TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ‼️

#ግምታዊ_ዋጋቸው 300 ሺህ ብር የሆኑ #የምግብ_ዘይት እና የተለያዩ #የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ። ዛሬ የካቲት 08 ቀን 2011 ዓ ም ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ የሰሌዳ ቁጥራቸው ኮድ 3- 37064 ኦሮ እና 02872 ሐረ የሆኑ ሚኒባስ እና አይሱዙ ጭነት ተሽከርካሪዎች የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹን በመያዝ እና መነሻቸውን ከጅግጅጋ አቅጣጫ በማድረግ ወደ ሐረር ከተማ ሊገቡ ሲሉ ጅግጅጋ እና ሐረር መካከል ቦምባስ በምትገኝ ቦታ ላይ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

በሚኒባስ ተሸከርካሪ ውስጥ በርካታ የምግብ ዘይት ሲያዙ በአይሱዙ የጭነት ተሸከርካሪ ውስጥ ደግሞ የተለያዩ የመኪና ጎማዎች፣ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች እና ልባሽ ጨርቆች ተይዘዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹም ለጊዜው #እንዳመለጡ ታውቋል፡፡ የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹን የፈዴራል ፖሊስ፣ የመከላከያ ሰራዊት እና የጉምሩክ ፈታሾች በጋራ በቁጥጥር ስር እንዳዋሉት ከገቢዎች ሚኒስቴር የተኘው መረጃ ያመለክታል።

ምንጭ፦ የገቢዎች ሚኒስቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
📩 ውድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች የምግብ ዘይት ዋጋ ከሳምንታት በፊት ከነበረበት ምን አይነት ለውጥ እየተመለከታችሁ ነው ? አቅርቦቱስ እንደልብ አለ ? ከተማችሁን በመግለፅ በ @tikvahethiopiaBOT መልዕክታችሁን አስቀምጡልን። @tikvahethiopia
#TikvahFamily🍛

" በሚዲያው ላይ የሚነገረው እና በመሬት ላይ ያለው ሁኔታ አይገናኝም " - የቲክቫህ አባላት

ከዘይት ዋጋ ጋር በተያያዘ ከሳምንታት በፊት ከነበረው ምን የተቀየረ ነገር አለ ? አቅርቦትስ እንደልብ እየተገኘ ነው ? የሚል ጥያቄ ለቤተሰቦቻችን ቀርቦ ነበር።

በሁሉም አቅጣጫዎች የሚገኙ የቤተሰብ አባላቶች መልዕክታቸውን በመላክ ሁኔታው አስረድተዋል። ያለውን ችግር እና ምሬት ገልፀዋል፤ መፍትሄ ይፈለግ ዘንድም ጠይቀዋል።

በአንዳንድ ቦታዎች አቅርቦቶች ቢኖርም በዋጋው ላይ አንዳች ግን ለውጥ እንዳላዩ የገለፁት አባላቶቻችን በአንዳንድ ቦታ ደግሞ አቅርቦት ማነስ ምክንያት በሚባለው ዋጋ ለመግዛት እራሱ ማግኘት እንዳልተቻለ ገልፀዋል።

በተለይ ከውጭ የሚገባው የፈሳሽ ዘይት ዋጋ አምስት ሊትሩ አሁንም ከ880 - 1000 ብር ድረስ እየተሸጠ ነው ፤ እንዲህ ያሉ መለማመዶች ተገቢ እንዳልሆነ አንስተዋል።

ዋጋውን እንዲህ በየቀኑ እያለማመዱን በዚሁ ተሰቅሎ እንዳይቀር ያሰጋናልም ብለዋል።

መወደዱን የተቀበልን በድህነት ውስጥ ያለን ዜጎች መከራ ላይ ነን፤ ለመኖርም እየሰጋን ነው ሲሉ ያሉበትን የከፋ ሁኔታ አስረድተዋል።

የነዋሪው ገቢ አይጨምርም ዘይት ሆነ ሌላው ሁሌም ዋጋው እንደናረ ነው ፤ ዓለም አቀፍ ሁኔታው ምን ያህል ከባድ እንደሆነ ለመረዳት ባያስቸግርም እዚሁ ሀገር ውስጥ ያለው የከፋ አሻጥር፣ ሙስና፣ የአስተዳደር ጉድለት ችግሩን እያባባሰው ነው ብለዋል።

ከተለያዩ ከተሞች በ @tikvahethiopiaBot የተላኩ መልዕክቶችን በጥቂቱ ከታች ያንብቧቸው።

(በተጨማሪ ቤተሰቦቻችን በብዙ ሺዎች የሚቆጠረውን የናተን አስተያየት በአንድ ለመሰብሰብ የሚከብድ ስለሆነ ከታች ባለው አስተያየት መስጫ ላይ ተጨማሪ ማስቀመጥ ትችላላችሁ)

NB. ውድ ቤተሰቦቻችን እንደሁል ጊዜው ማንኛውም የጥላቻ ንግግር ሆነ ሃሳብ፣ ስድብ፣ ሰውን ማንቋሸሽና ከጉዳዩ ጋር የማይገናኝ መልዕክት ማስፈር በቀጥታ እስከመጨረሻው ከቤተሰባችን ጋር እንደሚያለያይ ይታወቅ።

https://telegra.ph/Tikvah-Family-04-05
#Update

ኢንዶኔዥያ በሀገር ውስጥ #የምግብ_ዘይት አቅርቦት ላይ መሻሻሎች መታየቱን ተከትሎ እ.ኤ.አ. ከሰኞ ግንቦት 23 /2022 ጀምሮ የፓልም ዘይት ወደ ውጭ እንዳይላክ የተጣለው እገዳ እንደሚነሳ ፕሬዝዳንት ጆኮ ዊዶዶ በዛሬው ዕለት ተናግረዋል።

@tikvahethiopia