የዩኒቨርሲቲ ምደባን በተመለከተ⬇️

የዩኒቨርሲቲ ትምህርት በጥቅምት ወር የመጀመሪያ ሳምንት ይጀመራል የትምህርት ሚኒስቴር የ2011 ትምህርት ዘመን #በጥቅምት የመጀመሪያ ሳምንት እንደሚጀመር አስታወቀ።

በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተናገሩት፤ የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታ ማዘጋጃ ጥናት ላይ ሰፊ ውይይት ለማካሄድ፣ በመስከረም ወር ያሉትን ብሄራዊና የሀይማኖታዊ በአላትን እንዲሁም #የትራንስፖርት አገልግሎትን ከግምት በማስገባት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትምህርት መስጠት የሚጀመረው ከጥቅምት
ወር የመጀመሪያው ሳምንት ጀምሮ ይሆናል።

የአዲስ ተማሪዎች ምደባም #በቀናት ውስጥ ይፋ የሚደረግ ይሆናል ያሉት ዶ/ር ሳሙኤል፤ ይህን ተከትሎ ዩኒቨርስቲዎች በሚያወጡት ፕሮግራም መሰረት ነባርና አዲስ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲገቡ የሚደረግ ይሆናል።

ዩኒቨርስቲዎችም ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማስተናገድ አስፈላጊውን ዝግጅት አጠናቀዋል።

የ10ኛ ክፍል ወይም የመሰናዶ መግቢያ ሀገር አቀፍ ፈተና ያልቀረ መሆኑንና በነበረበት የሚቀጥል መሆኑንም አስታውቀዋል።

© አዲስ አበባ፣ መስከረም 18፣ 2011 (የኢትዮጵያ ፕሬሥ ድርጅት)
@tsegabwolde @tikvahethiopia