TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኢህአዴግ የደርግ መሰል #የቤት_ልማት_ፖሊስ ተግባራዊ ሊያደርግ ነው ተብሏል። በሀዋሳ በተደረገው የድርጅቱ 11ኛ ጉባኤ ላይ በቀረበው ሰነድ መሰረት #የመጠለያ ችግርን ከመቅረፍ አንፃር መሬት እና ፋይናንስ በማቅረብ ዜጎች ቤታቸውን #በራሳቸው ገንብተው የቤት ባለቤት የሚሆኑበት አሰራር ተግባራዊ ይደረጋል። መንግስት ቤት በራሱ ገንብቶ ለህብረተሰቡ ተደራሽ አደርጋለሁ ሲል ቢቆይም ከፍላጎት አንፃር መሄድ ያልቻለ እና #በሙስና እና #ብልሹ አሰራር የተተበተበ መሆኑ ሲያስተቸው መቆየቱ አይዘነጋም። በአዲሱ እቅድ መሬት እና ብድር ተመቻችቶ ቤት ፈላጊዎች በራሳቸው ይገነባሉ። ይህ አሠራር ደርግ እስከ መውደቂያው እለት ሲተገብረው የነበረ እና በርካቶችን እንዳ አቅማቸው የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ያደረገበት ፖሊሲ እንደነበር ይታወሳል።

ምንጭ፦Muluken Yewondwossen,ENF
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ዛሬ መግለጫ ይሰጣል። መግለጫው በቅርቡ በሰብአዊ መብት ጥሰትና #በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ እና በቁጥጥር ሥር እየዋሉ በሚገኙ ከፍተኛ አመራሮች እና
በሌሎች ወቅታዊ የፍትሕ ሥርዓት ጉዳዮች ላይ የሚሰጥ ነው ተብሏል። መግለጫው ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ እንደሚሰጥ ከጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፍፁም የሺጥላ🔝የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛ #ፍጹም_የሽጥላ ከሜቴክ ጋር በተያያዘ #በሙስና ወንጀል ተጠርጥራ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርባለች። በችሎቱ የተከላካይ ጠበቃ ልታገኝ ባለመቻሏ ፍርድ ቤቱ ለነገ ከሰዓት በኋላ 8 ሰዓት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የጃፓኑ መኪና አምራች ኩባንያ የኒሳን ሊቀመንበር ካርሎስ ጆሰን #በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው #ታሰሩ፡፡

ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቴዎድሮስ በእስር ላይ ይገኛል‼️

#ቴዎድሮስ_አዲሱ(ቴዲ ማንጁስ) በ80 ሺህ ብር ዋስ ቢፈቀድለትም #በሙስና_ወንጀል ተጠርጥሮ በእስር ላይ ይገኛል፡፡

ቴዎድሮስ አዲሱ ከሀምሌ 28-30 ቀን 2010ዓ.ም በጀጅጋ እና አካባቢው ተከስቶ በነበረው ሁከትና ብጥብጥ ተጠርጥሮ በተደጋጋሚ ፍርድ ቤት ቢቀርብም ዐቃቤ ህግ በጉዳዩ ላይ ምርመራውን ስላላጠናቀቀ እና በተደጋጋሚ የጊዜ ቀጠሮ መጠየቁ #ፍትሃዊ አለመሆኑንና የግለሰቡን ፍትህ የማግኘት መብት የሚጎዳ መሆኑን በማመን መዝገቡ እንዲዘጋ የጠየቀ ሲሆን ፍርድ ቤቱም በ80 ሺህ ብር ዋስ #እንዲወጣ ፈቅዶ ነበር፡፡

ሆኖም ግን ግለሰቡ በሌላ ወንጀል ከቀድሞው የሱማሌ ክልል ምክትል የትምህርት ቢሮ ኃላፊና ከኒያላ ኢንሹራንስ የጅጅጋ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ጋር በመመሳጠር #በተጭበረበረ የኢንሹራንስ ዋስትና አፈጻጸም የቅድመ ክፍያ ቦንድ ከኢንሹራንስ እንዲጻፍ በማድረግ በውሉ ላይ ከተጠቀሰው ቅድመ ከፍያ ላይ ብር 15,306,303.3 ከክልሉ ትምህርት ቢሮ ወጪ በማድረግ የወሰደ በመሆኑ ለትምህርት ቤቱ መፀሐፍቱን ሳያቀርብ ገንዘቡን ከጥቅም ተጋሪዎች ጋር በመከፋፈል ለግል ጥቅማቸው አውለዋል በሚል በሙስና ወንጀል ተጠርጥሮ ምርመራ እየተካሄደበት ይገኛል፡፡

መርማሪ ፖሊስ በቴዎድሮስ አዲሱ ላይ #በከባድ የሙስና ወንጀል የጀመረውን ምርመራው ለማከናወን የ14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደለት ተጠርጣሪው በእስር ቤት እንዲቆይ እና ለየካቲት 5 ቀን 2011 እንዲቀርብ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ምንጭ፦ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 23/2011 ዓ.ም.

ከትራንስፓርት ሚንስቴርና ከሌሎች ሚንስቴር መስሪያ ቤቶች የተወጣጣው የሉኡካን ቡድን የጅቡቲ ወደብን ጎብኝቷል።
.
.
ባሳለፍነዉ ሳምንት መጨረሻ በምዕራብ እንዲሁም ምሥራቅ ጉጂ በኢትዮጵያ መከላከያ ኃይልና በኦሮሞ ነጻነት ግንባር ታጣቂዎች መካከል በታካሄደ ግጭት የሰው ህይወት ማለፉን በርካቶች ከቤታቸው መፈናቀላቸው ተናግረዋል።
.
.
ከአመት በፊት ሳውዲ አረቢያ ጀምራው የነበረውን መጠነ ሰፊ የፀረ-ሙስና ዘመቻ እንዳጠናቀቀች አስታውቃለች፡፡ የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት 100 ቢሊዮን ዶላር በጥሬ ገንዘብ እና በቁስ መልክ በቁጥጥር ሥር ከዋሉት ሰዎች መሰብሰቡን አስታውቋል።
.
.
የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር በቅርቡ የፀደቀውን #የስደተኞች_አዋጅ በመቃወም ነገ በጋምቤላ ከተማ ሊደረግ ለታሰበው የተቃውሞ ሰልፍ ፈቃድ #ከልክሏል
.
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለ6 ሺህ ነጋዴዎች ግብር ሰርዣለሁ ብሏል፡፡ ግብር ስረዛው ከ2003 እስከ 2010 ዓ.ም ባለው ጊዜ ከፍተኛ የግብር ተመን ተጥሎባቸው አቤቱታ ሲያቀርቡ የቆዩትን ነጋዴዎች ያካትታል፡፡
.
.
4ኛው የህዝብና ቤት ቆጠራ ከመጋቢት 29 ቀን ጀምሮ ይካሄዳል።
.
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ህግን ተከትለው የሚሰሩ የሪል ስቴት አልሚዎችን እንደሚደግፍ ነገር ግን ህገወጥ የሆኑት ላይ #ዕርምጃ እንደሚወስድ አስታውቋል።
.
.
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ጃማ ወረዳ በጫነው አሸዋ ላይ 31 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ሲኖትራክ ተሽከርካሪ ተገልብጦ የሰዎች ህይወት እና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።
.
.
በቴፒ ከተማ ከትንላንት ጀምሮ ዳግም #ያገረሸው #አለመረጋጋት ዛሬም ቀጥሏል። የንግድ እና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ተቋርጦ ውሏል። ከተማዋ በፀጥታ ሃይሎች በከፍተኛ ደረጃ እየተጠበቀች ነው።
.
.
ዛሬ በስራ ላይ የሚውለውን የነዳጅ ዋጋ መጨመር ተከትሎ ምንም አይነት #የትራንስፖርት_ታሪፍ  ጭማሪ #እንደማይኖር የፌደራል ትራንስፖርት ባለስልጣን ገልጿል።
.
.
ጅቡቲ በተካሄደው 15ኛው የሚኒስትሮች የጋራ ኮሚሽን ስብሰባ ላይ የተካፈሉ የኢትዮጵያ ልዑካን ከሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያይተዋል።
.
.
በኦሮሚያ ክልል ለመንግስት ሰራተኞች #አዲስ የስራ ምደባ እየካሄደ መሆኑን የክልሉ የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ አስታውቋል።
.
.
#ኮማንድ_ፖስቱ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 3 ወረዳዎች ላይ በቁጥጥር ስር ካዋላቸዉ 528 ተጠርጣሪዎች 440 የሚሆኑትን በነፃ አሰናብቷል።
.
.
የአዋሽ ወልድያ ሃራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት የመጀመሪያው ምዕራፍ የሆነው ከአዋሽ እስከ ኮምቦልቻ ያለው 270 ኪሎ ሜትር የባቡር መንገድ ግንባታ 97 በመቶ #መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ገልጿል።
.
.
በሱማሌ ክልል ከምሽቱ 4 ሰዓት ጀምሮ ሰዓት ዕላፊ ገደብ ተጥሏል፡፡ የአደባባይ ስብሰባም ተከልክሏል፡፡
.
.
#ቴዎድሮስ_አዲሱ(ቴዲ ማንጁስ) በ80 ሺህ ብር ዋስ ቢፈቀድለትም #በሙስና_ወንጀል ተጠርጥሮ በእስር ላይ እንደሚገኝ ተሰምቷል።
.
.
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በኩል ለሚያልፉ ዐለም ዐቀፍ መንገደኞች #የነጻ ጉብኝት መርሃ ግብር ማዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡
.
.
የኢትዮጵያ ሚዲያ ካውንስል፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ዘርፍ ማህበር እና #የሰላም_ሚኒስቴር በጋራ በመሆን የሰላም ሚዲያ ህብረት ትስሰር ለመፍጠር የሚያስችል ውይይት ዛሬ ማምሻውን አካሂደዋል።
.
.
የሐረሪ ክልል የሰላምና ጸጥታ ሁኔታ #መሻሻል ማሳየቱን የክልሉ ፍትህና ጸጥታ ጉዳይ ቢሮ  አስታውቋል።
.
.
#ብሄሬን መሰረት ተደርጎ ጥቃት ተፈፅሞብኛል በሚል በሀሰት የሽንት መሽኛ #ብልቱን በፋሻና ፕላስተር በመጠቅለል ግጭት ለመቀስቀስ የሞከረው ግለስብ ድሬ ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሏል።
.
.
በአዲስ አበባ ከተማ በዳቦ ላይ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ አግባብነት የሌለውና ህብረተሰቡን ያላማከለ ነው ሲሉ ነዋሪዎች ቅሬታቸውን አሰምተዋል።
.
.
በሺህዎች የሚቆጠሩ ቤተ እስራኤላውያን አንድ #ኢትዮጵያዊ በእስራኤል ፖሊስ መገደሉን በመቃወም ቴላቪቭ ውስጥ ትናንት የተቃውሞ ሰልፍ አካሂደዋል።
.
.
በአሜሪካ በተከሰተው ከፍተኛ ቅዝቃዜ እስካሁን ቢያንስ ስምንት ሰዎች #መሞታቸው ተገለጸ፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው በአሜሪካ ሜድ ዌስት የተከሰተው ቅዝቃዜ በአስር አመታት ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ አደገኛ ነው፡፡
.
.
ምንጭ፦ etv፣ የጀርመን ራድዮ፣ ኢ.ፕ.ድ.፣ ዋዜማ ራድዮ፣ fbc፣ ኢዜአ፣ bbc፣ VOA፣ የሰላም ሚኒስቴር፣ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት
.
.
ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
#TikvahEthiopia #ቲክቫህኢትዮጵያ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዝርዝር የቀድሞ የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት የነበሩት ዶ/ር ጫላ ዋታ  ዛሬ ያለመከሰስ መብታቸው ተገፏል። የምክር ቤቱ የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስለ ዶ/ር ጫላ ዋታ ምን አለ ? #የመንግስት_ግዥ_ህግ ከሚፈቅደው አሰራር ውጭ በመሄድ የውስጥ ገቢ ማስገኛ በሚል " ቢኤችዩ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነሪንግ ጄነራል ሌቭል 1 ፒኤልሲ " የተባለ አማካሪ ድርጅት በማቋቋም በስማቸው ንግድ ፍቃድ በማውጣት…
" በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ነው " - የፍትህ ሚኒስቴር

ትላንት ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው የፓርላማ አባሉ ዶ/ር ጫላ ዋታ ዛሬ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቋል።

የቀድሞው የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጫላ ዋታ፤ #ዛሬ_ረቡዕ ረፋድ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፍትሕ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬትን ዋቢ በማድረግ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድረገፅ ዘግቧል።

ዶ/ር ጫላ በፌደራል ፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር የዋሉት #በሙስና_ወንጀል_ተጠርጥረው መሆኑን ዳይሬክቶሬቱ ለድረገፁ በሰጠው ቃል ገልጿል።

ማስታወሻ ፦ ዶ/ር ጫላ ዋታ የተጠረጠሩባቸው የሙስና ጉዳዮች ምንድናቸው ? እሳቸውስ ትላንት ለህ/ተ/ም/ቤት ምን አሉ ? መለስ ብለው በዚህ ያንብቡ : https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/77517

@tikvahethiopia
" በህግ ማስከበር ስም የድሆችን ቤት እና ቤተ እምነቶችን ማፍረስ ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው " - ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ

ነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ ባወጣው መግለጫ ፤ በአዲስ አበባ ከተማ ዙሪያ በአዲስ መልክ በመደራጀት ላይ ባለው " ሸገር ከተማ " ባለፉት ጥቂት ወራት ህገ ወጥ ግንባታዎችን ለመከላከል በሚል በተወሰደው እርምጃ በርካታ ቤቶች በመፍረስ ላይ እንዳሉ እንደሚታወቅ እና እርምጃው ዛሬም ድረስ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።

ፓርቲው እየተወሰደ ባለው እርምጃ በርካታ ቤቶች እንዲፈርሱ የተደረገ መሆኑንና በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በሚያሳዝን ሁኔታ ጎዳና ላይ እንዲወድቁ መደረጉን አመልክቷል።

እርምጃው ቤታቸው በፈረሰባቸው ዜጎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት እና እንግልት ከማሳደሩም ባሻገር፣ የማፍረስ ሂደቱ ከፍተኛ የህዝብ ቁጣ ቀስቅሷል ሲልም አክሏል።

ነእፓ ከተለያዩ ምንጮች አረጋግጫለሁ እንዳለው ቤት የማፍረስ እርምጃው ህጋዊ ፍቃድ የሌላችውን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ ህጋዊ ሰነድ ያላቸውን ዜጎች ጭምር ሰለባ ያደረገ መሆኑና ይህም ቤት የማፍረስ እርምጃው ዓላማ ግልጽነት የጎደለው እንዲሆን ማድረጉን ገልጿል።

" የማፍረስ እርምጃው ከዜጎች የመኖሪያ ቤት በተጨማሪ የእምነት ተቋማትን ኢላማ ያደረገ ነው " ያለው ነእፓ " በዚሁ ሳቢያ በርካታ #መስጂዶች መፍረሳቸው ተረጋግጧል፡ " ብሏል።

ይህ እርምጃ ምንም አይነት ህጋዊ መሰረት የሌለው፣ ተጠያቂነት የጎደለው ተግባር ከመሆኑ ባሻገር የእምነት ተቋማትን ክብር ያጎደፈ እና መንግስት ለምእመኑ ያለውን ንቀት የሚያሳይ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ሲል ገልጿል።

ነእፓ ፤ " አብዛኛው የሀገራች ህዝብ በአስከፊ ድህነት ውስጥ እየኖረ ባለበት፣ የእለት ጉርስ እና የአመት ልብስ ማግኘት ህልም በሆነበት፣ ዳቦ፣ ዘይት እና ስኳር ቅንጦት በሆነበት፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በጦርነት እና በግጭት ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው ባሉበት ሀገር ያለ በቂ ጥናት እና ዝግጅት የዜጎችን ቤት በጅምላ ማፍረስ በህግም ሆነ በሞራል ተቀባይነት የሌለውና ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው " ብሏል።

" በሀገራችን ተንሰራፍቶ በቆየው ብልሹ አስተዳደር ሳቢያ፣ እንዲሁም መንግስት የመኖሪያ ቤት እና ሌሎች መሰረታዊ አገልግሎቶችን ማቅረብ ባለመቻሉ፣ ዜጎች ራሳቸውን እና ቤተሰባቸውን ከጸሀይ ሀሩር እና ከክረምት ዝናብ የሚከልሉበት ጎጆ እንዲቀልሱ ተገደው ኖረዋል " ያለው ፓርቲው " በዚህ ምክንያት በአዲስ አበባም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች በመንግስት #ደካማ እና #በሙስና የተጨማለቀ አሰራር ምክንያት ዜጎች ለበርካታ አስርት አመታት ህጋዊ ይዞታ የሚያገኙበት ስርአት ሳይዘረጋላቸው ቆይቷል " ሲል ገልጿል።

ይህንን የመንግስት እንዝላልነት እና ብልሹ አሰራር ህግ እና ስርአት በጠበቀ መልኩ ማስተካከል ሲገባ፣ ዜጎች በሀብታቸው፣ በንብረታቸው እና በህይወታቸው ዋጋ እንዲከፍሉ ማድረግ ሰብአዊነት እና ኃላፊነት የጎደለው ታሪካዊ ስህተት ነው ብሏል።

" ቤት ማፍረሱ ሳያንስ፣ ዜጎች ለበርካታ አመታት ከኖሩበት ጎጆ በቂ ጊዜ እና አማራጭ የመኖሪያ ስፍራ እንዲያገኙ እድል ሳይሰጥ ' በጊዜ የለንም ' ፍጥነት ከመኖሪያ ደጃቸው እንዲነሱ የተደረገበት አሰራር ሂደቱን ይበልጥ አሳዛኝ፣ አሳሳቢ እና አጠያያቂ አድርጎታል " ያለው ነእፓ በአዲሱ የሸገር ከተማ በመካሄድ ላይ ያለው ቤት የማፍረስ ዘመቻ ፦
- በቂ ህጋዊ መሰረት የሌለው፣
- ከፍተኛ የአፈጻጸም ክፍተት ያለበት ፣
- የክልሉን ብሎም የሀገራችንን አሁናዊ የጸጥታ ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ድርብርብ ችግሮች እና ሀቆች በቅጡ ያላገናዘበ በመሆኑ #በአፋጣኝ_እንዲቆም አሳስቧል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia