TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የሰኔ 16ቱ የቦንብ ጥቃት⬇️

በሰኔ 16 ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክትር #አብይ_አህመድ የድጋፍ ሰልፍ ላይ #ቦምብ በመወርውር በማቀበል የተጠረጠሩ ጥላሁን ጌታቸውና ብርሃኑ ጃፋር ላይ ፍርድ ቤቱ የመጨረሻ የክስ መመስረቻ ጊዜ ሰጠ፡፡

ቀደም ሲል አቃቢ ህግ በሁለቱ ተጠርጣሪዎች ላይ በቦምብ ጉዳት የደረሰባቸው ተጨማሪ ቃል ለመቀበልና የስልክ ልውውጥ ማስረጃን እንዲሟላ ለመርማሪ ፖሊስ መዝገቡን መመለሱንና ማስረጃዎችንም ለሟሟላት ጊዜ መስጠቱ የሚታወስ ነው፡፡

በዚህ መሰረት በዛሬው ዕለት መርማሪ ፖሊስ ለፌደራል የመጀመሪ ደረጃ አንደኛ ተረኛ ወንጀል ችሎት ተጨማሪ ማስረጃውን አሟልቶ አጠናቆ ለአቃቢ ህግ መመለሱን አስረድቷል፡፡

የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ በበኩሉ የምርመራ መዝገቡን መቀበሉን በመግለጽ ይህንን ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠኝ በማለት ፍርድ በቱን ጠይቋል፡፡

እስከዚያውም አቃቤ ህግ ተጠርጠሪዎቹ በእስር እንዲቆዩ በማለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡

ተጠርጣሪ ጥላሁን ጌታቸውም ጨለማ ቤት እንደሚገኝ እንዲሁም በቦምብ አደጋ የደረሰብኝ በመሆኑ ህክምና እያገኘሁ አይደለም ሲል በዋስ ልወጣ ይገባል በማለት ፍርድ ቤቱ ጥያቄውን አቅርቧል፡፡

መርማሪ ፖሊስም በባለሙያ እየተደገፈ አቤት ሆስፒታል ህክምና እንዲያገኝ እየተደረገ መሆኑን በመግለጽ ለዚህም የተያዘ ቃለጉባዔ መኖሩንም ገልጿል፡፡

ጨለማ ቤት የተባለውም ጉዳይ ሐሰት መሆኑንና በአሁኑ ወቅት ጨለማ ቤት የሚባል እስር ቤት እንደሌለ ፖሊስ ለችሎት አስረድቷል፡፡

ተጠርጣሪ ብርሃኑ ጃፋር በበኩሉ እኔ ከተያዝኩ ብዙ ቀናትን ያስቆጠርኩ በመሆኑ እንዲሁም በተደጋጋሚ የጊዜ ቀጠሮ የተጠየቀብኝ ሲሆን አሁን የጊዜ ቀጠሮ ሊሰጥ አይገባም በማለት የዋስትና ይፈቀድልኝ ሲል ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡

አቃቢ ህግም ተጠርጣሪዎቹ የፈጸሙት ወንጀል ከባድና ውስብስብ እንዲሁም በርካታ ዜጎች ላይ ጉዳት ማድረሱ ለሁለት ሰዎች ህልፈት ምክንያት በመሆኑ ዋስትና ሊፈቀድላቸው አይገባም በማለት ጥያቄያቸውን ተቃውሟል፡፡

የሁለቱን ክርክር ያደመጠው ፍርድ ቤትም የዋስትና ጥያቄያቸው በማለፍ ጥላሁን ጌታቸው ላይ እስከ መስከረም 10 ባለው ጊዜ ውስጥ #ክስ እንዲመሰርት ብርሃኑ ጃፋር ላይ ደግሞ እስከ መስከረም ዘጠኝ ቀን የክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቅዷል፡፡

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ድሬዳዋ ፖሊስ⬇️

የድሬዳዋ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ሐምሌ 29/2010 ዓም ለ13 ሰዎች ህልፈትና ለንብረት መውደም ምክንያት በሆነው ግጭት ላይ ምርመራውን አጠናቆ ለአቃቤ ህግ ለመላክ መዘጋጀቱን ይፋ አደረገ ኮሚሽኑ ዛሬ ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ በእለቱ በተፈጠረው ሁከት በሶስት መኖሪያ ቤቶች ውስጥ የነበሩ የ13 ንፁሀን ዜጎች #ህይወት ማለፋንና በ42 ቤቶች ላይ ቃጠሎና ዝርፊያ መካሔዱን ገልጿል።

ኮሚሽኑ ባደረገው ምርመራ 4 ግለሰቦች በቤት ቃጠሎ ፣21 ግለሰቦች ደግሞ በቀጥታ በግድያው መሳተፋቸውን በማስረጃ ማረጋገጡን ገልጾ በ5 #ተጠርጣሪዎች ላይ ማስረጃ እያሰባሰበ መሆኑን በመግለጫው አስረድቷል።

ከ13ቱ ሟቾች 8ቱ የአንድ አመት ህፃንን ጨምሮ ከ15 አመት በታች እድሜ ያላቸው ሲሆኑ በንብረት ረገድም ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ ተገልጿል።

በግጭቱ ወቀት የነፍስ ግድያ ፣ የቤት ቃጠሎና የዝርፊያ ተደራራቢ ወንጀል በመፈፀሙ ምርመራውን ለማጠናቀቅ ጊዜ መውሰዱን በመግለጫው ተመልክቷል።

የተፈጠረውን ግጭት የብሔር ግጭት ለማስመሰል ሙከራ መደረጉን፣ የድሬዳዋ ሕዝብ ያዳበረው የአብሮ መኖር እሴት ለእንዲህ አይነቱ ኋላ ቀር አስተሳሰብ የማይመች በመሆኑና ፖሊስ ሁኔታውን መቆጣጠር በመቻሉ የታሰበው ሊሳካ አለመቻሉን የድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽን ሕዝብ ግኑኝነት ዲቪዥን ሀላፊ ዋና ሳጅን ባንታለም ግርማ ገልፀዋል።

ከሀምሌ 29 በኋላ ነሀሴ 29/2010 ዓም በድጋሚ ግጭት ለማስነሳት መሞከሩን የገለጹት ዋና ሳጂን ባንታለም ግርማ ፖሊስ ጉዳት ከመድረሱ በፊት ሁኔታውን በመቆጣጠር 300 የሚሆኑ ተጠርጣሪዎችን የያዘ ሲሆን ከተያዙት ውስጥ በ77 ቱ ላይ ምርመራ አጣርቶ
ለአቃቤ ህግ በመላኩ አቃቤ ህግ በፍርድ ቤት #ክስ መመስረቱን ተናግረዋል።

ሰሞኑን በቤቶች ላይ የተደረገውን ምልክት በተመለከተም ፖሊስ ከህብረተሰቡ ጋር እጅና ጓንት ሳይሆን መዳፍና ጣት ሆኖ በመስራቱ ምልክቱ ወደ ተግባር እንዳይለወጥ መደረጉን የህዝብ ግኑኝነት ሀላፊው ገልፀዋል።

ከነገ ጀምሮ በክርስትና እምነት ተከታዮች የሚከበረው የደመራና የመስቀል በአል ሀይማኖታዊ እሴቱን ጠብቆ በሰላም እንዲከበር ፖሊስ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቁን የገለጹት ዋና ሳጂን ባንታለም ግርማ ሰላም ወዳዱ የድሬዳዋ ሕዝብም ከስሜታዊነት ርቆ እንደ ሁልጊዜው ከፖሊስ ጋር በመተበባር ለሰላሙ ዘብ እንዲቆም ጠይቀዋል።

ኮሚሽኑ ህብረተሰቡ በተለይም #ወጣቶች እንዲሁም የአስተዳደሩ አመራሮች ሁከትን ለማክሸፍና ሠላምን ለማረጋገጥ ላሳዩት ቁርጠኝነት #ምስጋናውን አቅርቧል ።

ምንጭ፦ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የሰኔ 16ቱ የቦንብ ጥቃት⬇️

ጠቅላይ አቃቢ ህግ በሰኔ 16ቱ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ በተደረገው የድጋፍ ሰልፍ ላይ #ቦምብ አፈንድተዋል ያላቸው አምስት ግለሰቦች ላይ #ክስ መሰረተ፡፡

አምስቱ ግለሰቦች ጌቱ ግርማ፣ ብርሃኑ ጃፈር፣ ጥላሁን ጌታቸው፣ ባህሩ ቶላ እና ደሳለኝ ተስፋዬ ናቸው አቃቤ ህግ ቦምብ በማፈንዳት ወንጀል ክስ የመሰረተባቸው፡፡

ክሱ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ወንጀል ችሎት የተከፈተ ሲሆን ክሱን ለእያንዳንዳቸው በችሎት እንዲደርስ ይደረጋል ተብሏል፡፡

የጠቅላይ አቃቤ ህግ እንደሚያመላክተው አንደኛ ተከሳሽ ጌቱ ግርማ ከሁለተኛ ተከሳሽ ጋር ሱሉልታ ላይ በመገናኘት ሰልፉን የጠራው ገለልተኛ ወገን ሳይሆን ኢህአዴግ ነው ኤችአር 128 የተባለውን በአሜሪካ ኮንግረስ የተላለፈውን ውሳኔ ተግባራዊ እንዳይሆን ያደርጋል የሚል ምክንያቶችን በመግለጽ ቦምቡን #በመወርወር እንዲበተን እናድርግ በማለት እንዲዘጋጅ መግለጹን በክሱ ተመላክቷል፡፡

ለሦስተኛ ተከሳሽ #ደውሎም ቦምብ የሚወረውር ሰው አንዲፈልግ ተልዕኮ መስጠቱ በክሱ ተጠቅሷል፡፡

ሁለተኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ጃፈር ደግሞ በሚያዝያ ወር 2010 ዓመተምህርት ሁለት ኤፍ 1 እና አንድ የጭስ ቦምብ ያለው መሆኑን ለአንደኛ ተከሳሽ መግለጹን የጠቀሰው አቃቤ ህግ ሱሉልታ ከተማ ተገናኝተው ቦምቡን የድጋፍ ሰልፉ ላይ በመወርወር ጥቃት ለማድረስ በመነጋገር ቦምቡን መወርወር የሚችሉ ልጆች እንዲዘጋጁ ከአንደኛ ተከሳሽ ጋር ተነጋግረዋል ሲል አቃቤ ህግ በክሱ ጠቅሷል፡፡

ሦስተኛ ተከሳሽ ጥላሁን ጌታቸው በድጋፍ ሰልፉ ላይ ቦምብ እንዲያፈነዳ በአንደኛ ተከሳሽ ተገልጾለት ለአራተኛ ተከሳሻ በመደወል ቦምብ ለመወርወር ማቀዱን በመግለጽ በጉዳዩ ላይ #ለመወያየት እንዲገናኙ ማድረጉ ተገልጿል፡፡

አራተኛ ተከሳሽ ባህሩ ቶላ በአንደኛ ተከሳሽ አማካኝነት መስቀል አደባባይ ቦምቡን ለመወርወር ማቀዱን በመጥቀስ በሁኔታው ለመወያየት #አስኮ የተቀጣጠሩ ሲሆን ከዚያም ቡራዩ ላይ በአምስተኛ ተከሳሽ ቤት ተገናኝተዋል፡፡

ከተገናኙ በኋላም በአምስተኛ ተከሳሽ ቤት ያደሩ ሲሆን አንደኛ እና ሁለተኛ ተከሳሾች በሰኔ 16 2010 ዓመተምህረት ከንጋቱ 11፡00 ሰዓት ላይ ሁለተኛ ተከሳሽ በሚያሽከረክረው የሰሌዳ ቁጥር ኮድ2 262335 አዲስ አበባ በሆነ መኪና ውስጥ ሁለት ኤፍ 1 ቦምብ እና አንድ የጭስ ቦምብ በመያዝ አንደኛ ተከሳሽ ቤት ማስቀመጣቸውን በክሱ ተጠቅሷል፡፡

ያስቀመጡትን ቦምብም በዚሁ ተሸከርካሪ ጭነው አዲስ አበባ ውንጌት አካባቢ ከሦስተኛ፣ ከአራተኛ እና ከአምስተኛ ተከሳሽ ጋር በመገናኘት ፒያሳ አካባቢ የገቡ ሲሆን በምን መልኩ ጥቃቱን ማድረስ እንዳለባቸው መወያየታቸውም ተገልጿል፡፡

እንዲሁም በዕለቱ የዶክተር አብይ አህመድ ምስል ያለበትን ቲሸርት ገዝተው እንዲለብ ሱ በማድረግ በተጠቀሰው መኪና ቴዎድሮስ አደባባይ ድረስ በመሸኘት ቦምቡ እንዲፈነ ዳ ተልዕኮ በመስጠት የተመለሱ ሲሆን ሦስተኛ፣ አራተኛ እና አምስተኛ ተከሳሾች በተሰጣቸው ተልዕኮ መሰረት ከሰልፈኞች ጋር በመቀላቀል ሦስተኛ ተከሳሽ በሐራምቤ አቅጣጫ በማድረግ ወደ መስቀል አደባባይ መግባቱ የተጠቀሰ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር አድርገው ሲጨርሱ ከመድረኩ በቅርብ ርቀት ላይ በመገኘት ቦምቡን ወርውሮ ማፈንዳቱን አቃቢ ህግ ጠቅሷል፡፡

