TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኢህአዴግ የደርግ መሰል #የቤት_ልማት_ፖሊስ ተግባራዊ ሊያደርግ ነው ተብሏል። በሀዋሳ በተደረገው የድርጅቱ 11ኛ ጉባኤ ላይ በቀረበው ሰነድ መሰረት #የመጠለያ ችግርን ከመቅረፍ አንፃር መሬት እና ፋይናንስ በማቅረብ ዜጎች ቤታቸውን #በራሳቸው ገንብተው የቤት ባለቤት የሚሆኑበት አሰራር ተግባራዊ ይደረጋል። መንግስት ቤት በራሱ ገንብቶ ለህብረተሰቡ ተደራሽ አደርጋለሁ ሲል ቢቆይም ከፍላጎት አንፃር መሄድ ያልቻለ እና #በሙስና እና #ብልሹ አሰራር የተተበተበ መሆኑ ሲያስተቸው መቆየቱ አይዘነጋም። በአዲሱ እቅድ መሬት እና ብድር ተመቻችቶ ቤት ፈላጊዎች በራሳቸው ይገነባሉ። ይህ አሠራር ደርግ እስከ መውደቂያው እለት ሲተገብረው የነበረ እና በርካቶችን እንዳ አቅማቸው የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ያደረገበት ፖሊሲ እንደነበር ይታወሳል።

ምንጭ፦Muluken Yewondwossen,ENF
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE የትምህት ሚኒስቴር ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከመጪው ዓመት ጀምሮ ከመንግስት ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆኖ ራሱን የሚያስተዳድር ዩኒቨርሲቲ እንደሚሆን አስታወቀ፡፡ በኢትዮጵያ የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ነጻ ሆኖ የመመራት መብት የሚሰጥበት የውይይት መድረክ በዛሬው ዕለት ተካሄዷል። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ÷ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሰቲን ተከትሎ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ከሁለት እስከ አምስት…
#GondarUniversity

አንጋፋው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመቀጠል #በራሳቸው_ገቢ እንዲተዳደሩ ከተለዩ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ መሆኑን አሥራት አፀደወይን (ዶ/ር) የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ተናግረዋል።

ለዚህም ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደተግባር ለመግባት የሚያስችለውን ዝግጅት እያደረገ መሆኑን አሳውቀዋል።

ፕሬዜዳንቱ ፤ ዩኒቨርሲቲው የመጀመሪያ ዲግሪ መርሃ ግብሮችን በሂደት እየቀነሰ የሁለተኛ እና የሦሥተኛ ዲግሪ መርሃ ግብሮችን ለማስፋት እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የውጪ ሀገራት ተማሪዎችን ለመሳብ እየሰራ እንደሚገፅ የገለፁት አስራት አፀደወይን (ዶ/ር) በአሁኑ ወቅት 50 ዓለም አቀፍ ተማሪዎች እንዳሉት ገልፀዋል።

ዩኒቨርሲቲው አሁን ላይ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦሥተኛ ዲግሪ እንዲሁም በስፔሻሊቲ እና በሰብ ስፔሻሊቲ መርሃ ግብሮች ከ48 ሺህ በላይ ተማሪዎችን እያስተማረ ይገኛል።

Via @tikvahuniversity