TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የከፋ ዞን ምክር ቤት‼️

የካፋ ዞን ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ #ቦንጋ ላይ የተገነባው ብሔራዊ የቡና ሙዚዬም ሥራ እንዲጀምር ወሰነ።

የካፋ ዞን #የክልልነት ጥያቄንም በምክር ቤቱ አባላት ጸድቋል።

የዞኑ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ አቶ ግርማ ወልደ ሚካዔል ለኢዜአ እንደገለጹት ጉባዔው በዛሬው ወሎ በሁለት አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አስተሏልፏል ።

ጉባዔው ውሳኔ ካሳለፈባቸው አጀንዳዎች አንዱ በዞኑ ቦንጋ ከተማ ተገንብቶ ለአመታት ሥራ ያልጀመረው ሙዚዬም ወደ ሥራ እንዲገባ ወስኗል።

“ከምሁራን የተውጣጣ ኮሚቴ ተቋቁሞ ከሚመለከተው አካል ጋር በመነጋገር ሙዚዬሙ ወደ ሥራ እንዲገባ ውሳኔ ተላልፏል” ብለዋል ።

የካፋ ሕዝብ የክልልነት ጥያቄ ለምክር ቤቱ ቀርቦ በአባላቱ ውይይት ከተደረገበት በኋላ በሙሉ ድምጽ መፅደቁን ምክትል አፈ ጉባዔው ተናግረዋል።

ጉባኤው ነገ የዞኑን የ2010 በጀት ዓመት የአስፈጻሚ አካላት የሥራ ክንውን በመገምገምና በቀጣይ ዕቅድ ላይ በመወያየት ውሳኔ እንደሚያሳልፍ አመላክተዋል ።

እንደ ምክትል አፈ ጉባኤው ገለጻ በተለያዩ ምክንያቶች ያልጸደቀውን የዞኑን የ2011 በጀትና የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ሹመትም እንደሚፀድቅ ይጠበቃል።

ምንጭ፦ ena
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ቦንጋ

"በአሁን ሰዓት በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ያስተላለፈውን መግለጫ በመቃወም፤ መግለጫው እኛን አይወክለንም በማለት እንዲሁም ካፋ ዞን ራሱ በራሱን ያስተዳድር የክልልነት ጥያውቄው ይመለስለት "ክልላችን ካፋ ነው" በሚል ሰላማዊ ሰልፍ በመደረግ ላይ ይገኛል። የሰልፉ ተካፋዮች ከተለያዩ ወረዳዎች የተውጣጡ ናቸው።"

Via #SAMI

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ቦንጋ

•ሀገራዊ ለውጡ ይቅደም ብለን እንጂ ጥያቄያችን በበቂ ምክንያት ነው!!

•ከእንግዲህ ለግማሽ ቀን ስብሰባ ሁለት ቀን እንጓዝም!!

•የካፋ ህዝብ ክልል የመሆን ጥያቅም ፍትሃዊ ምላሽ እንጂ ድጋሚ ጥያት አያሻውም!!

•ክልላችን ካፋ ነው!!

•የካፋ ህዝብ ራሱን በራሱ የማስተዳደር ታሪካዊ ልምድና አቅም አለው!!

በካፋ ዞን ቦንጋ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ሰላማዊ ሰልፍ አሁንም እንደቀጠለ ይገኛል። ከተለያዩ ወረዳዎችም በርካታ ሰዎች ወደ ቦንጋ እየገቡ እንደሆነ ለማውቅ ተችሏል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን እያስመረቁ ነው።

#ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ 6 ሺህ 574 ተማሪዎችን ዛሬ እያስመረቀ ይገኛል፡፡

በ87 የመጀመሪያ እንዲሁም በ67 የድህረ ምረቃ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች ነው የሚያስመርቀው፡፡

በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ የውኃ መስኖ እና ኢነርጅ ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ተገኝተዋል፡፡

#ደብረታቦር_ዩኒቨርሲቲ

የደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ በተለያየ የትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎቹን እያስመረቀ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው ለስምንተኛው ዙር ነው ተማሪዎቹን እያስመረቀ የሚገኘው።

#ቦንጋ_ዩኒቨርሲቲ

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ 2ኛ Batch ተማሪዎች በዛሬው ዕለት እያስመረቀ ይገኛል።

#ደብረብርሃን_ዩኒቨርሲቲ

የደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በ13ኛ ዙር በተለያዩ መርሃ ግብሮች ያስተማራቸውን በ2ኛ ዲግሪ 231 ተማሪዎችን እና በ3ኛ ዲግሪ አንድ ተማሪ እያስመረቀ ነው።

#ኮተቤ_ሜትርፓሊታን_ዩኒቨርሲቲ

የኮተቤ ሜትርፖሊታን በተለያየ የትምህርት ክፍሎች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመርቋል።

ዩንቨርሲቲው በዛሬው እለት ያስመረቃቸው በመጀመሪያና ሁለተኛ ድግሪ ወንድ 448 ሴት 135 በድምሩ 583 ተማሪዎች ናቸው።

#ቅድስተ_ማርያም_ዩኒቨርሲቲ

የቅድስተ ማርያም ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በድህረ ምረቃ ያሰለጠናቸውን 636 ተማሪዎችን በኦሮሞ ባህል ማዕከል አስመርቋል።

አጠቃላይ ከተመረቁት ውስጥ 322 ወንዶች 314 ደግሞ ሴቶች ናቸው።

#ሀራምቤ_ዩኒቨርሲቲ

ሀራምቤ ዩኒቨርሲቲ በተለያየ ትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 3683 ተማሪዎችን እያስመረቀ ነዉ።

ዩኒቨርሲቲው ለ18ኛ ዙር ነው ተማሪዎችን እስመረቀ የሚገኘው።

ምንጭ፦ ኢፕድ፣ ዋልታ፣ አሚኮ፣ የዩኒቨርሲቲዎች ገፅ

@tikvahuniversity
#ቦንጋ

ኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ በቡና ሳይንስ ትምህርት መስክ የተማሩ ተማሪዎች ሊመረቁ ነው።

የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፤ በ2015 የትምህርት ዘመን መጨረሻ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ 37 ተማሪዎችን በ " ቡና ሳይንስ " የትምህርት መስክ ያስተማራቸውን ተማሪዎች እንደሚያስመርቅ አሳውቋል።

ዩኒቨርሲቲው የቡና ምርት ኢትዮጵያ ትልቁ የውጭ ምንዛሬ የምታገኝበት ሸቀጥ በመሆኑ በ2015 ዓ.ም መጨረሻ 37 ተማሪዎችን በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በቡና ሳይንስ የትምህርት መስክ ይመረቃሉ ብሏል።

ኢትዮጵያ ቡናን ለዓለም ያበረከተች ሀገር ብትሆንም እስካሁን ድረስ የቡና ትምህርት መስክ ብቁ ባለሙያዎችን ማፍራት አዳጋች ሆኖ ነበር ያለው ተቋሙ የዩኒቨርሲቲው ሴኔት የቡና ሳይንስ ትምህርት ክፍል እራሱን ችሎ በ2012 ዓ.ም እንዲከፈት ማድረጉን አስታውሷል ።

በቡና ምርት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመመርመር ከዘርፉ ተጠቃሚ ለመሆን ቡናን በትምህርትና ምርምር አስደግፎ ለመምራት ዩኒቨርሲቲው በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ የቡና ሳይንስና ቴክኖሎጂ ትምህርት ክፍል በማቋቋም ነው ተማሪዎችን እያስተማረ የሚገኘው።

በሚቀጥለው ዓመት በሁለተኛ ዲግሪ በቡና ሳይንስ ተማሪዎች የሚመረቁ ሲሆን፤ ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ ጊዜትም የቡና ሳይንስ ትምህርት መስክን በዶክትሬት ዲግሪ ደረጃ ማስተማር እንደሚጀምር ዶክተር ጴጥሮስ ጠቁመዋል፡፡

ዩኒቨርሲቲው ካለው 200 ሄክታር መሬት ውስጥ በ150 ሄክታሩ ላይ የግብርና ምርቶችን እያከናወነ መሆኑን ገልጿል።

#ኢፕድ

@tikvahethiopia