TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ወቅታዊ የሶማሌ ክልል ዳሰሳ⬇️

በአሁን ሰዓት በሶማሌ ክልል የተረጋጋ ሁኔታ ነው ያለው። ሰዎች እየተንቀሳቀሱ መገበያየት፤ በሰላም መውጣት እና መግባት ይችላሉ። ነገር ግን ይህ ሰላም ዘላቂና አስተማማኝ እንዲሆን መንግስት በክልሉ ላይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ እንደሚገባ ለጉዳዩ ቅርብ የሆነ ሰው ገልፆልኛል።

የሱማሌ ክልል ልዩ ሀይል የሀገር መከላከያ ሰራዊቱ እና የፌደራል ፖሊስ ቦታውን እንዲለቅለት የመፈለግ አዝማሚያ አሳይቶ ነበር። የሀገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስ ቦታውን መልቀቅ አካባቢውን እንዲረጋጋ እንደማያደርገው እና ቦታውን መልቀቁም ለአካባቢው ሰላም ዋስትና ስለማይሆን የሀገር መከላከያ እና የፌደራል ፖሊስ በክልሉ የሰላም ማስከበር እንደሚቀጥል ከስምምነት ተደርሶ በትብብር እየተሰራ ይገኛል።

ለጉዳዩ ቅርበት ያለው የቻናላችን ቤተሰብ እንዳጫወተኝ መንግስት የሱማሌ ክልልን በአግባቡ እንዲቆጣጠር የተለያዩ ስራዎችን መሰራት አለበት።

የሱማሌ ክልል ልዩ ፖሊስ አባላት የ4 ወር ያልተከፈላቸው ደሞዝ አላቸው። ያ ክፍያ በአግባቡ ሊከፈላቸው እንደሚገባም ነው የተጠቆመው። የተወሰኑ ትጥቅ እንዲፈቱ የተደረጉም የልዩ ፖሊስ አባላት አሉ እነኚህም ምንም አይነት ነገር አንዳልተደረገላቸውና በዚህም ምክንያት ወደ ጫካ መግባታቸውን ነው የተሰማው።

ጫካ ውስጥ ገብተዋል ተብለው የሚታመኑት ቡድኖችም እርስ በእርሳቸው የተከፋፈሉ ናቸው። ግማሹ ትክክለኛ ደሞዛችን ተከፍሎን ወደ ስራ እንግባ፤ ሰላም እንፈልጋለን የሚሉት ሲሆኑ ሌላኛው ቡድን ደግሞ "አብዲ ኢሌ" የቀድሞው ፕሬዘዳንት ከእስር ይፈቱልን ቦታውን እኛ እንቆጣጠር የሚሉት ናቸው። ወ ደ ጫካ ገብተዋል ተብለው ከሚታመኑት አብዛኛዎቹ የአብዲ ኢሌ ደጋፊ እንደሆኑ ይነገራል።

በሶማሌ ክልል ያለው የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የፌደራል ፖሊስ በልዩ ጥንቃቄ ነው የሰላም ማስከበር ስራውን እየሰራ የሚገኘው።

በነገራችን ላይ የሱማሌ ክልል ልዩ ሀይል ከባባድ መሳሪዎችን ነው በእጁ ላይ ያሉት። ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ በሶማሌ ክልል ጉዳይ ቁርጠኛ እና ዘላቂ ምፍትሄ ላይ መድረስ አለባቸው። ከክልሉ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት መደረግ አለበት። ልዩ ሀይል ከተባለው ሰራዊትም ጋር ውይይት ሊደረግ ይገባል። ብዙ ችግሮች እንዳሉባቸው ነው የሚናገሩት። የሚበሉት እንደሌላቸውና ገንዘብን ከጨረሱ እንደቆዩ ነው የሚናገሩት። ምን አይነት ችግር በልዩ ሀይል ውስጥ እንዳለ ሊሰማና ውይይት ሊደረግ ይገባል።

ይኸን መረጃ ያደረሰኝ ወዳጄ ጨምሮ እንደነገረኝ አንዳንድ የልዩ ሀይል አባላት ካለባቸው #ችግር የተነሳ ሳይወዱ በግድ ወደ ጫካ እየገቡ እንደሆነና ከተቃዋሚ ሀይሎች ጋር ለመቀላቀል እየተገደዱ እንደሆነ ገልፆልኛል።

ዶክተር አብይ በቅርቡ ከሆነው ሁኔታ አንፃር ዝርዝር መግልጫ ባለመስጠታቸው ብዙሀኑን ህዝብ ግርታ ውስጥ ከቶ ነበር። በአሁን ሰዓት በክልሉ የሰላም ማስከበር ስራ ላይ የተሰማሩት የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የፌደራል ፖሊስ፣ የየከተማው ፖሊስ እና ልዩ ሀይሉ ናቸው።

በሌላ በኩል...⬇️

ህዝቡ የተዘረፈበት ንብረት እንዲመለስልት፤ እንዲሁም በቂ የምግብ አቅርቦት እንዲሟላ እየጠየቀ ይገኛል።

# በሱማሌ ክልል የሰላም ምስከበር ሁኔታ ላይ ቅርበት ያለው የቻናላችን ቤተሰብ አካል የሆነው ሰው ይህን መረጃ ሊሰጠኝ የፈለገው በክልሉ ዘላቂ መፍትሄ እንዲኖር ከተፈለገ ጥልቅ ውይይት ሊደረግ እንደሚገባው እና የዶክተር አብይ መንግስት በዚህ ላይ በስፋት እንዲሰራ ለመጠቆም ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሁን አዲስ አበባ⬆️ነገ በአዲስ አበባ የሚጠበቀው የኦነግ አቀባበል ካለምንም #ችግር እንዲጠናቀቅ በከተማ ደረጃ ምን ያህል በቂ ዝግጅት እንደተደረገ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር #ታከለ_ኡማ ከፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ ከእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መቆጣጠርና መከላከል ባለስልጣን፣ ከፀጥታና ደህንነት፣ ከአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር እና ከመከላከያ ሰራዊት ጋር ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ።

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአዲስ አበባ ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ ነገ በአዲስ አበባ ለሚካሄደው የኦነግ የድጋፍ ላይ #ችግር እንፈጥራለን በሚሉ ወጣቶች ላይ #እርምጃ እንደሚወስዱ አስታወቁ፡፡ ከዓለማው ዉጭ በሚንቀሳቀሱ ወጣቶች ፖሊስ #እርምጃ ይወስዳል ብለዋል፡፡

©AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ድሬዳዋ ፖሊስ⬆️

በድሬዳዋ ከተማ በአንዳንድ አካባቢዎች በቤቶች ላይ ምልክት መደረጉን ተከትሎ ምልክቱ የጥቃት ነው በሚል በማህበራዊ ድረ ገፅ #ስጋት
ፈጣሪ ሀሳቦች ተሰራጭተዋል። በመሆኑም የአስተዳደሩና የፌዴራል የፀጥታ አካላት ከትላንት ጀምሮ #የተጠናከረ ጥበቃና ክትትል እያደረጉ
መሆኑን የድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽን ሕዝብ ግኑኝነት ዲቪዥን ሀላፊ ዋና ሳጂን ባንታለም ግርማ ገልፀዋል።

እስከ አሁን በተጨባጭ የተፈጠረ #ችግር የለም ያሉት ዋና ሳጂን ባንታለም ግርማ ህብረተሰቡ በማህበራዊ ድረ ገፅ በሚለቀቁ መረጃዎች ተደናግሮ ለሁከትና ግጭት በር ሳይክፈት የለት ተለት ሠላማዊ ኑሮውን ሊቀጥል ይገባል ብለዋል። ብጥብጥ ለመፍጠር የሚፈልግ አካል ካለም በድሬዳዋ #የማይሳካ መሆኑና ፖሊስም የማይታገስ መሆኑን አውቆ ከጥፋት ድርጊት እንዲታቀብ አሳስበዋል።

ህብረተሰቡ ስጋት ፈጣሪ እንቅስቃሴዎች ባየ ጊዜ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥም ዋና ሳጅኑ ጠይቀዋል፦

☞025 111 16 00
☞025 111 52 11

በተያያዘ ፦ ሀምሌ 29 - 2010 በድሬዳዋ ለ13 ንፁሀን ዜጎችና ህልፈትና ለንብረት መውደም ምክንያት የሆነውን ሁከት ተከትሎ ፖሊስ የደረሰበትን የምርመራ ውጤት የፊታችን #ማክሰኞ ለሕዝብ በይፋ የሚገለጽ መሆኑን ዋና ሳጅን ባንታለም ግርማ አሳውቀዋል።

©Diredawa Mayoroffice
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በጋምቤላ ክልል ለታዩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ክፍተቶች በየደረጃው የሚገኙ የጋህአዴን #አመራር አካላት #ችግር መሆኑ ተገለጸ፡፡ ከክልል እስከ ወረዳ የሚገኙ የድርጅቱ የአመራር አካላት በጋምቤላ ከተማ ጥልቅ ግምገማ እያካሄዱ ይገኛሉ።

Via~ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትኩረት‼️አምቦ ዩኒቨርሲቲ (ዋናው ግቢ) ያለውን #ችግር የሚመለከተው አካል በጋራ ሊፈታው ይገባል ሲሉ ተማሪዎች ጠይቀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ‼️

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን የሆነው B-737-800 በበረራ ቁጥር ET338 የተመዘገበው አውሮፕላኑ ዛሬ ማለዳ በኡጋንዳ ሊያርፍ ሲል ከማኮብኮቢያው #ተንሸራቶ የመውጣት #ችግር እንዳጋጠመው አስታወቀ፡፡

በዛሬው ዕለት ከአዲስ አበባ ተነስቶ ወደ ኡጋንዳ የበረረው አውሮፕላኑ በኢንቴቤ አውሮፕላን ማረፊያ ለማረፍ ሲሞክር ከማኮብኮቢያ ሜዳው መስመር በመውጣቱ ችግሩ እንዳጋጠመው አየር መንገዱ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡

በአውሮፕላኑ ውስጥ በነበሩ መንገደኞችና የበረራ ሰራተኞች ላይ ምንም የደረሰ ጉዳት አለመኖሩንና በሰላም ወደ መንገደኞች ማቆያ መወሰዳቸውንም አየር መንገዱ አስታውቋል፡፡

በአጋጠመው የመንሸራተት ችግር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው አውሮፕላን ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳልደረሰበትም መግለጫው አመልክቷል፡፡

በችግሩ ምክንያት መስተጓጎል የተፈጠረባቸውን ደንበኞቹን አየር መንገዱ ይቅርታ ጠይቋል፡፡ ቀጣይ በረራ ላላቸው ደንበኞቹም የማመቻቸት ስራ እንደሚሰራ አመልክቷል፡፡

የአደጋውን ምክንያት ለማወቅ በምርመራ ላይ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል፡፡

ምንጭ፡- የኢትዮጵያ አየር መንገድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ከጅቢቲ ወደ የመን በማምራት ላይ ሳሉ በሰጠሙት ሁለት ጀልባዎች ውስጥ ከተጫኑት #ኢትዮጵያውያን ናቸው ከተባሉ ስደተኞች መካከል #የሞቱት ቁጥር ወደ 52 ከፍ ማለቱ ተነገረ። ዓለም አቀፉ የስደተኞች ጉዳይ ድርጅት በምህጻሩ IOM እንዳስታወቀው የህይወት አድን ሠራተኞች ከሁለቱ ጀልባዎች ተጨማሪ አስከሬኖችን በማግኘታቸው ትናንት 43 የነበረው የሟቾቹ ቁጥር ዛሬ ወደ 52 ከፍ ብሏል። 16 ሰዎች ከአደጋው መትረፋቸውን ድርጅቱ አስታውቋል። በአደጋው የሞቱት ሰዎች ትክክለኛ ቁጥር እስካሁን በግልጽ አልታወቀም። ድርጅቱ አንደኛዋ ጀልባ 130 ሰዎችን አሳፍራ ነበር የሚል እምነት አለው። የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ያነጋገረው አንድ ከአደጋው የተረፈ የ15 ዓመት ወጣት ቁጥራቸው 80 ከሚሆን ኢትዮጵያውያን ጋር በአንደኛው #ጀልባ ተጭኖ እንደነበር ገልጿል። የጀልባዋ ነጂ ሞተሩ ከባድ #ችግር እንዳጋጠመው ከተናገረ በኋላ ጀልባዋ መስመጠም መጀመሯን እርሱ ግን ከባህር ውስጥ በጅቡቲ የባህር ጠረፍ ጠባቂ #ተጎትቶ መውጣቱን ወጣቱ ተናግሯል። ጦርነት እየተካሄደባት ቢሆንም ወደ #የመን የሚደረገው ስደት እንደቀጠለ ነው።

ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ሬድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፓይለቱ ችግር ገጥሞት ነበር‼️

የአውሮፕላኑ አብራሪ #ችግር ስላጋጠመው ወደ አዲስ አበባ #ለመመለስ ጠይቆ እንዲመለስ ተነግሮት እንደነበር የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረ ማሪያም ተናግረዋል። አውሮፕላኑ ከጆሃንስበርግ በረራው ሲመለስ ምንም አይነት የበረራ ችግርን የሚመለከት መረጃ እንዳልነበርና ከሶስት ሰዓት በላይም መሬት ላይ ቆይቶ እንደነበር አቶ #ተወልደ ገልፀዋል።

Via BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update ከሳምንታት በፊት በምእራብ ወለጋ #ነጆ_ወረዳ ሁምና ዋቀዮ በሚባል አከባቢ በአሰቃቂ ሁኔታ 5 ሰዎች በኦነግ ታጣቂዎች በተባሉ ኃይሎች መገደላቸዉ ይታወሳል። ከተገደሉት የ2ቱ የውጪ ዜጎች ዉስጥ የሕንድ ዜግነት ያለዉ ግለሰብ አስከሬኑ ለቤተሰቦቹ የተላለፈ ሲሆን ነገር ግን #የጃፖን ዜግነት ያላት ሁለተኛዎ ሞች አስከሬን የመለየት ስራ #ችግር እንደገጠመዉ እና አስከሬኗ አሁንም ቅዱስ ፖዉሎስ ሆስፒታል እንደሚግኝ ለማወቅ ተችሏል።

Via ዳዊት እንደሻው
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ኢትዮጵያ ምርጫ ማካሄድ የሚያስችል ሁኔታ ውስጥ አይደለችም-" የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮች

ኢትዮጵያ አሁን ላይ ቀጣዩን ብሄራዊ ምርጫ ማካሄድ የሚያስችል ሁኔታ ውስጥ እንደማትገኝ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ። ኢትዮጵያ የ2012 ብሄራዊ ምርጫን ማካሄድ የሚያስችል ሁኔታ ውስጥ እንደማትገኝና ለሰላምና መረጋጋት ቅድሚያ በመስጠት መስራት እንደሚገባ ኢዜአ ያነጋገራቸው የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ተናገሩ።

የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮቹ በህጉና በህገ መንግስቱ መሰረት ምርጫው በተያዘለት የጊዜ ገደብ ቢካሄድ ፍላጎታቸው ቢሆንም አሁን ከምርጫ ይልቅ በትኩረት መሰራት ያለበት በሰላም ጉዳይ ላይ መሆኑን ጠቁመዋል። ለዚህ ደግሞ ገዥውና ተፎካካሪ ፓርቲዎች ለብሄራዊ ምርጫው መሳካት የድርሻቸውን ሃላፊነት መወጣት አለባቸው ብለዋል። እንደ አስተያየት ሰጭዎቹ የአገሪቷ ሰላም ሳይረጋገጥ ”ምርጫ ካልተደረገ ሞቼ እገኛለሁ” ማለት አላዋቂነት ነው።

መራጩ ህዝብ የፖለቲካ ፓርቲዎችን አጀንዳ ጠንቅቆ ባልተረዳበት ሁኔታ ምርጫን ማካሄድ ኢ-ዴሞክራሲያዊነት መሆኑንም ያነሱ አሉ። የኦሮሞ ነጻነት አንድነት ግንባር ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ ዑመር መሃመድ ምርጫ ያለሰላምና መረጋጋት የማይታሰብ ነው ይላሉ።

ይሁንና አሁን አገሪቷ ያጋጠማትን #ችግር በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲፈታ በማድረግ የ2012 ምርጫን ማካሄድ አለባት ብለዋል። ለምርጫው በጣት የሚቆጠሩ ወራት የቀሩ ቢሆንም መንግስትና ባለድርሻ አካላት የሰላም ችግሩን በመፍታት ምርጫው በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲከናወን ጥረት ማድረግ አለባቸውም ነው ያሉት።
 
Via #ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia