TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሁን🔝ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #ዐቢይ_አህመድ 81 ተፎካካሪ የፖለቲካ ድርጅቶችን ያሳተፈውን ስብሰባ ጀምረዋል።

ምንጭ:- ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update በሰብአዊ መብት ጥሰት፣ በሙስናና የተደራጀ ሌብነት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎችን #ብሔርን መሰረት ተደርጐ እርምጃ እየተወሰደ ነው በሚል የሚሰጡ አስተያየቶች የተሳሳቱ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ገልፀዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update ጠ/ሚር #ዐቢይ አህመድ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ተቋማዊ ለዉጥ የጋራ ኮሚቴ ጋር ታሕሳስ 4, 2011 ተወያዩ። ውይይቱም በዋናነት የኮሚቴውን የ5 ወራት የግጭት አፈታት እንቅስቃሴዎችና የተገኙ ውጤቶችን ገምግሟል። ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ እስካሁን የተመዘገበውን ለውጥ በተለይም በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የጋራ የሆነ አንድነትን የሚያጠናክር ተቋም መመስረቱን መንግስታቸው እንደሚያደንቅ ገልፀዋል። በተጨማሪም ጠ/ሚሩ የታዩትን መግባባቶችን ለማጠናከርና እነሱንም ለማደናቀፍ የሚሰሩ ማናቸውንም እንቅፋቶች ለመከላከል የመንግስታቸውን ድጋፍ ገልፀዋል።

ምንጭ፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማስታወሻ🗓

በነገው ዕለት ጠ/ሚ ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ከመላ ሀገሪቱ ከተውጣጡ መምህራን ጋር ይወያያሉ።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠ/ሚር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ዛሬ ከመምህራን ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ስለህዳሴው ግድብ ፕሮጀክት ከተናገሩት የተወሰደ...
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"መንግስት ሀገር መምራት አልቻለም፣ አቅም አጥሮታል፣ የምትሉ ወገኖች መግረፍና ማሰር ነው ያልቻልነው እንጂ መምራት የምንችልና ለውጥ ያመጣን መሆኑን ዓለም መስክሮልናል'' ጠ/ሚር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ከመላ ሀገሪቱ ከተውጣጡ መምህራን ጋር ባደረጉት ውይይት ከተናገሩት የተወሰደ...

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶ/ር አብይ ሀዘናቸውን ገልፁ‼️

ጠቅላይ ሚኒስትር #ዐቢይ_አህመድ በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ውስጥ በሰላማዊ ዜጎች ላይ በተፈጸመው ጥቃት መንግሥት የተሰማውን ሀዘን ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቃቱ በንጹሃን ዜጎች ላይ የተፈጸመ #ዘግናኝ ድርጊት ሲሉ ኮንነውታል። ለተጎጂ ቤተሰቦችና በሀዘን ላይ ለሚገኙት መላው ኬንያውያን የተሰማቸውን ልባዊ ሀዘን ገልጸዋል። ትናንት ናይሮቢ ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት 14 ሰዎች መገደላቸውን የኬንያው ፕሬዚዳንት #ኡሁሩ_ኬንያታ ዛሬ መግለጻቸው ይታወሳል።

ምንጭ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዳዲስ ሹመቶች‼️

ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ከጥር 9 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ ለተለያዩ የመንግስት ሀላፊነት ቦታዎች #ሹመቶችን ሰጥተዋል፡፡

እንደ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት መረጃ መሰረት፦

•አቶ ፍራኦል ተፈራ የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነቶች ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣

•አቶ ማተቤ አዲስ የኮንስትራክሽን ስራዎች ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር፣

•አቶ እዮብ አወቀ የስደተኞና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣

•ዶ/ር መብራህቱ ገ/ማሪያም የኢትዮጵያ ጨረራ መከላከያ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣

•አቶ መስፍን ነገዎ የኮንስትራክሽን ስራዎ ተቆጣጣሪ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር፣

•አቶ እስማኤል አሊሴሮ በሚንስትር ዴኤታ ማእረግ የሰላም ሚንስትር አማካሪ፣

አቶ ታምሩ ግንበቶ የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነቶች ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾመዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ከፓርላማ አባላት ለተነሱት ጥያቄ ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች:-

• ዴሞክራሲን ለመገንባት መንግስት አርቆ አሳቢና ሆደሰፊ መሆን አለበት

• 20 የሚጠጉ የታጠቁም ያልጠተቁም የፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ አገር ተመልሷል፣ ይህንን እንደ ድል ማየት ያስፈልጋል፡፡ እሱን ድል ዘንግተን ከመግባታቸው ጋር ተያይዞ የተፈጠሩ ችግሮች ላይ ማተኮር የለብንም

• የቀረበው የሰላም ጥሪ የሰላም መርህን የተከተለ ነው

• ከሁሉም ፓርቲዎች ጋር ተመሳሳይ መርህን የተከተለ ድርድር ነው የተደረገው፡፡

• ውግያ አያስፈልግም፣ ለበርካታ ዓመታት ሲንዋጋ ቆይተናል፤ የጦር መሳሪያ ድምጽ መሰመት የለበትም፣ በሀሳብ እንወያይና እናሸንፍ ነው ያልነው

• ከውጭ የገቡት ፓርቲዎች ዴሞክራሲን ለመገንባት የሚሰሩ አሉ፣ ያን የማያደርጉ አንድ እግራቸውን አዲስአባባ አንድ እግራቸውን ውጭ አድርገው የሚጫወቱ አሉ እሱ አካሄድ ውጤታማ አያደርግም፡፡

• በሀሳብ አሸናፊ ለመሆን ነው መስራት ያለብን፡፡

• ችግር እየፈጠሩ ከችግር ለማትረፍ የሚሞክሩ ኃይሎች አሉ

• የፖለቲካ ምህዳሩ ሰፊቷል፣ ረጅም ርቀት መሮጥ የማይችሉ ፓርቲዎች ትንፋሽ ያጥራቸዋል፡፡ እነዚህ ፓርቲዎች ያላቸው ምርጫ ሀሳብ ወዳላቸው ፓርቲዎች ሰብሰብ ማለት ነው

• ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ዴሞክራሲ ሰላም ነው የሚንሰረው፤ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት፣ ሰላም ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ነገር ሲኖር የማያደጋም እርምጃ እንወስዳለን

Via ETV
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ከፓርላማ አባላት መከላከያን አስመልክቶ ለተነሱት ጥያቄ ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰዱ አንኳር ነጥቦች:-

• የመከላከያ ሰራዊት በሰፈር ውስጥ አንድ ሌባ ቦርሳ ይዞ ሲሮጥ ለምን ቦርሳ አላስጣልክም ብሎ መጠየቅ የለበትም፡፡

• የአገር ሉዓላዊነት ተደፍሮ መከላከያ ዝም ያለበት ጊዜ የለም፡፡ ያ ነው የመከላከያ ሰራዊት ስራ፡፡

• ችግሮች ሲገጥሙ መከላከያ አስፈላጊውን መስዋዕትነት ከፍሎ ችግሮችን ማረጋጋት ችሏል፡፡

• መከለካያ በአገር ውስጥም በውጭም ሕይወቱን ገብሮ ለዚህች አገር እየሰራ ነው

• ወለጋ ውስጥ የክልሉ መንግስት ጥሪ ሲያደርግ መከላከያ ችግሩን ለመፍታት ሁለት ወር አልፈጃበትም፡፡

via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia