" በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ነው " - የፍትህ ሚኒስቴር
ትላንት ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው የፓርላማ አባሉ ዶ/ር ጫላ ዋታ ዛሬ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቋል።
የቀድሞው የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጫላ ዋታ፤ #ዛሬ_ረቡዕ ረፋድ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፍትሕ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬትን ዋቢ በማድረግ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድረገፅ ዘግቧል።
ዶ/ር ጫላ በፌደራል ፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር የዋሉት #በሙስና_ወንጀል_ተጠርጥረው መሆኑን ዳይሬክቶሬቱ ለድረገፁ በሰጠው ቃል ገልጿል።
ማስታወሻ ፦ ዶ/ር ጫላ ዋታ የተጠረጠሩባቸው የሙስና ጉዳዮች ምንድናቸው ? እሳቸውስ ትላንት ለህ/ተ/ም/ቤት ምን አሉ ? መለስ ብለው በዚህ ያንብቡ :
https://publielectoral.lat/s/tikvahethiopia/77517@tikvahethiopia