TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#WANTED #ተፈላጊ

በምስራቅ ጎጃም ዞን በ ' ሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ' በቀራንዮ ንዑስ ከተማ ታህሳስ 18 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 አካባቢ የፍቅር ጥያቄ አቅርቦ አለመግባባት በመፈጠሩ ምክንያት ተጠርጣሪው አቶ ይኸነው ፈንታ ይሁኔ የተባለ ግለሰብ የፍቅር ጥያቄ ባቀረበላት ወጣት ፊት እና ሌሎች የሰውነት ክፍሏ ላይ አሲድ በመድፋት ከፍተኛ አካላዊ ጉዳት በማድረስ ከአካባቢው ተሰውሯል፡፡

የወረዳው ፖሊስም ወንጀሉ ከተፈፀመበት ሰዓት ጀምሮ ተጠረጣሪ ወንጀለኛውን ለመያዝ ክትትል እያደረገ የሚገኝ ቢሆንም አሁንም በቁጥጥር ሥር አልዋለም።

ስለሆነም ተጠረጣሪ ግልሰቡ ያለበትን አካባቢ ለፖሊስ ትብብርና ጥቆማ በመስጠት በህግ ቁጥጥር ሥር እንዲውል ህዝቡ እገዛ እንዲያደርግ ጥብቅ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

ስልክ ቁጥር ፡ 058 661 02 01

" ወንጀል ሠርቶ ከተጠያቂነት ማምለጥ አይቻልም "

( በምስራቅ ጎጃም ዞን የሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ፖሊሲ ጽህፈት ቤት )

#ሼር #Share

@tikvahethiopia
#Wanted #ይፈለጋሉ

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ አይተንፍስ እንደሻው ስለሺ እና ያቤል መንገሻ የተባሉ ግለሰቦችን (በፎቶ ከላይ ይታያሉ) በወንጀል እፈልጋቸዋለሁ ብሏል።

ፖሊስ እነዚህን 2 ግለሰቦች የሚፈልጋቸው #በከባድ_የማጭበርበር ወንጀል መሆኑን ገልጿል።

ግለሰቦቹን ያየ አልያም ያሉበትን የሚያውቅ ዘውትር በስራ ሰዓት ከ2:30 - 11:30 በ01115309047 / 01111711206 እና በማንኛውም ሰዓት በ0111119475 / 0111711012 በመደወል እንዲያሳውቀው የጠየቀው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ህብረተሰቡ የተለመደውን ትብብሩን እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
#በወንጀል_ይፈለጋሉ #Wanted

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከላይ በፎቶ የሚታዩትን ተጠርጣሪዎች በወንጀል እየፈለጋቸው ይገኛል።

የተጠርጣሪዎቹን አድራሻቸውን የሚያውቅ አልያም በአጋጣሚ የተመለከተ ማንኛውም ገለሰብ በስልክ ቁጥር ፦

👉 0115309139 ዘውትር (በስራ ሰዓት ከ2:30 - 11:30)

👉 በ0111119475 / 0111711012 በማንኛውም ሰዓት ደውሎ እንዲያሳውቅ ተጠይቋል።

ነፃ የስልክ መስመር 861 መጠቀምም ይቻላል።

ግለሰቦቹ በሞጆ፣ አንድ ወርቅ ቤት በመግባት ሲዘርፉ የሚታይ ሲሆን ከመካከላቸው የፌዴራል ፖሊስ ልብስ የለበሰ ይገኝበታል።

እነዚህ ተጠርጣሪዎች ወደ ወርቅ ቤቱ በመግባት በሰዓቱ ስራ ላይ የነበረችውን ግለሰብ በማዘናጋት ብዛት ያለው ለሽያጭ የቀረበ ንብረት ዘርፈው ሲወጡ በቤቱ የደህንነት ካሜራ አይን ውስጥ ገብተዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ፖሊስ ምርመራ ላይ ነው " - የአ/አ/ከ/እ/ጉ/ከ/ምክር ቤት የበድር መስጂድ ኢማም እና ኸጢብ ሸይኽ አብዱ ያሲንን የግድያ ሁኔታ በተመለከተ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በምርመራ ላይ መሆኑን የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ገልጿል። ወንጀል የፈፀመውን አካል በማፈላለግ ረገድ ፖሊስ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ማህበረሰቡ በንቃት ጉዳዩን እንዲከታተል እና…
#ይፈለጋል #Wanted

" ... ሟች ያሳድጉት የነበረው መሀመድ ሽኩር አበባው ፤ ሼህ አብዲ ያሲንን በመግደል ወንጀል ተጠርጥሮ ይፈለጋል " - ፖሊስ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፤ ሼህ አብዱ ያሲንን በመግደል የሚጠረጠረው መሀመድ ሽኩር አበባው የተባለ ግለሰብ መሆኑን ገልጿል።

ግለሰቡ #እጁን_እንዲሰጥም ፖሊስ አሳስቧል።

ፖሊስ ተጠርጣረው ያለበትን የሚያውቅ ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪውን አስተላልፏል።

የወንጀሉን ፈፃሚ በቁጥጥር ስር ለማዋል የክትትልና የምርመራ ቡድኖችን አዋቅሮ ክትትሉን አጠናክሮ መቀጠሉን የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ " የመኖሪያ አድራሻው ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ነዋሪ የነበረ ሟቹ ያሳድጉት የነበረው መሀመድ ሽኩር አበባው ሼህ አብዲ ያሲንን በመግደል ወንጀል ተጠርጥሮ ይፈለጋል። " ሲል አሳውቋል።

መሀመድ ሽኩር አበባው ያለበትን የሚያውቅ ሆነ ማንኛውም መረጃ ያለው በስልክ ቁጥር 011-1-11-01-11 ወይም በነፃ ስልክ ቁጥር 991 መረጃ በመስጠት እንዲተባበር ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

በወንጀል የተጠረጠረ ግለሠብን መደበቅ ሆነ እንዲያመልጥ መተባበር የህግ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ይፈለጋል #Wanted " ... ሟች ያሳድጉት የነበረው መሀመድ ሽኩር አበባው ፤ ሼህ አብዲ ያሲንን በመግደል ወንጀል ተጠርጥሮ ይፈለጋል " - ፖሊስ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፤ ሼህ አብዱ ያሲንን በመግደል የሚጠረጠረው መሀመድ ሽኩር አበባው የተባለ ግለሰብ መሆኑን ገልጿል። ግለሰቡ #እጁን_እንዲሰጥም ፖሊስ አሳስቧል። ፖሊስ ተጠርጣረው ያለበትን የሚያውቅ ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪውን አስተላልፏል።…
#ይፈለጋል #Wanted

ሼህ አብዱ ያሲንን በመግደል የሚጠረጠረው መሀመድ ሽኩር አበባው በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ ክትትሉን አጠናክሮ መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

አንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያዎች ተጠርጠሪው እንደተያዘ በማስመሰል የሚያሰራጩት መረጃ #ሀሰተኛ መሆኑን አስታውቋል።

በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተጠርጣሪው ሳይያዝ እንደ ተያዘ አድርጎ መረጃ ማሰራጨት ተገቢ እንዳልሆነ የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ መሀመድ ሽኩር አበባው ያለበትን የሚያውቅም ሆነ ማነኛውም መረጃ ያለው በስልክ ቁጥር 011-1-11-01-11 ወይም በነፃ ስልክ ቁጥር 991 መረጃ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia