የሚሊዮኖች የሳቅ ምንጭ የነበረው ኮሜዲየን ወንደሰን ብርሃኑ (ዶክሌ) ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

በኢትዮጵያ ውስጥ በኮሜዲ ዘርፍ ከታዩ እጅግ ተወዳጅ እና ምርጥ ኮሜዲያኖች እንዱ እንደሆነ የሚነገርለት ኮሜዲያን ወንድወሰን ብርሃኑ ( #ዶክሌ ) በ57 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየቱ ተሰምቷል።

ኮሜዲያኑ ላለፉት ዓመታት ኑሮውን በአሜሪካ ሀገር አድርጎ የነበረ ሲሆን ባጋጠመው የልብ ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 11 ቀን 2014 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

የኮሜዲያን ወንደሰን (ዶክሌ) አጫጭር የኮሜዲ ስራዎች እጅግ በርካታ ሲሆኑ በተለያዩ ረጃጅም ፊልሞች ላይም በትወና ሰርቷል ፤ ላለፉት ሁለት አስርት አመታት በዚሁ ሞያ ውስጥ ቆይቷል።

ኮሜዲያኑ ባለትዳርና የ5 ልጆች አባት ነበር።

@tikvahethiopia