አርበኞች ግንቦት 7🔝

በዛሬው እለት አርበኞች ግንቦት 7 በአዊ ዞን እንጅባራ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም እና በአዊ ባህል ማዕከል አዳራሽ የተሳካ እና ደማቅ ሕዝባዊ ውይይት አድርጓል። በርካታ ሕዝብ በተገኘበት በዚሁ ስብሰባ የንቅናቄው ሊቀመንበር ፕ/ር #ብርሃኑ_ነጋ ፣የሰማያዊ ፖርቲ ሊቀመንበር አቶ #የሽዋስ_አሰፋ ፣ የኢዴፓ ሊቀመንበር ዶ/ር # ጫኔ_ከበደ እና የቀድሞ የሰማያዊ ፓርቲ የውጭ ጉዳይ ሃላፊ #አለነህ_ማህፀንቱ ተገኝተው ከስብሰባው ታዳሚዎች የተነሳላቸውን ጥያቄዎች እና አስተያየቶችን በመቀበል ስለ #ዜግነትን መሠረት ያደረገ ፖለቲካን እና # ማኅበራዊፍትህን በተመለከተ ለታዳሚው ሰፊ ገለፃ አድርገዋል።

Via Patriotic Ginbot 7
@tsegabwolde @tikvahethiopia