TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከአርባ ምንጭ⬆️

ጋሞ ባይራኮ!
ጋሞይ ጊታኮ!

ዛሬ በተካሄደው የጋሞ ህዝብና የኦሮሞ ህዝብ ምክክርና ይፋ የምስጋና ፕሮግራም ላይ በርካታ የጋሞ #ናቶዎችና በርካታ የኦሮሞ #ቄሮዎች ተገኝተዋል።

ከዛ ባሻገርም የጋሞ ወጋ አባቶች የኦሮሞ አባገዳዎች እርስ በእርስ ለእርቅ ድርድር ምቹ መንገድ ፈጥረዋል።

በዛሬው ቀን ከተነሱ ሃሳቦች ውስጥ በቡራዩ በተነሳው እልቂት ቄሮ እጁ እንደሌለበት እናውቃለን ነገር ግን ቄሮ ይህንን የወንብዴ ግሩፕ ለማስቆም እንዴት ተሳነው? የሚሉ ጥያቄዎች ተነስተዋል።

በተጨማሪም በቀጣይ ቄሮና የኦሮሚያ መንግስት ለዚህ ጨዋ እና ይቅር ባይ ህዝብ ምን ዋስትና ይሰጣል? የሚል ጥያቄም ተነስቶ ነበር። ቡራዩ የሚገኙት የጋሞ ተወላጆች ከዚህ ቡኋላ አስተማማኝ ጥበቃ እንዲደረግላቸውም ተጠይቋል።

ከአመስጋኞቹ በኩልም ቄሮን በመወከል ይቅርታ የጠየቁ ሲሆን ከዚህ ቡኋላም የጋሞን ህዝብ ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ በኦሮሚያ የሚገኙ የሌሎች ብሄረሰብ ህዝቦችን የመጠበቅ ግዴታ የኛ የቄሮና የክልሉ መሆኑን አስረድተዋል። ናቶንና የጋሞ ሽማግሌዎችንም አመስግነዋል።

በመጨረሻም ከሁለቱም ወገን የሰላም ፎረም የተቋቋመ ሲሆን ከኦሮሞና ከጋሞ ወጣቶች አራት አራት ወጣች በሰላም ፎረሙ ላይ እንዲካተቱ ተደርጓል።

©ፋሪስ ንጉሴ ከአርባምንጭ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update #ሀያት_ግሩፕ በአዲስ አበባ በኣአፍሪቃ የመጀመሪያ የሆነውን ሆቴል በያዝነው የፈረንጆች አመት መጨረሻ ሊከፍት ነው። ዘመናዊና ግዙፍ የሆነው ሀያት ሆቴል በመላው አለም የሚንቀሳቀስና ዝና ካላቸው ድርጅቶች አንዱ ነው። ሆቴሉ ወደ አዲስ አባባ የሚደረግ ጉዞ በከፍተኛ ደረጃ በመጨመሩ ይህን ገበያ ለመጠቀም ያለመ መሆኑን ብሎምበርግ ዘግቧል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ETV Zena Live! 10ኛው የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባዔ የመክፈቻ ስነ ስርዓት በቀጥታ በመተላለፍ ላይ ይገኛል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ⬇️

የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር #ወርቅነህ_ገበየሁ በ73ኛ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ ለአካባቢው ሰላም እና ዘላቂ ልማት ተግታ የምትሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ኢትዮጵያ እንደ ተመድ መስራች አባል ሀገር ለባለብዙ ወገን መድረክ ትኩረት በመስጠት የተ.መ.ድ መርህ እንዲከበር እንዲሁም ተግዳሮቶች እና ስጋቶች እንዲወገዱ በጋራ ትሰራለች ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ የተካሄደው ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ለሀገሪቱ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ ክስተት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ እንዲሁም ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ተሰፋው እንዲፈነጥቅ ያደረገ መሆኑንም ዶ/ር ወርቅነህ አውስተዋል፡፡

የህግ የበላይነት እንዲከበር፣ ፍትህ እንዲሰፍን፣ የአገር ኢኮኖሚ በአግባቡ ለማስተዳደር እንዲቻል፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት እንዲኖር፣ የብዙሃኑ ተሳትፎ እንዲረጋገጥ እንዲሁም ዴሞክራሲ እንዲያብብ ለማድረግ መንግስት በስፋት እና በጥልቀት እየሰራ መሆኑን ሚኒስትሩ
ተናግረዋል፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሚመራው መንግስት በሁሉም አቅጣጫ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት እና እንደ ሙስና፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ መልካም አስተዳደር ያሉትን የእድግት ማነቆዎች ለመቅረፍ በርካታ ተግባራት እየከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በቀጠናው የሰላም አየር እንዲነፍስ ያበረከተቸውን አስተዋጽኦም አብራርተዋል።

ለ20 አመታት ያክል በግጭት ላይ የነበሩት ኢትዮጵያና ኤርትራ አዲስ የግንኙነት ምዕራፍ መክፈታቸው፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ እንዲሁም #ጅቡቲ እና #ኤርትራ ችግሮቻቸውን በውይይት እንዲፈቱ የተደረገው ጥረት ከቀጠናው አልፎ ለአፍሪካ ሰላም ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ
መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰሚ ያጣው ዶሴ.doc
2.2 MB
ለሚመለከተው አካል በሙሉ‼️

ሰሚ ያጣው ዶሴ የምስራቅ ጎጃም ዞን ዉሃ መስኖና ኢነርጂ ልማት መምሪያ!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ለአራት ቀናት የሚቆየው የደኢህዴን 10ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት #በሀዋሳ ከተማ ጀምሯል፡፡ጉባዔው ከሌሎች ጊዜ በተለየ ሁኔታ በክብር የሚሰናበቱ አመራሮች እንደሚኖሩ ተገልጿል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የህገ ደንብ፣ #አርማና #ስያሜ ለውጥን የሚመለከቱ ውይይቶች ይካሄዳሉ ተብሏል፡፡ በ10ኛው የደኢህዴን ጉባዔ አዳዲስ አመራሮች ወደ ድርጅቱ የመሪነት እርከን ይቀላቀላሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የሰኔ 16ቱ የቦንብ ጥቃት⬇️

ጠቅላይ አቃቢ ህግ በሰኔ 16ቱ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ በተደረገው የድጋፍ ሰልፍ ላይ #ቦምብ አፈንድተዋል ያላቸው አምስት ግለሰቦች ላይ #ክስ መሰረተ፡፡

አምስቱ ግለሰቦች ጌቱ ግርማ፣ ብርሃኑ ጃፈር፣ ጥላሁን ጌታቸው፣ ባህሩ ቶላ እና ደሳለኝ ተስፋዬ ናቸው አቃቤ ህግ ቦምብ በማፈንዳት ወንጀል ክስ የመሰረተባቸው፡፡

ክሱ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ወንጀል ችሎት የተከፈተ ሲሆን ክሱን ለእያንዳንዳቸው በችሎት እንዲደርስ ይደረጋል ተብሏል፡፡

የጠቅላይ አቃቤ ህግ እንደሚያመላክተው አንደኛ ተከሳሽ ጌቱ ግርማ ከሁለተኛ ተከሳሽ ጋር ሱሉልታ ላይ በመገናኘት ሰልፉን የጠራው ገለልተኛ ወገን ሳይሆን ኢህአዴግ ነው ኤችአር 128 የተባለውን በአሜሪካ ኮንግረስ የተላለፈውን ውሳኔ ተግባራዊ እንዳይሆን ያደርጋል የሚል ምክንያቶችን በመግለጽ ቦምቡን #በመወርወር እንዲበተን እናድርግ በማለት እንዲዘጋጅ መግለጹን በክሱ ተመላክቷል፡፡

ለሦስተኛ ተከሳሽ #ደውሎም ቦምብ የሚወረውር ሰው አንዲፈልግ ተልዕኮ መስጠቱ በክሱ ተጠቅሷል፡፡

ሁለተኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ጃፈር ደግሞ በሚያዝያ ወር 2010 ዓመተምህርት ሁለት ኤፍ 1 እና አንድ የጭስ ቦምብ ያለው መሆኑን ለአንደኛ ተከሳሽ መግለጹን የጠቀሰው አቃቤ ህግ ሱሉልታ ከተማ ተገናኝተው ቦምቡን የድጋፍ ሰልፉ ላይ በመወርወር ጥቃት ለማድረስ በመነጋገር ቦምቡን መወርወር የሚችሉ ልጆች እንዲዘጋጁ ከአንደኛ ተከሳሽ ጋር ተነጋግረዋል ሲል አቃቤ ህግ በክሱ ጠቅሷል፡፡

ሦስተኛ ተከሳሽ ጥላሁን ጌታቸው በድጋፍ ሰልፉ ላይ ቦምብ እንዲያፈነዳ በአንደኛ ተከሳሽ ተገልጾለት ለአራተኛ ተከሳሻ በመደወል ቦምብ ለመወርወር ማቀዱን በመግለጽ በጉዳዩ ላይ #ለመወያየት እንዲገናኙ ማድረጉ ተገልጿል፡፡

አራተኛ ተከሳሽ ባህሩ ቶላ በአንደኛ ተከሳሽ አማካኝነት መስቀል አደባባይ ቦምቡን ለመወርወር ማቀዱን በመጥቀስ በሁኔታው ለመወያየት #አስኮ የተቀጣጠሩ ሲሆን ከዚያም ቡራዩ ላይ በአምስተኛ ተከሳሽ ቤት ተገናኝተዋል፡፡

ከተገናኙ በኋላም በአምስተኛ ተከሳሽ ቤት ያደሩ ሲሆን አንደኛ እና ሁለተኛ ተከሳሾች በሰኔ 16 2010 ዓመተምህረት ከንጋቱ 11፡00 ሰዓት ላይ ሁለተኛ ተከሳሽ በሚያሽከረክረው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ2 262335 አዲስ አበባ በሆነ መኪና ውስጥ ሁለት ኤፍ 1 ቦምብ እና አንድ የጭስ ቦምብ በመያዝ አንደኛ ተከሳሽ ቤት ማስቀመጣቸውን በክሱ ተጠቅሷል፡፡

ያስቀመጡትን ቦምብም በዚሁ ተሸከርካሪ ጭነው አዲስ አበባ ውንጌት አካባቢ ከሦስተኛ፣ ከአራተኛ እና ከአምስተኛ ተከሳሽ ጋር በመገናኘት ፒያሳ አካባቢ የገቡ ሲሆን በምን መልኩ ጥቃቱን ማድረስ እንዳለባቸው መወያየታቸውም ተገልጿል፡፡

እንዲሁም በዕለቱ የዶክተር አብይ አህመድ ምስል ያለበትን ቲሸርት ገዝተው እንዲለብ ሱ በማድረግ በተጠቀሰው መኪና ቴዎድሮስ አደባባይ ድረስ በመሸኘት ቦምቡ እንዲፈነ ዳ ተልዕኮ በመስጠት የተመለሱ ሲሆን ሦስተኛ፣ አራተኛ እና አምስተኛ ተከሳሾች በተሰጣቸው ተልዕኮ መሰረት ከሰልፈኞች ጋር በመቀላቀል ሦስተኛ ተከሳሽ በሐራምቤ አቅጣጫ በማድረግ ወደ መስቀል አደባባይ መግባቱ የተጠቀሰ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር አድርገው ሲጨርሱ ከመድረኩ በቅርብ ርቀት ላይ በመገኘት ቦምቡን ወርውሮ ማፈንዳቱን አቃቢ ህግ ጠቅሷል፡፡

በዚህም ሙሳ ጋዲሳና ዮሴፍ አያሌው የተባሉ ግለሰቦች በፍንዳታው ህይወታቸው ማለፉን በክሱ ተጠቅሷል፡፡

በፍንዳታው ከ163 በላይ በሆኑ ንጹሃን ግለሰቦች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት አድርሰውባቸዋል ተብሏል፡፡

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ሀዋሳ⬇️

በሀዋሳ ከተማ የተለያዩ #የጦር_መሳሪያዎች እና #ስለታም ነገሮችን ይዘው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ አምስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ፡፡

በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የአድማ ብተና እና ልዩ ኃይል ዘርፍ ኃላፊ በምክትል ኮሚሽነር ማዕረግ መሳፍንት ሙሉጌታ እንደገለጹት በሀዋሳ ከተማ መስከረም 17 ቀን 2011 ዓ.ም በተለያዩ ቦታዎች በተደረገው #ፍተሻ 3 ስታር #ሽጉጥ የተለየዩ ስለታማ መሳሪያዎችና 834 ሺህ ብር መያዙን ገልፀዋል፡፡

እንደ ኃላፊው ገለጻ የፀጥታ አካሉ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥና የከተማውን ሠላም ለማስጠበቅ በቋሚና ተንቀሳቃሽ ጥበቃ እያደረገ እንደሚገኝና በዚህም አምስት ግለሰቦት የጦር መሳሪያዎችንና ስለታማ ጩቤዎችን ይዘው ሲንቀሳቀሱ በድንገት በተደረገው ፍተሻ በጎድጓዳ፣ ጥቁር ውሃ እና ታቦር ክፍለ ከተማ እንደተያዙ አስረድተው ግለሰቦቹ ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል ሲል የኮሚሽኑ ሕዝብ ግንኙነት ዳይሮክተሬት ዋና ሳጅን ደጀኔ አሰፋ አስረድተዋል።

©የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ⬆️የነባር እና አዲስ ተማሪዎች መግቢያ ቀናትን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል። 18/01/2011

©ትግዕስት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ስለ ሰኔ 16ቱ ጥቃት ሪፖርተር እና EBC⬇️

በሰኔ 16ቱ የቦንብ ጥቃት በተጠረጠሩ 5 ግለሰቦች ላይ #የሽብር ወንጀል ክስ ተመሰረተ።

የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ በሰኔ 16ቱ የቦንብ ጥቃት ተሳትፈዋል በሚል የተጠረጠሩ አምስት ግለሰቦች ላይ በሽብር ወንጀል #ክስ መሰረተባቸው።

ጠቅላይ ዓቃቢ ህግ በሽብር ወንጀል ክስ የመሰረተባቸው ጌቱ ግርማ ፣ብርሃኑ ጁፋር ፣ጥላሁን ጌታቸው ፣ባህሩ ቶላና ደሳለኝ ተስፋዬ ላይ ነው፡፡

ዓቃቢ ህግ ሁሉንም ተከሳሾች ሰኔ 16 በነበረው የድጋፍ ሰልፍ ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር #ዐቢይ_አሕመድ ላይ ጥቃት ለማድረስ ብሎም በሀገሪቱ እየታየ ያለውን ለውጥ ለማደናቀፍ በጠቅላይ ሚንስትሩ የሚመራ መንግስት መኖር የለበትም የሚል ዓለማ ይዘው እንደነበር በክሱ ተጠቅሷል።

እንደ ክሱ ገለፃ ከሆነ ይህ ዓለማ ቀድሞ በተደራጀ በኦነግ ስም በሚንቀሳቀሱና የቦንብ ጥቃት ማድረስ በሚችሉ አባላት አማካኝነት መሆን እንዳለበትም የሚያስችል ስምምነት ላይ መደረሱን ተከትሎ ነው።

ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ተቀባይነት የሌላቸው በተለይም በኦሮሞ ብሔር ዘንድ አንደማይፈለጉ አድርጎ ለማሳየት በሚረዳ መልኩ ጥቃቱን ለመፈፀም ዐቅደው መንቀሳቀሳቸውም በክሱ ተጠቁሟል።

ለዚህ ደግሞ በኬንያ የምትኖር ገነት ታምሩ ወይንም በቅፅል ስም #ቶሎሺ ታምሩ በምትባል የቡድኑ አባል አማካኝነት ተልዕኮ እንደተሰጣቸው በክሱ ተገልጿል።

አንደኛ ተከሳሽ ጌቱ ግርማ ከዚች ሴት ጋር ሰኔ 2010 በስልክ በመገናኘት ' ለጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የድጋፍ ሰልፍ መካሄድ የለበትም'፣' መሰረታዊ ለውጥ አልመጣም '፣ ' ሰልፉን የጠራው ገለልተኛ ወገን ሳይሆን ኢህአዲግ ነው '፣ ' HR128 የተባለውና በአሜሪካ ኮንግረንስ የተላለፈው ውሳኔ ተግባራዊ እንዳይሆን ያደርጋል' በሚል ሰልፉ እንዲበተን አድርጉ የሚል ተልኮ እንደተቀበለም ክሱ አመልክቷል።

አንደኛ ተከሳሽ ጌቱ ግርማ ከሁለተኛ ተከሳሽ ብረሃኑ ጁፋር ጋር በሰኔ ሱሉልታ ላይ ስለ ተልኮው በመነጋገር ቦንብ እዲያዘጋጅ፣ ቦንቡን የሚወረውርን እንዲያፈላልግ ተነጋግረው ለሶስተኛ ተከሳሽ ጥላሁን ጌታቸው ደውሎ ቦንብ የሚወረውር ሰው እንዲፈልግ ተልኮ
መስጠቱም ክሱ ያሳያል።

ሁለተኛ ተከሳሽ ያዘጋጀውን ሁለት ኤፍ 1 ቦንብ እንዲሁም አንድ የጭስ ቦንብ በአንደኛ ተከሳሽ ቤት በማስቀመጥ ከሱሉልታ በመነሳት ሰልፉን በመቀላቀል በኛው ተከሳሽ አመካኝነት ቦንቡን በማፈንዳት ሙሳ ጋዲሰና ዬሴፍ አያለው የተበሉ ግለሰቦች ላይ የሞት 165 የሚሆኑ ሰዎች ላይ ከባድ ና ቀላል ጉዳት ማድረሳቸውም በክሱ ተጠቁሟል። በዘህም መሰረት ዓቃቢ ህግ ክስ መስርቶባቸዋል

ምንጭ፦ EBC

ሪፖርተር፦

ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. በመስቀል አደባባይ በተፈጸመው የቦምብ ጥቃት የተጠረጠሩ አምስት ግለሰቦች #የሽብርተኝነት ክስ ተመሠረተባቸው፡፡

በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ወንጀል ችሎት ዓርብ መስከረም 18 ቀን 2011 ዓ.ም. ክሱን ያቀረበው ዓቃቤ ሕግ፣ የቦምብ ጥቃቱ የተፈጸመው ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) #ለመግደል መሆኑን በክሱ አስታውቋል፡፡

በቦምብ ጥቃቱ ክስ የተመሠረተባቸው ተጠርጣሪዎች አቶ ጌቱ ግርማ፣ አቶ ብርሃኑ ጃፋር፣ አቶ ጥላሁን ጌታቸው፣ አቶ ባህሩ ቶሎሳና አቶ ደሳለኝ ተስፋዬ ናቸው፡፡

ዓቃቤ ሕግ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ክስ እንደገለጸው፣ ተከሳሾቹ በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ ላይ ግድያ ለመፈጸም ያነሳሳቸው በእሳቸው የሚመራ መንግሥት #መኖር ስለሌለበት ነው፡፡ የአገሪቱ መንግሥት መመራት ያለበት ቀድሞ በተመሠረተው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ነው የሚል ዓላማ ተከሳሾቹ እንዳላቸው ዓቃቤ ሕግ በመሠረተው #ክስ ጠቁሟል፡፡

በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት የላቸውም በማለትም፣ ተጠርጣሪዎቹ ለግድያ መነሳሳታቸውን ዓቃቤ ሕግ አስታውቋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአሜሪካ ኮንግረስ የፀደቀውን ኤችአር 128 ለማስፈጸምና በስመ ሕዝበኝነት የራሳቸውን ዓላማ የሚያራምዱ መሆናቸውን፣ በዚህም ምክንያት የኦሮሞን ሕዝብ ፍላጎት ስለማያስፈጽሙ ተጠርጣሪዎቹ ጥቃቱን ለመፈጸም መነሳሳታቸቸውን ዓቃቤ ሕግ
በክሱ አክሏል፡፡

የሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. የመስቀል አደባባይ የወንጀል ድርጊት ያቀነባበረችው በኬንያ ናይሮቢ የምትገኝ ገነት ታምሩ (ቶለሺ ታምሩ) የምትባል መሆኗን፣ ዓቃቤ ሕግ በክሱ አመልክቷል፡፡

በመስቀል አደባባይ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ድጋፍና ምሥጋና በተደረገ ሥነ ሥርዓት ላይ በተፈጸመ የቦምብ ጥቃት ሁለት ግለሰቦች ሲሞቱ፣ ከ150 በላይ ጉዳት እንደደረሰባቸው ይታወሳል፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ📌ፈተና ሳትፈተኑ ስለወጣችሁ የBiT ተማሪዎች ጉዳይ ተጨማሪ መረጃ አሰባስቤ አሳውቃችኋለሁ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኢሬቻ 2011/2018⬇️

የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ #ለኢሬቻ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልክእት አስተላለፉ።

ርእሰ መስተዳድር አቶ #ለማ_መገርሳ በመልክታቸው፥ በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ትልቅ ስፍራ ለሚሰጠው የኢሬቻ በዓል እንኳን አደረሳችሁ ብለዋል።

ዘንድሮ የሚከበረው የኢሬቻ በዓል በተቀናጀ እና አስገራሚ በሆነ መልኩ እንዲከበር ሁሉም የህብረተሰብ አካላት የበኩሉን እንዲወጣም ጥሪ አስተላልፈዋል።

አባ ገዳዎች፣ ወጣቶች እና ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በሙሉ ባህልን በሚያፅባርቅ መልኩ የኢሬቻን በዓል አንዲያከብሩም ጠይቀዋል።

የ2010 ዓ.ም የኢሬቻ በዓል በተቀናጀ እና ሰላማዊ በሆነ መንገድ የተከበረ መሆኑን ያስታወሱት አቶ ለማ፥ የዘንድሮውም ከአምናው በተሻለ መልኩ ሰላማዊ እና ባህላችንን ለዓለም በምናስተዋውቅበት መልኩ ሊከበር ይገባል ብለዋል።

የኢሬቻ በዓል የገዳ ስርዓት ነፀብራቅ በመሆኑ ልክ እንደ ገዳ ስርዓት ሁሉ የኢሬቻ በዓልንም በዩኔስኮ በዓለም ቅርሰነት ለማስመዝገብ እየተሰራ መሆኑን አቶ ለማ አንስተዋል።

ስለዚህ በዓሉን ለማክበር ወደ ስፍራው የሚሄዱ በሙሉ ከፖለቲካ ፓርቲ አርማ፣ ባንዲራ እና ዘፈኖች ራሳቸውን እንዲቆጥቡም ጠይቀዋል።

የዘንድሮ የኢሬቻ በዓል ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲጠናቀቅ መንግስት ከአባ ገዳዎች ህብረት እና ከወጣቶች ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑንም ርእሰ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ አንስተዋል።

ከጤና ጋር ተያይዞ ችግር ካጋጠመም የጤና ባለሙያዎች ከወዲሁ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን መግለፃቸውን ከኦሮሚያ ክለል የመንግሰት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የዩኒቨርሲቲ ምደባን በተመለከተ⬇️

የዩኒቨርሲቲ ትምህርት በጥቅምት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ይጀመራል የትምህርት ሚኒስቴር የ2011 ትምህርት ዘመን #በጥቅምት የመጀመሪያ ሳምንት እንደሚጀመር አስታወቀ።

በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተናገሩት፤ የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታ ማዘጋጃ ጥናት ላይ ሰፊ ውይይት ለማካሄድ፣ በመስከረም ወር ያሉትን ብሄራዊና የሀይማኖታዊ በአላትን እንዲሁም #የትራንስፖርት አገልግሎትን ከግምት በማስገባት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትምህርት መስጠት የሚጀመረው ከጥቅምት
ወር የመጀመሪያው ሳምንት ጀምሮ ይሆናል።

የአዲስ ተማሪዎች ምደባም #በቀናት ውስጥ ይፋ የሚደረግ ይሆናል ያሉት ዶ/ር ሳሙኤል፤ ይህን ተከትሎ ዩኒቨርስቲዎች በሚያወጡት ፕሮግራም መሰረት ነባርና አዲስ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲገቡ የሚደረግ ይሆናል።

ዩኒቨርስቲዎችም ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተናገድ አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቀዋል።

የ10ኛ ክፍል ወይም የመሰናዶ መግቢያ ሀገር አቀፍ ፈተና ያልቀረ መሆኑንና በነበረበት የሚቀጥል መሆኑንም አስታውቀዋል።

© አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2011 (የኢትዮጵያ ፕሬሥ ድርጅት)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አብዲ ኢሌ⬇️

በሶማሌ ክልል ጅግጅጋና ሌሎች ዞኖች በጅምላ ጭፍጨፋ፣ የብሄርና ሀይማኖት ግጭት ቅስቀሳ ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት የቀድሞ ሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር #አብዲ_መሀመድን ጨምሮ 4 ግለሰቦች ላይ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ወንጀል ችሎት ለተጨማሪ ምርመራ የ10 ቀን #ፈቀደ፡፡

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የምርመራ ቡድን አብዲ መሀመድ፣ ወ/ሮ ረሂማ መሀመድ፣ አብዱረዛቅ ሳኒ እና ኮሚሽነር ፈረሃን ባሂር ላይ ፍርዱ ቤቱ በፈቀደው 14 ቀን የምርመራ ጊዜ በርካታ ተግባራትን ማከናወኑን አስታውቋል፡፡

በዚሁ ወቅት የ41 ምስክሮች ቃል መቀበሉንና የተዘረፈውን ንብረት ግምት እንዱሁም #በሄጎ እና በልዩ ሀይሉ የተጨፈጨፉ ሰዎች አስክሬን
ምርመራ ውጤት መሰብሰቡም ፖሊስ ገልጿል፡፡

የፍርድ ቤት ማዘዣ የወጣባቸውን ግብራበሮች መያዝ፣ በአንድ ጉድጓድ ውስጥ የተቀበሩ ሰዎች ማንነትን መለየት፣ የአስገድዶ መድፈር የተፈጸመባቸውን ሴቶች መለየት፣ የሕክምና መስረጃ ማሰባሰብ፣ የተደበቀ የጦር መሳሪያና ገንዘብ ማሰባሰብ፣ የምስክር ቃል ለመቀበል 14 ቀን እንዲፈቀድለት ጠይቋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በራሳቸውና አማካኝነት ፖሊስ የጠየቀውን የ14 ቀን ምርመራ ጊዜ ተገቢነት የለውም፣ የፖሊስ አቀራረብ በዝርዝር አይደለም፣ ተገቢውን ህክምና እያገኘን አይደለም፣ በአያያዝም በኩል ችግር በመኖሩ ፍ/ቤቱ የምርመራ መዝገቡ ሊለያይ ይገባል የሚሉ ሁኔታዎችን አንስተዋል᎓᎓

መርማሪ ፖሊሰ ምርመራው በዝርዝር ነው የቀረበው ተጠርጣሪዎች በክልሉ በነበረው የብሔርና የሃይማኖት ግጭት ጅምላ ጭፍጨፋ የዜጎች መፈናቀልና የንብረት ውድመት በቅንጅት ነው የሰሩት ብሏል᎓᎓ምርመራው ተነጣጥሎ ሊታይ አይገባውም᎓᎓

ለምሳሌ የሴቶችና የህፃናት ጉዳዮች ሃላፊ ወይዘሮ #ራሂማ_መሃመድና የዲያስፖራ ቢሮ ሃላፊው #አብዱልራዛቅ_ሳኒ ግጭቱን በፌስ ቡክ ሲቀሰቅሱ ነበር ብሏል መርማሪ ቡድኑ᎓᎓

የፖሊስ ኮሚሽነር የነበረው ፈሪሃን ጣሂር ሂጎዎችን በራሱ ጊዜ መሳሪያ አስታጥቆ ሰው ያስጨረሰ ልዩ ሃይሎችንም ለጥፋት ሲያነሳሳ ግጭቱን በመኪና እየዞረ ያጠናከረ ብሎም በርካታ ታራሚዎችን ከማረሚያ አስወጥቶ ያስረሸነ ነው ብሏል ቡድኑ᎓᎓ ምርመራው ሰፊ በመሆኑ ዋስትናውን ተቃውሟል᎓᎓

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia