TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ‼️

#ግምታዊ_ዋጋቸው 300 ሺህ ብር የሆኑ #የምግብ_ዘይት እና የተለያዩ #የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ። ዛሬ የካቲት 08 ቀን 2011 ዓ ም ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ የሰሌዳ ቁጥራቸው ኮድ 3- 37064 ኦሮ እና 02872 ሐረ የሆኑ ሚኒባስ እና አይሱዙ ጭነት ተሽከርካሪዎች የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹን በመያዝ እና መነሻቸውን ከጅግጅጋ አቅጣጫ በማድረግ ወደ ሐረር ከተማ ሊገቡ ሲሉ ጅግጅጋ እና ሐረር መካከል ቦምባስ በምትገኝ ቦታ ላይ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

በሚኒባስ ተሸከርካሪ ውስጥ በርካታ የምግብ ዘይት ሲያዙ በአይሱዙ የጭነት ተሸከርካሪ ውስጥ ደግሞ የተለያዩ የመኪና ጎማዎች፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች እና ልባሽ ጨርቆች ተይዘዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹም ለጊዜው #እንዳመለጡ ታውቋል፡፡ የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹን የፈዴራል ፖሊስ፣ የመከላከያ ሰራዊት እና የጉምሩክ ፈታሾች በጋራ በቁጥጥር ስር እንዳዋሉት ከገቢዎች ሚኒስቴር የተኘው መረጃ ያመለክታል።

ምንጭ፦ የገቢዎች ሚኒስቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia