TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
‹‹በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የፓለቲካ ፓርቲዎች እንቅሰቃሴ ማድረግ #ፈጽሞ አይፈቀድም፡፡›› ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ #ደመቀ_መኮንን

ክልከላው የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) #የሚያካትት እንደሆነም ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተሰምቷል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update ከላልይበላ ከተማ እና ከቅዱስ ላልይበላ ደብር የተወከሉ ልዑካን ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ #ደመቀ_መኮንን ጋር በቅርሱ ጥገና ዙሪያ ባደረጉት ውይይት ቅርሱን ከጉዳት ለመከላከል የተሰራው መጠለያ በዚህ ዓመት እንደሚነሳ ቃል እንደተገባላቸው ተናግረዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር #ደመቀ_መኮንን ሳዑዲ አረቢያ ናቸው። አቶ ደመቀ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ያቀኑት በሀገሪቱ በሚደረገው አለም አቀፍ የንግድ ጉባዔ ለመካፈል ነው። እግረ መንገዳቸውንም ከሳዑዲ ባለስልጣናት ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ይመካከራሉ ብሏል ቃል አቀባያቸው።

ምንጭ፦ ዋዜማ ራድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"የሰላም ውድ ዋጋ በግልፅ የሚስተዋለው ላፍታ ሲጓደል ነው!" ም.ጠ.ሚ/ር አቶ ደመቀ መኮንን
~~~~~<>~~~©

ዘላቂ የሃገር ሰላም ግንባታ ሂደት ውስጥ ሁሉም ዜጋ የበኩሉን መወጣት እንደሚገባው ም.ጠ.ሚ/ር አቶ #ደመቀ_መኮንን አሳሰቡ።

ም.ጠ.ሚ/ር አቶ ደመቀ መኮንን የሰብዓዊ መብት ተሟጋች እና የሰላም አቀንቃኝ የሆኑትን አቶ #ኦባንግ_ሜቶን በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

በሰሜን አሜሪካ "ግድግዳውን እናፍርስ፤ ድልድዩን እንገንባ" በሚል መርህ ከወራት በፊት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዓብይ አህመድ የቀረበውን ጥሪ አቶ ኦቦንግ በአክብሮት ተቀብለው ወደ እናት ሃገራቸው በመመለሳቸው ም.ጠ.ሚ/ር አቶ ደመቀ ምስጋና እና አድናቆት ቸረዋል።

አቶ ኦባንግ በሃገር ቤት የወራት ቆይታ በተለያዩ ክልሎች እና ከተሞች እየተዘዋወሩ ሃገራዊ ለውጡ ቀጣይነቱ እንዲጎለብት ለትውልዱ የሚያስተላልፉት አነቃቂ መልዕክት ተቀባይነት ያለውና ሊጠናከር እንደሚገባ አቶ ደመቀ ተናግረዋል።

በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች የሚስተዋሉ ግጭቶችን ለመከላከል እና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የሚያደርገውን ሃገራዊ ጥረት ለማገዝ ፤ አቶ ኦባንግ በትውልዱ ዘንድ ያላቸውን ሰፊ የተደማጭነት እና የተቀባይነት ዕምቅ አቅም መንዝረው በቀጣይ እንዲደግፉ ም.ጠ.ሚ/ሩ
ጠይቀዋል።

የሰላም ውድ ዋጋ በግልፅ የሚታወቀው ላፍታ ሲጓደል በመሆኑ፤ በማህበረሰቡ ዘንድ ሰፊ የግንዛቤ እና የንቅናቄ ስራዎች እንደሚያስፈልጉ አቶ ደመቀ አስረድተዋል።

አቶ ኦባንግ በበኩላቸው በም.ጠ.ሚ/ር አቶ ደመቀ በተደረገላቸው አቀባበል እጅግ መደሰታቸውን በመግለጽ፤ ተስፋ የፈነጠቀው ሃገራዊ የለውጥ ጉዞ ዘላቂነት እንዲኖረው የግል ጥረታቸው እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል።

በውጭ ሃገር "ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ" የተሰኘ ድርጅት በመስራችነትና በዋና ዳይሬክተርነት የሚንቀሳቀሱት አቶ ኦባንግ፤ በሃገር ቤት በሚኖራቸው ስምሪት ድርጅቱ በሰብዓዊ መብት እና በሰላም ዙሪያ የህብረተሰቡን ግንዛቤ ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራ አስረድተዋል።

በቀጣይ በውጭ ሃገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በማስተባበር ትርጉም ያለው ስራ መስራት ፍላጐት እንዳላቸው
አቶ ኦባንግ ገልጸዋል።

በሃገር ውስጥ ህጋዊ ዕውቅና እና ምዝገባ አጠናቀው ከመንግሥት ጋር በቅንጅት ለመስራት ሰፊ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑንም አብራርተዋል።

በመጨረሻም ለሃገራዊ ሰላም ግንባታ የጋራ ጥረት እና ዘላቂ ውጤት መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ም.ጠ.ሚ/ር አቶ ደመቀ አረጋግጠዋል።

ምንጭ፦ Office of Deputy Prime Minister
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወራቤ🔝የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ዛሬ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ #ደመቀ_መኮንን፣ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ #ሚሊዮን_ማቲዎስ፥ በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ሂሩት ወ/ማርያም እና በኢጋድ የሰላምና ደህንነት ተጠሪና የዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ በይፋ ተመርቋል፡፡

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምክትል ጠ/ሚ አቶ #ደመቀ_መኮንን...

"ውድ ተማሪዎች . . . [ቢያንስ ቢያንስ] ለሃገር ክብር በጋራ እንደተዋደቁት፤ ለሃገር ልዕልና በጀግንነት እንደተዋጉት፤ ለሃገር አንድነት ዕድሜ ልካቸውን እንደደከሙት እንዲሁም ለእናት ሃገራቸው ሲሉ በቁርጠኝነት ለውጥ እንዳራመዱት. . .የቀደሙ አያቶቻችን እና አባቶቻችን እንድትሆኑ #እለምናችኋለሁ።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚ ዶ/ር #ዐቢይ_አሕመድና ም/ጠ/ሚር #ደመቀ_መኮንን በአማራ ክልል የሚገኘውን የኩሳኤ ቀበሌ ስንዴ ማሳ ክላስተር ጎበኙ። የሀገራችን የግብርና ኮመርሻላይዜሽን ክላስተር አሰራር አራት አላማዎች አሉት፡፡ እነርሱም የአነስተኛ አርሶ አደሩን ገቢ ማሣደግ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ገበያን ማመቻቸት፣ የአግሮ ኘሮሰሲንግና የእሴት ጭማሪ ስራን ማሣደግ እና የሥራ እድልን መፍጠር ናቸው፡፡

ምንጭ፦ የጠ/ሚ ጽ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የ5 ተማሪዎች ህይወት አልፏል‼️

በቅርቡ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በግለሰቦች ደረጃ ተፈጥሮ የነበረው አለመግባባት የቡድን መልክ በመያዝ ወደሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች #ተዛምቶ የአምስት ተማሪዎች ህይወት ማለፉን የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ገለጸ።

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመማር ማስተማር ወቅታዊ ሁኔታ ላይ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት እየመከሩ ናቸው።

በምክክር መድረኩ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ #ደመቀ_መኮንን፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስራ ኃላፊዎችን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ናቸው።

ምክክሩ ሲጀመር የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶክተር #ሂሩት_ወልደማሪያም እንደተናገሩት፤ በዩኒቨርሲቲዎች ተከስቶ በነበረው ግጭት ለሰው ህይወት መጥፋት ጭምር የዳረገ ጉዳት ደርሷል።

በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በግለሰቦች ደረጃ የተፈጠረ አለመግባባት ወደ #ቡድን መልክ በመቀየር በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተዛምቶ የነገ ተስፋ የሆኑ አምስት ተማሪዎችን ህይወት ቀጥፏል ብለዋል።

ችግሩን ለማርገብና ዘላቂ ሰላም  ለማስፈን ታልሞ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ግጭት ወደተከሰተባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ተንቀሳቅሰው ባከናወኑት ተግባር አንጻራዊ ሰላም እንደመጣ ዶክተር ሂሩት ተናግረዋል።

አሁን ባለድርሻ አካላት በሚያደርጉት ምክክር ዘላቂ የሆነ ሰላም ሊያረጋግጥ የሚችል ሃሳብ እንደሚፈልቅ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመማር ማስተማር ሂደትን ሰላማዊ ለማድረግ ሁሉም ባለድርሻ አካል ሀላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ተባለ። በዛሬው ዕለት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ የመማር ማስተመሩን ሂደት በሚያውኩ ችግሮች እና የመፍትሄ ሃሳቦችን በሚጠቁም ጥናት ላይ ውይይት እየተካሄደ ነው። በውይይቱም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ #ደመቀ_መኮንን ጨምሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የስራ ኃላፊዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጎንደር🔝

በጎንደር የሰላምና እርቅ ጉባኤ እየተካሄደ ነው። በአማራ እና ቅማንት ማህበረሰብ የተፈጠረውን ቁርሾ መፍትሄ ለመስጠት ያለመ ህዝባዊ #የሰላምና #የእርቅ ጉባኤ በጎንደር እየተካሄደ ነው፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር #ደመቀ_መኮንን እና የሐይማኖት አባቶች በተገኙበት መድረክ የሰላምና ጉባኤው በዛሬው ዕለት ሲካሄድ ይውላል፡፡

ዓላማውም በጎንደር በተለይም ማዕከላዊና ሰሜን ጎንደር ዞኖች ማንነትን መሰረት አድርገው የሚነሱ ግጭቶችን ሰላማዊ በሆነ መንገድ #በዘላቂነት ለመፍታት ያለመ ነው፡፡

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia