TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የሚሊዮኖች የሳቅ ምንጭ የነበረው ኮሜዲየን ወንደሰን ብርሃኑ (ዶክሌ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

በኢትዮጵያ ውስጥ በኮሜዲ ዘርፍ ከታዩ እጅግ ተወዳጅ እና ምርጥ ኮሜዲያኖች እንዱ እንደሆነ የሚነገርለት ኮሜዲያን ወንድወሰን ብርሃኑ ( #ዶክሌ ) በ57 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየቱ ተሰምቷል።

ኮሜዲያኑ ላለፉት ዓመታት ኑሮውን በአሜሪካ ሀገር አድርጎ የነበረ ሲሆን ባጋጠመው የልብ ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 11 ቀን 2014 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

የኮሜዲያን ወንደሰን (ዶክሌ) አጫጭር የኮሜዲ ስራዎች እጅግ በርካታ ሲሆኑ በተለያዩ ረጃጅም ፊልሞች ላይም በትወና ሰርቷል ፤ ላለፉት ሁለት አስርት አመታት በዚሁ ሞያ ውስጥ ቆይቷል።

ኮሜዲያኑ ባለትዳርና የ5 ልጆች አባት ነበር።

@tikvahethiopia