀባበል እንደሚደረግ ሰብሳቢው ተናግረው በአቀባበሉ ሥነ-ስርዓቱም "ለአርበኛ ታጋዮች ቅድሚያ ይሰጣል" ብለዋል፡፡

ቅዳሜ መስከረም 5/2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 2 ሰዓት በባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የአቀባበል ሥነ-ስርአቱ ይካሄዳል፡፡ ከሰዓት በኋላ ደግሞ የውይይት መድረክ መዘጋጀቱን አቶ ዳዊት ገልጸዋል፡፡

©AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ፌደራል ፖሊስ-አልታገስም አለ⬆️

ወደ ሀገር ቤት የሚገቡ የድርጅት አመራሮችን ለመቀበል በሚደረግ ቅድመ ዝግጅት ላይ በወጣቶች መካከል እየተፈጠረ ያለውን ግጭትና ህገወጥ ተግባር ከዚህ በኋላ #እንደማይትገስ የፌደራል ፖሊስ አስታወቀ።

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል ከአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር የስራ አስፈጻሚ አባል አቶ ኢብሳ ነገዎ ጋር በመሆን መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫው ላይም ኮሚሽነር #ዘይኑ_ጀማል፥ በትናንትናው እለት እና ዛሬ ወደ ሀገር ቤት የሚገቡ የድርጅት አመራሮችን ለመቀበል በሚደረግ ቅድመ ዝግጅት ላይ በወጣቶች መካከል ግጭት መፈጠሩን አስታውቀዋል።

በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራውን #የኦነግ ቡድን ለመቀበል እየተደረገ ባለ ቅድመ ዝግጅት ወቅት ወጣቶች የድርጅቱን አርማ ለመስቀል ዝግጅት እያደረጉ ነበር፤ ይህንን የከለከላቸው አካል የለም ያሉት ኮሚሽነር ዘይኑ፥ ሆኖም ግን አስፋልትን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማትን እንዳያቀልሙ ተከልክው፤ ይህንንም ተወያይተን እሺ ብለው ተቀብለው ትተው ነበር ብለዋል።

ሆኖም ግን ማንም ያልፈቀደላቸው አካላት የእነሱን ባንዲራ አውርደው የሌላ ለመስቀል ሲሉ ግጭት ተፈጥሯል ሲሉም ገልፀዋል።

ግጭቱ ለማንም ጠቃሚ አይደለም ያሉት ኮሚሽነር ዘይኑ፥ ችግሩን #በውይይት መፍታት ሲቻል ወደ አላስፈላጊ ግጭት መግባት ተገቢ አይደለም ሲሉም ተናግረዋል።

ፖሊስ የህግ የበላይነትን የማስከበር ሀላፊነት ስላለበት ከዚህ በኋ እንዲህ አይነት #ግጭቶችን በትእግስት እንደማያልፍም ኮሚሽነር ዘይኑ አሳስበዋል።

የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር #ብርሃኑ_ነጋ፥ የዴሞክራሲ ስርዓትን እንገንባ ብለን ስንሰና ስርዓቱን ለመገንባት የሚያስፈልግ እነዚህን ባህሪያትን ተቀብለን ካልተነሳን ግን ስርዓቱን መገንባት እንችልም ብለዋል።

የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ውስጥ ልዩነቶችን መቀበል የግድ ነው ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፥ ልዩነቶቹ ደግሞ ሀሳቦችን፣ አርማዎችን እና ባንዲራዎችን ሊያጠቃልል ይችላል ብለዋል።

ትናንትና እና ዛሬ በአዲስ አበባ የተስተዋሉ ችግሮች ደግሞ ከዚህ ጋር የሚፃረሩ ነው ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፥ ማንኛውም አካል ስሜቴን ይገልፅልኛል ያለውን አርማ የመያዝ እና የማውለብለብ #መብት አለው ሲሉም ተናግረዋል።

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር የስራ አስፈጻሚ አባል አቶ #ኢብሳ_ነገዎ በበኩላቸው፥ ሰሞኑን በአዲስ አበባ እና አካባቢዋ የተስተዋለው ችግር #ተቀባይነት የሌለው መሆኑን አንስተዋል።

ወጣቱም ከዚህ አይነት እንቅስቃሴዎች ሊቆጠብ እንደሚገባም አቶ ኢብሳ ጥሪ አስተላልፈዋል።

አሁን ላይ እየታየ ያለው ግጭት እና ያልተገባ #ፉክክር ድርጅታቸውን የማይወክል መሆኑንም ነው አቶ ኢንብሳ ተናግረዋል።

©Fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፌሰር #ብርሃኑ_ነጋ የአንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ አባል በመሆን ተሹመዋል። ፕሮፌሰሩ እስከ ምርጫ 97 ድረስ በዩኒቨርሲቲው የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል ያለምንም ክፍያ በመምህርነት ማገልገላቸው የሚታወቅ ነው።

Via Petros Ashenafi Kebede
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አበኞች ግንቦት 7~ደብረ ማርቆስ🔝

"ጥፋትን በጥፋት ለማረም መሞከር ተገቢ አይደለም!!" ፕ/ር #ብርሃኑ_ነጋ
.
.
#የአርበኞች_ግንቦት_7 ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ታላቅ ህዝባዊ ዝግጅት በደብረማርቆስ ተካሄደ። የተለያዩ ጥሪ የተደረገላቸው የሀገር ሽማግሌዎችና ባልሰጣናትም በቦታው ተገኝተው ነበር።

አግ7 #የዜግነት_ፖለቲካ ብቸኛው ብሎም ሀገራችን ከገባችበት የዘርና የመከፋፈል አደጋ የምንወጣበት ስልት ነው ብሎ እንደሚያምን አመራሮቹ ተናግረዋል።

በአደባባይ የውጣው ህዝብ ለድርጅቱ ያላቸውን እምነት በመግለፅ መሪዎቹ ለሃጋራቸው ያበረከቱትን አስተዋጽኦ #አመስግነዋል

#አዘጋጆቹም ህዝቡን በማመስገን ህዝቡ ወደ ድርጅቱ የደብረማርቆስ ቢሮ እየመጣ እንዲመዘገብና አባል እንዲሆን ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

ምንጭ፦ አግ7
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አግ7~ደብረ ማርቆስ🔝

''ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ከአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን እና ከብሄራዊ እርቅ ኮሚሽን ጎን ልንቆም ይገባል'' አርበኞች ግንቦት ሰባት
.
.
በሃገሪቱ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን ከአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን እና ከብሄራዊ እርቅ ኮሚሽን ጎን ልንቆም ይገባል ሲል የአርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ #አሳሰበ፡፡

የአርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ከደብረ ማርቆስ ከተማ ነዋሪዎች፣ ከደጋፊዎቹ እና ከአባላቱ ጋር ዛሬ በደብረ ማርቆስ ከተማ ዉይይት አካሂዷል፡፡

የፓርቲዉ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር #ብርሃኑ_ነጋ የጎጃም ህዝብ በተለያዩ ጊዜያት ፍትሃዊ አሰራር እንዲሰፍን እንደ ሌሎች የሃገሪቱ ነዋሪዎች ሁሉ ለለዉጡ መስዋዕትነት መክፈሉን ተናግረዋል፡፡

"ወገኖቻችን የደሙላት ፣ ህይወታቸዉን ያጡባትን ሃገር ሰላም አስጠብቀን ለልጅ ልጆቻችን ልናወርስ ይገባል፤ ይህ ካልሆነ ግን ወገኖቻችን ደግመን እንደገደልናቸዉ ነዉ የሚቆጠረዉ" ነው ያሉት፡፡

ሰላም የመኖርና ያለመኖር የህልዉና ጉዳይ በመሆኑ የአስተዳደር ወሰን እና የማንነት ጉዳዮች ኮሚሽን እና የብሄራዊ እርቅ ኮሚሽን ለሚሰሩት ስራ ከጎናቸዉ ልንቆም ይገባልም ብለዋል፡፡

አብመድ እንደዘገበው የአርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ጸሃፊ አቶ #አንዳርጋቸዉ_ጽጌ ስልጣን በህዝብ የተገነባ እንዲሆን እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አርበኞች ግንቦት 7🔝

በዛሬው እለት አርበኞች ግንቦት 7 በአዊ ዞን እንጅባራ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም እና በአዊ ባህል ማዕከል አዳራሽ የተሳካ እና ደማቅ ሕዝባዊ ውይይት አድርጓል። በርካታ ሕዝብ በተገኘበት በዚሁ ስብሰባ የንቅናቄው ሊቀመንበር ፕ/ር #ብርሃኑ_ነጋ ፣የሰማያዊ ፖርቲ ሊቀመንበር አቶ #የሽዋስ_አሰፋ ፣ የኢዴፓ ሊቀመንበር ዶ/ር # ጫኔ_ከበደ እና የቀድሞ የሰማያዊ ፓርቲ የውጭ ጉዳይ ሃላፊ #አለነህ_ማህፀንቱ ተገኝተው ከስብሰባው ታዳሚዎች የተነሳላቸውን ጥያቄዎች እና አስተያየቶችን በመቀበል ስለ #ዜግነትን መሠረት ያደረገ ፖለቲካን እና # ማኅበራዊፍትህን በተመለከተ ለታዳሚው ሰፊ ገለፃ አድርገዋል።

Via Patriotic Ginbot 7
@tsegabwolde @tikvahethiopia