በዚህም ሙሳ ጋዲሳና ዮሴፍ አያሌው የተባሉ ግለሰቦች በፍንዳታው ህይወታቸው ማለፉን በክሱ ተጠቅሷል፡፡

በፍንዳታው ከ163 በላይ በሆኑ ንጹሃን ግለሰቦች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት አድርሰውባቸዋል ተብሏል፡፡

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ስለ ሰኔ 16ቱ ጥቃት ሪፖርተር እና EBC⬇️

በሰኔ 16ቱ የቦንብ ጥቃት በተጠረጠሩ 5 ግለሰቦች ላይ #የሽብር ወንጀል ክስ ተመሰረተ።

የፌደራል ጠቅላይ አቃቢ ህግ በሰኔ 16ቱ የቦንብ ጥቃት ተሳትፈዋል በሚል የተጠረጠሩ አምስት ግለሰቦች ላይ በሽብር ወንጀል #ክስ መሰረተባቸው።

ጠቅላይ ዓቃቢ ህግ በሽብር ወንጀል ክስ የመሰረተባቸው ጌቱ ግርማ ፣ብርሃኑ ጁፋር ፣ጥላሁን ጌታቸው ፣ባህሩ ቶላና ደሳለኝ ተስፋዬ ላይ ነው፡፡

ዓቃቢ ህግ ሁሉንም ተከሳሾች ሰኔ 16 በነበረው የድጋፍ ሰልፍ ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር #ዐቢይ_አሕመድ ላይ ጥቃት ለማድረስ ብሎም በሀገሪቱ እየታየ ያለውን ለውጥ ለማደናቀፍ በጠቅላይ ሚንስትሩ የሚመራ መንግስት መኖር የለበትም የሚል ዓለማ ይዘው እንደነበር በክሱ ተጠቅሷል።

እንደ ክሱ ገለፃ ከሆነ ይህ ዓለማ ቀድሞ በተደራጀ በኦነግ ስም በሚንቀሳቀሱና የቦንብ ጥቃት ማድረስ በሚችሉ አባላት አማካኝነት መሆን እንዳለበትም የሚያስችል ስምምነት ላይ መደረሱን ተከትሎ ነው።

ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ተቀባይነት የሌላቸው በተለይም በኦሮሞ ብሔር ዘንድ አንደማይፈለጉ አድርጎ ለማሳየት በሚረዳ መልኩ ጥቃቱን ለመፈፀም ዐቅደው መንቀሳቀሳቸውም በክሱ ተጠቁሟል።

ለዚህ ደግሞ በኬንያ የምትኖር ገነት ታምሩ ወይንም በቅፅል ስም #ቶሎሺ ታምሩ በምትባል የቡድኑ አባል አማካኝነት ተልዕኮ እንደተሰጣቸው በክሱ ተገልጿል።

አንደኛ ተከሳሽ ጌቱ ግርማ ከዚች ሴት ጋር ሰኔ 2010 በስልክ በመገናኘት ' ለጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ የድጋፍ ሰልፍ መካሄድ የለበትም'፣' መሰረታዊ ለውጥ አልመጣም '፣ ' ሰልፉን የጠራው ገለልተኛ ወገን ሳይሆን ኢህአዲግ ነው '፣ ' HR128 የተባለውና በአሜሪካ ኮንግረንስ የተላለፈው ውሳኔ ተግባራዊ እንዳይሆን ያደርጋል' በሚል ሰልፉ እንዲበተን አድርጉ የሚል ተልኮ እንደተቀበለም ክሱ አመልክቷል።

አንደኛ ተከሳሽ ጌቱ ግርማ ከሁለተኛ ተከሳሽ ብረሃኑ ጁፋር ጋር በሰኔ ሱሉልታ ላይ ስለ ተልኮው በመነጋገር ቦንብ እዲያዘጋጅ፣ ቦንቡን የሚወረውርን እንዲያፈላልግ ተነጋግረው ለሶስተኛ ተከሳሽ ጥላሁን ጌታቸው ደውሎ ቦንብ የሚወረውር ሰው እንዲፈልግ ተልኮ
መስጠቱም ክሱ ያሳያል።

ሁለተኛ ተከሳሽ ያዘጋጀውን ሁለት ኤፍ 1 ቦንብ እንዲሁም አንድ የጭስ ቦንብ በአንደኛ ተከሳሽ ቤት በማስቀመጥ ከሱሉልታ በመነሳት ሰልፉን በመቀላቀል በኛው ተከሳሽ አመካኝነት ቦንቡን በማፈንዳት ሙሳ ጋዲሰና ዬሴፍ አያለው የተበሉ ግለሰቦች ላይ የሞት 165 የሚሆኑ ሰዎች ላይ ከባድ ና ቀላል ጉዳት ማድረሳቸውም በክሱ ተጠቁሟል። በዘህም መሰረት ዓቃቢ ህግ ክስ መስርቶባቸዋል

ምንጭ፦ EBC

ሪፖርተር፦

ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. በመስቀል አደባባይ በተፈጸመው የቦምብ ጥቃት የተጠረጠሩ አምስት ግለሰቦች #የሽብርተኝነት ክስ ተመሠረተባቸው፡፡

በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ወንጀል ችሎት ዓርብ መስከረም 18 ቀን 2011 ዓ.ም. ክሱን ያቀረበው ዓቃቤ ሕግ፣ የቦምብ ጥቃቱ የተፈጸመው ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) #ለመግደል መሆኑን በክሱ አስታውቋል፡፡

በቦምብ ጥቃቱ ክስ የተመሠረተባቸው ተጠርጣሪዎች አቶ ጌቱ ግርማ፣ አቶ ብርሃኑ ጃፋር፣ አቶ ጥላሁን ጌታቸው፣ አቶ ባህሩ ቶሎሳና አቶ ደሳለኝ ተስፋዬ ናቸው፡፡

ዓቃቤ ሕግ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ክስ እንደገለጸው፣ ተከሳሾቹ በጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ ላይ ግድያ ለመፈጸም ያነሳሳቸው በእሳቸው የሚመራ መንግሥት #መኖር ስለሌለበት ነው፡፡ የአገሪቱ መንግሥት መመራት ያለበት ቀድሞ በተመሠረተው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ነው የሚል ዓላማ ተከሳሾቹ እንዳላቸው ዓቃቤ ሕግ በመሠረተው #ክስ ጠቁሟል፡፡

በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት የላቸውም በማለትም፣ ተጠርጣሪዎቹ ለግድያ መነሳሳታቸውን ዓቃቤ ሕግ አስታውቋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአሜሪካ ኮንግረስ የፀደቀውን ኤችአር 128 ለማስፈጸምና በስመ ሕዝበኝነት የራሳቸውን ዓላማ የሚያራምዱ መሆናቸውን፣ በዚህም ምክንያት የኦሮሞን ሕዝብ ፍላጎት ስለማያስፈጽሙ ተጠርጣሪዎቹ ጥቃቱን ለመፈጸም መነሳሳታቸቸውን ዓቃቤ ሕግ
በክሱ አክሏል፡፡

የሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. የመስቀል አደባባይ የወንጀል ድርጊት ያቀነባበረችው በኬንያ ናይሮቢ የምትገኝ ገነት ታምሩ (ቶለሺ ታምሩ) የምትባል መሆኗን፣ ዓቃቤ ሕግ በክሱ አመልክቷል፡፡

በመስቀል አደባባይ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ድጋፍና ምሥጋና በተደረገ ሥነ ሥርዓት ላይ በተፈጸመ የቦምብ ጥቃት ሁለት ግለሰቦች ሲሞቱ፣ ከ150 በላይ ጉዳት እንደደረሰባቸው ይታወሳል፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ሰመጉ⬇️

ሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ የተካሄደው #ጅምላ እስር በመንግሥት ሙሉ ማብራሪያ ሊሰጥበት እንደሚገባ፣ የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ሰመጉ) ጥያቄ አቀረበ፡፡ #ሰመጉ ይህን ጥያቄ ያቀረበው ዓርብ መስከረም 18 ቀን 2011 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ ነው፡፡

ሰመጉ በመግለጫው ምንም እንኳን ፖሊስ ከተማዋን #ለማረጋጋት ዕርምጃ መውሰዱ #ተገቢ እንደሆነ ቢያምንም፣ ‹‹ከሕግ አግባብ ውጪ ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ መጠነ ሰፊ እስራት መፈጸሙ፣ የጅምላ እስራቱ ሰላማዊ ዜጎችንም ጭምር ዒላማ ማድረጉ፣ ጥቂት የማይባሉ ታሳሪዎች ላይ ፖሊስ ድብደባ መፈጸሙ፣ በሕግ ወንጀል  እንዳልሆነ በግልጽ ባልተደነገጉ ሥፍራዎች ያገኛቸውን ዜጎች ማሰሩ፣ ከሕግ አግባብ ውጭ ከምሽቱ 12 ሰዓት በኋላ እስራቶቹ መፈጸማቸው፣ እንዲሁም ሰላማዊውን ሕዝብ ጭንቀት ውስጥ በከተተና ግልጽነት በጎደለው ሁኔታ የጅምላ እስሩን መነሻ ምክንያትና የታሳሪዎችን ዕጣ ፈንታ በፍጥነት ለሕዝብ ይፋ አለማድረጉ››፣ የፖሊስን ዕርምጃ ሕጋዊነት ጥያቄ ውስጥ የሚጥል እንደሆነ አስታውቋል፡፡

የእስሩን ገፈት የቀመሱ ግለሰቦች፣ ‹‹የተቀናቃኝ ፓርቲዎች አመራሮች ወደ አገር ቤት ሲመለሱ የአቀባበል ዝግጅቱን ለምን #አስተባበራችሁ? ለምን የፓርቲዎች ደጋፊዎች ሆናችሁ? የሚሉና ተመሳሳይ የምርመራ ጥያቄዎች እንደቀረበላቸው›› ሰመጉ ከታሳሪዎች ባገኘው መረጃ መሠረት ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡

ፖሊስ ታሳሪዎቹን በመደበኛ ፖሊስ ጣቢያዎች ለማቆየት ያልቻለበትን ምክንያት ግልጽ አላደረገም የሚለው ሰመጉ፣ ይህ የፖሊስ ድርጊት ‹‹የዜጎችን ሕገ መንግሥታዊ መብት በግልጽ የጣሰ በመሆኑ፣ ከሕግ አግባብ ውጪ የተያዙ፣ ክስ ሳይቀርብባቸው ወይም ሳፈረድባቸው የታሰሩ ዜጎች እንዲፈቱ፤›› በማለት ጥሪውን አቅርቧል፡፡

አገሪቱ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ውስጥ በነበረችበት ወቅት በተለያዩ ወታደራዊ ካምፖች ታስረው የነበሩ ዜጎች ይደርስባቸው የነበራት የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ትውስታ ከአዕምሮ ባልጠፋበት በዚህ ወቅት፣ ለሥልጠና በሚል ሰበብ መንግሥት ዜጎችን ወደ ወታደራዊ ካምፕ በማጋዙ ለሌላ ዙር መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳያጋልጣቸው የሚል ሥጋቱንም ሰመጉ ገልጿል፡፡

‹‹በሁከትና በግርግር ውስጥ ተሳትፈዋል በሚል በሕግ ሥር የሚገኙ ዜጎች ሰብዓዊ መብታቸውን ተጠብቆ የመያዝ መብታቸው እንዲከበር፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በወዳጆቻቸውና በሕግ አማካሪዎቻቸው የመጎብኘት መብታቸው እንዲጠበቅላቸው፣ እንዲሁም #ክስ ያልተመሠረተባቸው ዜጎች በፍጥነት እንዲለቀቁ፤›› ሲል ሰመጉ ጥያቄውን አቅርቧል፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ሻሸመኔ⬇️

በሻሸመኔ ከተማ ሰው በመግደልና ዘቅዝቆ በመስቀል ወንጀል የተጠረጠሩ 14 ግለሰቦች በቁጥጥር ስል አውሎ በስድስቱ ላይ #ክስ እንደሚመሰርት የከተማው ፓሊስ መምሪያ አስታወቀ።

ግለሰቦቹ ነሃሴ 6 ቀን 2010 ዓመተ ምህረት የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ዳይሬክተር አቶ #ጃዋር_መሀመድ አቀባበል ስነ ስርዓት ላይ ግርግር በመፍጠር አንድ ግለሰብን #በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሎ በመስቀል ወንጀል ጠርጠራቸውን የአቃቤ ህግ መዝገብ ይጠቁማል።

የከተማው ፓሊስ መምሪያ አዛዝ ኮማንደር መኮንን ታደሰ ለጣቢያችን እንዳሉት፥ ከተያዙት ተጠርጣሪዎች መካከል በስድስቱ ላይ አቃቤ ህግ ክስ ለመመስረት የሚያስችል በቂ ማስረጃ በማግኘቱ ክስ ለመመስረት መዘጋጀቱን  ተናግረዋል።

ተጠርጣሪዎቹ በዛሬው እለት በሻሸመኔ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፊት እንደሚቀርቡም አስታውቋል።

ነሃሴ 6 ቀን 2010 ዓመተ ምህረት በተፈጠረው ግርግርና ግፊያ የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ የከተማው ፓሊስ ተሽከርካሪ ቃጠሎ እንደደረሰበት ይታወሳል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አብዲ ኢሌ ላይ ክስ ተመሰረተ‼️

በሶማሌ ክልል የቀድሞው ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ #መሃመድ_ዑመርን ጨምሮ በ47 ግለሰቦች ላይ #ክስ ተመሰረተ።

ተከሳሾቹ አቶ አብዲ ሙሃመድ፣ ራህማ መሀመድ ሀይቤ፣ አብዱራዛቅ ሰሀኔ ኢልሚ፣ አቶ ፈርሃን ጣሂር በርከሌ፣ ጉሌድ ኦበል ዳውድ እና ወርሰሜ ሼህ አብዲ ሸሂድን ጨምሮ 47 ግለሰቦች ናቸው። ተከሳሾች በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የወንጀል ችሎት ነው ክስ የተመሰረተባቸው። ግለሰቦቹ ለጊዜው ካልተያዙ ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን በቀጥታ ወይም በአድራጎታቸው በወንጀሉ ተካፋይ በመሆን በህብረትና በማደም፥ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ቀኑ ባልታወቀ ሰኔ ወር 2010 ዓ.ም እስከ ሀምሌ 30 ቀን 2010 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናቶች በክልሉ ውስጥ አንዱ ወገን በሌላው ወገን ላይ የጦር መሳሪያ እንዲያነሳ ለማድረግ በማሰብ መንቀሳቀሳቸው
ተጠቅሷል።

በዚህም በአንዳንድ የሶማሌ ብሔር ተወላጆች እና በሶማሌ ክልል በሚኖሩ የሌሎች ብሄር ተወላጆች መካከል አለመግባባት እንዲፈጠር በማሰብ በግጭቱ ውስጥ የሚሳተፉና ሄጎ በሚል ወጣቶችን ማደራጀታቸውም በክሱ ተነስቷል። የተደራጀውን የሄጎ ቡድን በገንዘብ እና በተለያዩ ቁሳቁሶች በመደገፍ፣ መሳሪያ በማስታጠቅ፣ ግጭቱ የሚመራበትና መልዕክት የሚተላለፍበት ሄጎ ዋሄገን የሚል የፌስቡክ ገጽ በመክፈትና በተለያዩ ስብሰባዎች ላይ ሰዎችን ሊያነሳሱ የሚችሉ መልእክቶችን አስተላልፈዋልም ነው ያለው የአቃቢ ህግ ክስ

በኦሮሞ ወታደሮች ተወረናል፣ የኦሮሞ ተወላጆች መሬታችንን ለቀው መውጣት አለባቸው፣ ነዳጃችንን፣ መሬታችንን እና ወርቃችንን በጉልበት ሊወስዱብን ነው፣ የፌደራል መንግስት በህገወጥ መንገድ ሊወረን እና አዲስ መንግስት ለማቋቋም እንቅስቃሴ እያደረገ ነው፣ ሁላችንም አንድ በመሆን በክልላችን ውስጥ ከሶማሌ ብሄር ውጭ ያሉ ብሔረሰቦችን መግደል፣ ንብረታቸውንም መዝረፍ እና ማውደም፣ ባንኮችን እና ኢንሹራንሶችን መዝረፍ፣ ቤተክርስቲያኖችን እና ነዳጅ ማደያዎችን ማቃጠል አለብን የሚል ይዘት ያላቸውና ሌሎች መልዕክቶችም ተላልፈዋል ነው ያለው አቃቢ ህግ።

ከዚህ ጋር ተያይዞም ይህንን ማድረግ የሚያስችል የራሳችን ወታደሮች እና የተደራጁ የሔጎ አባላት አሉን በሚል እንዲሁም በስብሰባና በፌስ ቡክ ቅስቀሳ በማድረግ እንዲሁም የክልሉ አድማ ብተና ሃይልም ሄጎዎች የሚሰሩትን ማንኛውንም ነገር እንዳይከላከል ከካምፕ እንዳይወጣ ትእዛዝ ሰጥተዋልም ተብሏል።

እንዲሁም በክልሉ ውስጥ ግጭት እንዲነሳ በማድረግና በግጭቱ ምክንያት የሰው ህይወት እንዲጠፋ፣ በመንግስት እና በእምነት ተቋማት እንዲሁም በግለሰብ ንብረት ላይ ጉዳት እንዲደርስ፣ ሴቶች እንዲደፈሩና እና በርካታ የከተማው ነዋሪ እንዲፈናቀል ማድረጋቸውም በክሱ ተካቷል። በአጠቃላይ ከ1ኛ እስከ 26ኛ ተራ ቁጥር የተመለከቱት ተከሳሾች ከላይ በተገለጸው አግባብ በመቀስቀስና በማነሳሳት በዚህ የማነሳሳት ተግባራቸው በሶማሌ ብሔር ተወላጆች እና በክልሉ የሚኖሩ ሌሎች ብሔሮች መካከል አለመግባባት እና ግጭት እንዲፈጠር አድርገዋልም ነው የተባለው።

በዚህ ግጭትም በሰነድ ማስረጃው ላይ በተገለፀው አግባብ ከ59 ሰዎች በላይ ህይወት እንዲጠፋ፣ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑ ካህናት እና የእምነቱ ተከታይ የሆኑ ግለሰቦች በአሰቃቂ ሁኔታ ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ በመግደልና በእሳት እንዲቃጠሉ ማድረጋቸው በክሱ ተነስቷል። ከ266 በላይ ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት እንዲደርስ፣ በምስክርነት የተጠቀሱ ሴቶችን በሄጎ ቡድን እና በክልሉ ልዩ ሀይል ፖሊስ አባላት እንዲደፈሩ በማድረግ እንዲሁም ግምቱ 412 ሚሊየን 468 ሺህ 826 ብር በላይ የሚሆን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን፣ የመንግስት፣ በግለሰብ መኖሪያ ቤትና የንግድ ድርጅት ንብረቶች እንዲቃጠሉ፣ እንዲዘረፉ እና ብዛታቸው በውል ያልታወቁ ከሶማሌ ብሔር ተወላጅ ውጭ የሆኑ የከተማው ነዋሪዎች ከቤትና ንብረታቸው እንዲፈናቀሉ አድርገዋልም ነው የሚለው ክሱ።

በዚህም ተከሳሾች በፈፀሙት የጦር መሳሪያ ይዞ በማመጽ ወይም የእርስ በእርስ ጦርነት በማስነሳት በመንግስት ላይ የሚደረግ ወንጀል ክስ ቀርቦባቸዋል። በዛሬው እለት ተከሳሾች ከጠበቆቻቸው ጋር የቀረቡ ባለመሆናቸው ክሳቸውን በንባብ ለመስማት ፍርድ ቤቱ ለጥር 29 ቀን 2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በተያያዘም አቶ ቴዎድሮስ አዲሱ (ቴዲ ማንጁስ) በ80 ሺህ ብር ዋስ እንዲወጣ ተፈቅዶለታል። ቴዲ ማንጁስ በሶማሌ ክልል በተፈጠረው ግጭት የሰው ህይወት መጥፋትና መፈናቀል ወንጀል ላይ ተሳትፏል በሚል መጠርጠሩ ይታወሳል።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 22/2011 ዓ.ም.

