TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የከፋ ዞን ምክር ቤት‼️

የካፋ ዞን ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ #ቦንጋ ላይ የተገነባው ብሔራዊ የቡና ሙዚዬም ሥራ እንዲጀምር ወሰነ።

የካፋ ዞን #የክልልነት ጥያቄንም በምክር ቤቱ አባላት ጸድቋል።

የዞኑ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ አቶ ግርማ ወልደ ሚካዔል ለኢዜአ እንደገለጹት ጉባዔው በዛሬው ወሎ በሁለት አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አስተሏልፏል ።

ጉባዔው ውሳኔ ካሳለፈባቸው አጀንዳዎች አንዱ በዞኑ ቦንጋ ከተማ ተገንብቶ ለአመታት ሥራ ያልጀመረው ሙዚዬም ወደ ሥራ እንዲገባ ወስኗል።

“ከምሁራን የተውጣጣ ኮሚቴ ተቋቁሞ ከሚመለከተው አካል ጋር በመነጋገር ሙዚዬሙ ወደ ሥራ እንዲገባ ውሳኔ ተላልፏል” ብለዋል ።

የካፋ ሕዝብ የክልልነት ጥያቄ ለምክር ቤቱ ቀርቦ በአባላቱ ውይይት ከተደረገበት በኋላ በሙሉ ድምጽ መፅደቁን ምክትል አፈ ጉባዔው ተናግረዋል።

ጉባኤው ነገ የዞኑን የ2010 በጀት ዓመት የአስፈጻሚ አካላት የሥራ ክንውን በመገምገምና በቀጣይ ዕቅድ ላይ በመወያየት ውሳኔ እንደሚያሳልፍ አመላክተዋል ።

እንደ ምክትል አፈ ጉባኤው ገለጻ በተለያዩ ምክንያቶች ያልጸደቀውን የዞኑን የ2011 በጀትና የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ሹመትም እንደሚፀድቅ ይጠበቃል።

ምንጭ፦ ena
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደኢህዴን‼️

በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ባሉ አንዳንድ የዞን ም/ቤቶች የሚነሱ #የክልልነት_ጥያቄዎች ከደኢህዴን ጉባኤ አቅጣጫ ውጭ መሆናቸውን የድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡

ማዕከላዊ ኮሚቴው ይህን ያስታወቀው በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ መሆኑን የማዕከላዊ ኮሚቴው ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡

ኃላፊው እንዳሉት ማዕከላዊ ኮሚቴው የህብረተሰቡን ጥያቄዎች ለመመለስ በ10ኛው የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባኤ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን አፈፃፀም ሂደት ገምግሟል፡፡

አስተዳደራዊ አደረጃጀትን በተመለከተ ዝርዝር ጥናት እየተደረገ መሆኑን የጠቀሰው ማዕከላዊ ኮሚቴው ጥናቱ ሲጠናቀቅ በጉባኤው የፀደቁ አዳዲስ የመዋቅር አደረጃጀቶች በክልሉ ም/ቤት ህጋዊ ማዕቀፍ ኖሯቸው እንደሚቋቋሙ ገልጿል፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በክልሉ እየተበራከቱ የመጡትን የክልላዊ አደረጃጀት ጥያቄዎች በተመለከተም ጥልቅ ጥናት የሚያደርግ ከባለሙያዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጣ ቡድን መቋቋሙ ተገልጿል፡፡

ጥናቱን ተከትሎም ተገቢው ምላሽ እንደሚሰጥና ከዚህ ውጭ በዞን ም/ቤቶችና በተለያየ መልኩ የሚነሱ ጥያቄዎች ከድርጅቱ ጉባኤ አቅጣጫ ውጭ መሆናቸውን ማዕከላዊ ኮሚቴው አስታውቋል፡፡

ተቋማትን በመዝጋትና የዜጎችን ነፃ እንቅስቃሴ በመገደብ ሃሳብን በኃይል ለመጫን የሚደረጉ ተግባራት ተቀባይነት የላቸውም ያለው ኮሚቴው የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ግልፅ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡

ማዕከላዊ ኮሚቴው የኅብረተሰቡን ጥያቄዎች ተከትሎ በተከሰቱ ግጭቶች በደረሰው የህይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘንም መግለፁን የማዕከላዊ ኮሚቴው ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ተናግረዋል፡፡

ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert

"ለሲዳማ የክልልነት ጥያቄ የምርጫ ቦርድን ስራ በትእግስት መጠባበቅ ይገባል'" አቶ ቃሬ ጫዌቻ
.
.
#የክልልነት ጥያቄው በህገ-መንግስቱ መሰረት ምላሽ እንዲያገኝ የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ስራ በመጀመሩ መላው የሲዳማ ብሔር ተወላጆች በትዕግስት እንዲጠባበቁ የሲዳማ ዞን አስተዳዳሪ አስታወቁ።

ዋና አስተዳዳሪው አቶ ቃሬ ጫዊቻ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በሲዳማ የክልልነት ጥያቄ ዙሪያ ህዝበ ውሳኔ ለማድረግ እንዲቻል ቅድመ-ዝግጅቱን ጀምሯል።

ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ትናንት በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው ህዝበ ውሳኔውን ለማድረግ እንዲያስችል በደቡብ ክልልና በሲዳማ ዞን መከናወን ያለባቸውን ተግባራት በመለየት ማሳወቁንና እስከ ሐምሌ 19 ድረስ ዝርዝሩን በጽሁፍ ማቅረብ እንዲቻል የጊዜ ገደብ መስጠቱን አስታውቀዋል።

የሲዳማ ዞን አስተዳደር ከክልሉ መንግስትና ከደኢህዴን ጋር በመሆን በጥያቄው ዙሪያ በጋራ እየሰሩ እንደሚገኙና ምርጫ ቦርድ በአምስት ወራት ጊዜ ውስጥ ህዝበ ውሳኔ እንደሚደረግ በመግለጹ መላው የሲዳማ ተወላጆችና ወጣቶች ጉዳዩን በትዕግስት እንዲጠብቁ አሳስበዋል።

ቦርዱ በህዝበ ውሳኔ ማደራጀት ዙሪያ ከሲዳማ ዞንና ከክልሉ መንግስት ጋር በተለያዩ ጊዜያት መወያየቱን ያስታወሱት አቶ ቃሬ ህዝበ ውሳኔውን አምስት ወር ባልሞላ ጊዜ አደራጅቶ ለጥያቄው አፋጣኝ ምላሽ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።

Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Wolkite

ዛሬ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ወደ ደቡብ ክልል፣ ጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ በማቅናት ከህብረተሰቡ ጋር ውይይት ስለማድረጋቸው አሳውቀዋል።

ውይይቱን ተከትሎ ፤ " የጉራጌ ሕዝብ የሚነሡ ችግሮችን ገንቢ በሆነ ተሳትፎና ውይይት የሚፈታ ሰላም ወዳድ ሕዝብ ነው። " ያሉ ሲሆን " በዛሬው ውይይቶች ያነሧቸውን ሥጋቶች እና ተስፋዎች በመስማቴ ደስተኛ ነኝ " ብለዋል።

በየደረጃው ሊፈቱ የሚችሉ ችግሮችን ለመፍታት እንሠራለን ሲሉ ገልጸዋል።

ዛሬ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ወደ ወልቂጤ ከተጓዙ ባለስልጣናት መካከል የኦሮሚያ ክልል ፕሬዜዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ፣ የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሙስጠፌ መሀመድ፣ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ይገኙበታል።

ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የወልቂጤ ጉዞ ጋር በተገናኘ ዛሬ የማህበራዊ መገናኛዎች ትኩረት ሆኖ የነበረው በከተማው የነበረው የእንቅስቃሴ / የስራ ማቆም አድማ እንዲሁም ደግሞ የሚጠበቀውን ያህል የከተማው ህዝብ በነቂስ ወጥቶ አቀባበል አለማድረጉ ነበር።

በወልቂጤ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት የጠቅላይ ሚኒስትሩን መምጣት ተከትሎ ከተማዋ እንቅስቃሴ ተቀዛቅዞ እንደነበር አመልክተዋል ፤ ይህ የሆነውን ህዝቡ እየጠየቀው ካለው #የክልልነት_ጥያቄ ጋር በተያያዘ እንደሆነ አመልክተዋል።

ምንም እንኳን የዞን ምክር ቤት በክልል መደራጀትን ውሳኔ አሳልፎ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ቢያስገባም እንዲሁም የክላስተር አደረጃጀትን እንደማይደግፍ በአብላጫ ድምፅ ቢወስንም የክልልነት ጥያቄው ግን ምላሽ እንዳላገኘ ይህ ደግሞ የህዝቡን ህገመንግስታዊ መብት የሚጥስ እንደሆነ አስረድተዋል።

" ህዝቡ መብቱን ነው የጠየቀው ፤ ለዚህ ደግሞ ኃይል ፣ እስር ፣ ማሳደድ፣ ማፈን መልስ አይሆንም መንግሥት አሁንም የያዘውን ግትር አቋሙን መልሶ ማጤን ይገባዋል " ሲሉ አስረድተዋል።

በዞኑ ከክልልነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ አመራሮችን ጨምሮ በርካቶች ታስረው እንደነበር አይዘነጋም። በተጨማሪ ዞኑ ላይ የአመራር ለውጦችም ተደርገዋል።

የደቡብ ክልልን ለሁለት ለመክፈል በተላለፈው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ በወላይታ (እንዲደገም) ፣ ጋሞ፣ ጎፋ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዴኦ፣ ኮንሶ ዞኖች፣ ደራሼ፣ አማሮ፣ ቡርጂ፣ አሌ፣ ባስኬቶ ልዩ ወረዳዎች ላይ በቅርቡ ህዝበ ውሳኔ መደረጉ ይታወቃል።

አንድ ላይ እንዲቀጥለው የተባሉት ሀዲያ፣ ሀላባ፣ ከምባታ ጠምባሮ፣ ስልጤ፣ ጉራጌ ሲሆኑ ከነዚህም መካከል የጉራጌ ዞን የክላስተር የአደረጃጀትን ውሳኔ ቀደም ብሎ ያልተቀበለው / በምክር ቤቱም በአብላጫ ድምፅ ውድቅ ያደረገው ዞን እንደነበር አይዘነጋም።

Photo : PM OFFICE & TIKVAH WOLKITE FAMILY

@tikvahethiopia