በሶማሌ ክልል የቀድሞው ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ #መሃመድ_ዑመርን ጨምሮ በ47 ግለሰቦች ላይ #ክስ ተመስርቷል።
.
.
ለከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት ላይ ያሉትን ‹‹ቪ8›› መኪኖች በሌሎች አዳዲስና ወጪ ቆጣቢ ተሽከርካሪዎች የመተካቱ ሂደት በመጠናቀቅ ላይ መሆኑ ተገልጿል።
.
.
በድሬዳዋ ከተማ ተፈጥሮ በነበረው #አለመረጋጋት እና የተቃውሞ ቀናት ጉዳት ሳይደርስበት በሀሰት ጉዳት የደረሰበት በማስመሰልና ይህንን የሃሰት ፎቶ በማህበራዊ ድረ ገፅ በመልቀቅ ግጭቶች እንዲፈጠሩ ለማድረግ የሞከረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡
.
.
በቅርቡ የፀደቀውን የስደተኞች አዋጅ በመቃወም በአዲስ አበባና በጋምቤላ #የተቃውሞ_ሠልፍ ሊደረግ እንደሆነ ተሰምቷል።
.
.
በሶማሌ ክልል ግጭት፣ ግድያና ቃጠሎ ጋር በተያያዘ ከአራት ወራት በላይ በእስር ላይ የነበረው #ቴዎድሮስ_አዲሱ (ቴዲ ማንጁስ) በ80,000 ብር ዋስ ከእስር እንዲፈታ ፍርድ ቤት ትእዛዝ ሰጥቷል።
.
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ባለስልጣን "ግዴታዬን እወጣለሁ ፣ መብቴንም እጠይቃለሁ!" በሚል መርህ ቃል የከተማ አቀፍ የታክስ ንቃናቄ መድረክ ተካሂዷል።
.
.
ከኮንሶ ዞን ወደ ሶያማ ቡርጂ ወረዳ ሲጓዝ በነበረ የጭነት መኪና ላይ ባልታወቁ #ታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ በትላንትናው ዕለት የአራት ሰዎች ህይወት አልፏል።
.
.
#በምሥራቅ_ወለጋ_ዞን በተለያዩ ወረዳዎች የሚገኙ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎች 2ሺህ 380 ዩኒት ደም መለገሳቸውን የነቀምቴ ደም ባንክ አገልግሎት አስታውቋል።
.
.
የመልካም አስተዳደርና የሥራ  አጥነት መሠረታዊ ጥያቄዎች በፍጥነት ለመመለስ የሚያግዝ የ60 ቀናት ዕቅድ ተዘጋጅቶ እንቅስቃሴ መጀመሩን የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ተናግረዋል።
.
.
ሰሞኑን በድሬዳዋ በተፈጠረው ሁከትና ነውጥ #በማራገብ ሂደት #ፖሊስ እና #አድማ_በታኝ አሉበት፤ ይህም በፖሊስ ውስጥ መሠረታዊ ሪፎርም እንደሚያስፈልግ ያመለክታል ተብሏል።
.
.
15ኛው የኢትዮ-ጅቡቲ የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ በዛሬው ዕለት በጂቡቲ ተጀምሯል፡፡
.
.
ትናንት በሶማሌ ክልል መዲና- ጅግጅጋ የሃይማኖት ክብረ በዓልን ተከትሎ በተፈጠረ ግጭት ሁለት ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል።
.
.
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ እና የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው #በኔዘርላንድ የሚገኙ ኩባንያዎችን ጎብኝተዋል።
.
.
የኢትዮጵያ #ጉብኝታቸዉን አጠናቀዉ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ በዝግጅት ላይ ያሉት የጀርመኑ ፕሬዝዳንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር የሚበሩበት አዉሮፕላን የቴክኒክ #እክል ገጥሞት መዘግየቱ ተሰምቷል።
.
.
ከአዲስ አበባ ወደ ነቀምት በህገ-ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረ 11 ሺህ ሊትር ነዳጅ መያዙን የኢሉገላን ወረዳ ፖሊስ አስታውቋል።
.
.
በአማራ ክልል በአምሀራ ሳይንት ወረዳ በአጅባር ከተማ በተቀሰቀሰ #ተቃውሞ የመንግስትም ሆነ የግል ተቋማት ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ማቋረጣቸውን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
.
.
ከጥረት ኮርፖሬት የሃብት ምዝበራ ጋር በተያያዘ የአምባሰል ንግድ ስራዎች ስራ አስኪያጅ የነበሩትን አቶ #ምትኩ_በየነን ጨምሮ አምስት ሰዎች ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ በህግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
.
.
የኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያና ዩጋንዳ የፖሊስ አመራሮችና አቃቤ ሕጎች የሶስት ቀናት አውደጥናትን ዛሬ #በኤርትራ_አስመራ ተጀምሯል፡፡
.
.
በአለም ላይ ያለውን የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ጭማሪን ግምት ውስጥ በማስገባት እና በህዳር ወር ተደረገው ዋጋ #ማስተካከያ ዝቅተኛ በመሆኑ፥ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ #መጠነኛ_ጭማሪ ማድረጉን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ምንጭ፦ etv፣ fbc፣ የጀርመን ራድዮ፣ ኢ.ፕ.ድ፣ ኢዜአ፣ የንግድ እና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት

ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሜቴክ አመራሮች ላይ ክስ ተመሰረተ‼️

ለሁለት ስኳር ፋብሪካዎች የውሃ መርጫ መሳሪያ ሳያስፈልግ በራሳቸው ፍቃድ እንዲገዛ በማድረግ ከ15 ሚሊየን ብር እንዲባክን አድርገዋል የተባሉ ሶስት ግለሰቦች ላይ #ክስ ተመሰረተ።

ክሱ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 15ኛ የወንጀል ችሎት ለተከሳሾቹ እንዲደርሳቸው ተደርጎ በችሎት ተነቧል።

ተከሳሾቹ 1ኛ የብረታብረትና ኢንጂነሪንግ የማኑፋክቸሪንግ እና ማሽን ግንባታ ስራ አስኪያጅ ሌተናል ኮሎኔል ተሰማ ግደይ፣ 2ኛ በሜቴክ ማኑፋክቸሪግና ግንባታ ስራ ምክትል ስራ አስኪያጅና የግብይትና ሽያጭ ክፍል ሃላፊ ሻለቃ መስፍን ስዩም እንዲሁም 3ኛ በንግድ ስራ የተሰማሩት አቶ ክፍላይ ንጉሴ ናቸው።

1ኛ እና 2ኛ ተከሳሾች ከ2004 እስከ 2008 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት ለፊንጫና ወንጂ ስኳር ፋብሪካዎች የውሃ መርጫ መሳሪያ ሳያስፈልግ በራሳቸው ፍላጎትና በወቅቱ የማምረት ፍቃድ ከሌለው ከ3ኛ ተከሳሽ ክፍላይ ንጉሴ ውል በመዋዋል ግዥ እንዲፈጸም ማድረጋቸው በክሱ ተጠቅሷል።

በዚህ መልኩ በተፈጸመ ያለአግባብ ግዥ ከ15 ሚሊየን ብር በላይ እንዲባክን ማድረጋቸውን እና የውሃ መርጫ መሳሪያው እስካሁን አገልግሎት ላይ ሳይውል መቀመጡ በክሱ ተመላክቷል።

ተከሳሾቹ የተነበበላቸው ክስ ላይ መቃወሚያ ካላቸው ለመመልከት ችሎቱ ለየካቲት 6 ቀን 2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ምንጭ፦ FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️

አቶ #ኢሳያስ_ዳኛው ከ 44.5 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በሚሆን ከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው #ክስ ተመሰረተባቸው፡፡

ተከሣሽ በኢትዩ ቴሌኮም የኤን.ጂ.ፒ.ኦ. (N.G.P.O.) ዳይሬክተር ሆነው ሲሰሩ የተጣለባቸውን ከፍተኛ የመንግሥት
ኃላፊነት ወደጎን በመተው በተሰጣቸው የሥራ ሥልጣን መሠረት ዜድ.ቲ.ኢ. (ZTE) ከተባለ የቻይና ኩባንያ ጋር የ44‚ 510‚ 971.00 (አርባ አራት ሚሊዩን አምስት መቶ አስር ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰባ አንድ) የአሜሪካን ዶላር የግዥ ውል ለጊዜው ስማቸው በክሱ ውስጥ ካልተጠቀሱት (እና ካልተያዙ) ግብረአበራቸው ጋር ቀጥታ ግዥ እንዲፈጸም በማድረግ በስውር ጥቅም በመመሳጠር በመንግሥትና በኮርፖሬሽኑ የተሰጣቸውን ሹመት፣ ሥልጣን ወይም ኃላፊነት በግልጽ ተግባር ወይም በግድፈት ያላግባብ በመገልገል እንዲሁም ከተሰጣቸው ሥልጣን በላይ አልፎ በመስራት የማይገባውን ጥቅም ለማገኘት እንዲሁም ለዜድ.ቲ.ኢ. (ZTE) ለማስገኘት እና በመንግሥትና በኢትዩ ቴሌኮም ኮርፖሬሽን ጥቅም ላይ ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል፡፡

አቅራቢው ኩባንያም ካቀረባቸው ቴክኒካል ሰነዶች ሊገዛ የታሰበውን ዕቃ ወይም አገልግሎት በተጠየቀው ቴክኒካል እስፒሴፊኬሽን መሠረት በግልጽና በተሟል መልኩ ለማቅረብ ወይም ለመሸጥ መስማማቱ ባልተረጋገጠበት ሁኔታ፣ የዕቃውን ወይም የአገልግሎቱን የማቅረቢያ ጊዜ፣ የቅድመ ክፍያ ዋስትና፣ የአከፋፈል ሁኔታን፣ የመልካም ሥራ አፈጻፀም ዋስትና በገምጋሚ ኮሚቴ ባልተገመገመበት ሁኔታ ተከሣሽ ግዥ እንዲፈጸም ፈቅደዋል፡፡

ተከሣሽ ለዩኒቨርሲቲዎች የኔትዎርክ ግንባታ የአገልግሎት ግዥ ውል ኤን.ጂ.ፒ.ኦ. ሊጠቀምበት ይገባ የነበረውን የግዥ ማንዋል ያልተጠቀሙና በኢትዩ ቴሌኮም የግዥ መመሪያ፣ ፖሊሲና የሥነ- ሥርዓት ማንዋል እና በሌሎች አግባብነት ባላቸው የግዥ ሕጎች መሠረት በግልጽ ጨረታ በማወዳደር ከፍተኛ ብቃት ያላቸውን ተወዳዳሪዎች በመጋበዝ ከጊዜ፣ ከሐብትና ከቴክኖሎጂ አኳያ የተሻለውን መግዛት ሲገባው የግዥ ሥራን በማያመች አኳኃን በመምራትና በማስፈፀም #በኢትዩ_ቴሌኮም ላይ ከፍተኛ ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉ በመሆናቸው በመላ ሃሳባቸውና በወንጀል ድርጊቱና በውጤቱ በሙሉ ተካፋይ በመሆን በዋና ወንጀል አድራጊነት የመንግሥትን ሥራ በማያመች አኳኃን በመምራት ከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል።

በሌላ በኩል መርማሪ ፖሊስ ከዚህ ቀደም አቶ ኢሳያስ ዳኘው ከሌሎች ግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን ያለውድድርና ጨረታ ‘ኢዲኤም’ የተባለ የውጭ አማካሪ ድርጅት ጋር ውል በመፈጸም መጠርጠራቸውን አዲስ የምርመራ መዝገብ ከፍቶ ክረክር ያደረገ ቢሆንም በተጠረጠሩበት በከባድ የሙስና ወንጀል በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 10ኛ የወንጀል ችሎት ቀርበው ጉዳያቸውን ሲከታተሉ ከቆዩ በኋላ በ50 ሺህ ብር ዋስ እንዲወጡ ተፈቅዶላው የነበረ ሲሆን መርማሪ ፖሊስም ግለሰቡ በዋስ መውጣት የለባቸውም በሚል ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ማለቱ ይታወቃል፡፡

ይሁን እንጂ ፍርድ ቤቱ ዛሬ ጠዋት በዋለዉ ችሎት ከዚህ ቀደም በተወሰነው መሰረት ከሃገር እንዳይወጡ በተጣለ እገዳ በ50 ሺህ ዋስ እንዲለቀቁ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔውን ያጸና ቢሆንም ዛሬ ከሰዓት ዐቃቤ ህግ #በተከሳሹ ላይ ባቀረበው ከባድ የሙስና ወንጀል ተከስ ተከሳሹ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 15ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ክሳቸው ተነቦ እንዲረዱት የተደረገ ሲሆን የክስ መቃወሚያቸውን ይዘው ለመቅረብ ለ19/06/2011 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡

ምንጭ፦ የፌዴራል ጠ/አቃቤ ሕግ
@tsegabwolde @tikvahethiopi
TIKVAH-ETHIOPIA
#ነዳጅ " 10 ሰዓት ተኩል ላይ ነዳጁን ማራገፋቸውን ሪፖርት ካላደረጉ ርምጃ ይወሰዳል " - የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ከጂቡቲ ተነስተው አዲስ አበባ እና የተለያዩ ዋና ከተሞች መድረስ የነበረባቸው 200 ነዳጅ ጫኝ ቦቴዎች ከአዲስ አበባ ውጪ በየሠፈሩ ተደብቀው መገኘታቸውን የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታወቀ። የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ ሰዓረላ አብዱላሂ በሰጡት መግለጫ " በተለይ…
#Update

ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች ትናንት እስከ ቀኑ 10፡30 ድረስ ወደየመዳረሻ ከተሞች ገብተው የጫኑትን ነዳጅ እንዲያራግፉ ያንን ካላደረጉ ግን እንዲወረሱ ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል።

ትላንት ነዳጁን እንዲያራግፉ ማሳሰቢያ ከተሰጣቸው 200 ቦቴዎች መካከል እስካሁን ትዕዛዙን የፈፀሙት 22 ብቻ ናቸው ተብሏል።

ከመካከላቸው 18ቱ አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን 3ቱ ዱከም፣ 1ዱ ሞጆ፣ 1ዱ አዳማና ሌላ 1 ቦቴ ቢሾፍቱ ከተማ ገብተው ማራገፋቸው ተነግሯል፡፡

ምናልባት ቦቴዎች ደርሰው ግን ሪፖርት ያላደረጉ የክልል ከተሞች ካልተገኙ በቀር ቀሪዎቹ 180 የሚጠጉት ቦቴዎች የጫኑን ነዳጅ መንግስት በውሳኔው መሰረት #ይወርሳል ተብሏል፡፡

ከጅቡቲ የተነሱና ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች ወደ አዲስ አበባና ወደ ተለያዩ መዳረሻ ቦታዎቻቸው ገሚሱ ከቀናት በፊት፤ ገሚሱ ከሳምንት በፊት መድረስ የነበረባቸው ቢሆንም 200 ያህሉ በየጥጋጥጉ ተደብቀው ተገኝተዋል።

የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዳሬክተር ወ/ሮ ሳህረላ አብዱላሂ ፥ እስከ ትናንት ቀኑ 10፡30 ድረስ ወደየመዳረሻቸው ደርሰው ነዳጁን አራግፈው ሪፖርት ካላደረጉ እንደሚወረሱ ለባለቤቶቹ መነገሩን ያስታወሱት ዳይሬክተሯ ዛሬ ሪፖርቱ ተጣርቶው ውሳኔው ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል።

እንዲህ ባለ አሻጥር ምክንያት ለአዲስ አበባ ከተመደወበው ኮታ 1/3ኛ ያህሉ ብቻ ናፍጣ እየገባ ስነበር ከሰሞኑ በከተማዋ የተከሰተውን እጥረትም አንስተዋል፡፡

ችግሩ እንዲፈጠር ምክንያት የሆኑትን መረጃቸውን ለፍትህ ሚኒስቴር ልከን #ክስ እንዲመሰረትም እናደረጋለን ብለዋል።

(ሸገር ኤፍ ኤም 102.1)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከ60 በላይ የጤና ባለሙያዎች ፤ " ጤና ሚኒስቴር በሕግ የተወሰነልንን ልዩ አበል አልከፈለንም " አሉ። የጤና ባለሙያዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት፤ የኮቪድ - 19 ወረርሽኝ መጋቢት 8 ቀን 2012 ዓ / ም መከሰቱን ተከትሎ የጤና ማኒስቴር ባወጣው ጥሪ መሠረት የኢፌደሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ግንቦት 18 ቀን 2012 ዓ / ም ባወጣው መመሪያ የሕክምና አገልግሎት ለሚሰጡ ለመላው ሀኪሞች በቀን…
#ጤና_ሚኒስቴር #ክስ

የፍርድ ቤት ውሳኔን በተደጋጋሚ ጣሰ የተባለው " ጤና ሚኒስቴር " ለ70 የጤና ባለሙያዎች የኮቪድ -19 ልዩ አበል እንዲከፍል ፍርድ ቤት በድጋሚ ለንግድ ባንክ ትዕዛዝ አስተላለፈበት።

70 የጤና ባለሙያዎች የኮቪድ ወረርሽኝ #ልዩ_አበል እንዲሰጣቸው በመሰረቱበት ክስ መሠረት ገንዘቡን እንዲከፍል ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሳኔ በተደጋጋሚ ጥሷል የተባለው " ጤና ሚኒስቴር " አሁንም ከንግድ ባንክ አካውንቱ #እየቆረጠ_እንዲከፍል ፍርድ ቤት በድጋሚ ለንግድ ባንክ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጤና ባለሙያዎቹ ገለጻና ከተጻፈው ደብዳቤ መረዳት ችሏል።

የጤና ባለሙያዎቹ ተወካይ የፍርድ ሂደቱ በተመለከተ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?

* ፍርድ ቤት ለባንክ ሲያዝ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው።

* የፋይናንስ ክፍሉ ኃላፊ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ድክመት ለፍርድ ቤት #ታስረው ቀርበው እንዲያስረዱ ቢታዘዝም ጉዳዩን እንዲያስፈፅም የታዘዘው የፌደራል ፖሊስ መስሪያ ቤቱ ድርስ በመሄድ ቢጠይቅም እረፍት እንደወጡና እስከ ሰኞ (ያለፈው ሳምንት ሰኞ) እንደሚመጡ አሳውቀው ነበር። ከዚያ በኋላም ፍርድ ቤት መጥተው አያውቁም።

* ታስረው እንዲቀርቡም #ከሁለት_ጊዜ_በላይ ነው የታዘዘው።

* ፍርድ ቤት በራሳቸው እንዲፈፅሙ ግን በተደጋጋሚ (ከአምስት ጊዜ በላይ) ትዛዝ ሰቶ ነበር።

* ሰዎቹ በፍፁም ለህግ ተገዢ አለመሆናቸውን እና እምቢተኝነታቸውን በተደጋጋሚ ጊዜ አሳይተውናል።

* ለፍርድ ቤት ውሳኔ ያላቸው ንቀት በቃላት የሚገለፅ አይደለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፤ ይሄንን የጤና ባለሞያዎች መረጃ በማደራጀት ሂደት የጤና ሚኒስቴርን ምላሽ እና ማብራሪያ ለማካከት ብዙ ቢደክምም ምላሽ ሰጪ አላገኘም።

አሁንም #በአካልም ይሁን #በስልክ ምላሽ ሰጣለሁ የሚል የሚኒስቴር መ/ቤቱን አካል ለማስተናገድ ዝግጁ ነው።

ዝርዝሩን ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-14

የመረጃው ዝግጅት በአዲስ አበባ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia