TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ለነቀምት ነዋሪዎች‼️

ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል #የተፈናቀሉ ወገኖቻችን በ03፣ 04 እና 07 ቀበሌ፤ በነቀምት የመምህራን ኮሌጅ፣ ዳንዲ ቦሩ ኮሌጅ እንዲሁም በነቀምት ከተማ አስተዳደር ግቢ ውስጥ ይገኛሉ። እነኚህ ወገኖቻችን ምግብ እና መኝታ ያስፈልጋቸዋል። የነቀምት ነዋሪዎች እና #ቄሮዎች በቻላችሁት አቅም ድጋፍ እንድታደርጉላቸው ጥሪያችንን እናቀርባለን።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለነቀምት ነዋሪዎች‼️

ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል #የተፈናቀሉ ወገኖቻችን በ03፣ 04 እና 07 ቀበሌ፤ በነቀምት የመምህራን ኮሌጅ፣ ዳንዲ ቦሩ ኮሌጅ፣ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም በነቀምት ከተማ አስተዳደር ግቢ ውስጥ ይገኛሉ። እነኚህ ወገኖቻችን ምግብ እና መኝታ ያስፈልጋቸዋል። የነቀምት ነዋሪዎች እና #ቄሮዎች በቻላችሁት አቅም ድጋፍ እንድታደርጉላቸው ጥሪያችንን እናቀርባለን።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስቸኳይ~ነቀምት‼️

ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል #የተፈናቀሉ ወገኖቻችን በ03፣ 04 እና 07 ቀበሌ፤ በነቀምት የመምህራን ማሰልጠኛ፣ ዳንዲ ቦሩ ኮሌጅ፣ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም በነቀምት ከተማ አስተዳደር ግቢ ውስጥ ይገኛሉ። እነኚህ ወገኖቻችን ድጋፍ እና እገዛ ያስፈልጋቸዋል። ሁላችንም ከጎናቸው እንሁን!

#ሼር #SHARE
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስቸኳይ~ነቀምት‼️

ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል #የተፈናቀሉ ወገኖቻችን በ03፣ 04 እና 07 ቀበሌ፤ በነቀምት የመምህራን ማሰልጠኛ፣ ዳንዲ ቦሩ ኮሌጅ፣ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም በነቀምት ከተማ አስተዳደር ግቢ ውስጥ ይገኛሉ። እነኚህ ወገኖቻችን ድጋፍ እና እገዛ ያስፈልጋቸዋል። ሁላችንም ከጎናቸው እንሁን!

#ሼር #SHARE
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለተፈናቀሉ ዜጎችን ለመርዳት የባንክ ሂሳብ⬇️

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝና ከምስራቅ ወለጋ ዞን አጎራባች ወረዳዎች #የተፈናቀሉ ዜጎችን ለመርዳት የባንክ ሂሳብ ተከፈተ፡፡

ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ካማሺ ዞን እና በምስራቅ ወለጋ ዞን ስር በሚገኙ አጎራባች ወረዳዎች ውስጥ የፀጥታ ችግር መፈጠሩ ይታወሳል፡፡

በዚህም ምክንያት ከ20 በላይ ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉና ከ70 ሺ በላይ ዜጎች ከንብረትና ቄያቸው መፈናቀላቸው ይነገራል፡፡

እነዚህን የተፈናቀሉ ዜጎች ለመርዳት የባንክ ሂሳብ መከፈቱን ኦሮሚያ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ በድረ ገፁ አስፍሯል፡፡

ድጋፍ ለማድረግም በኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ 937719፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000259030138፣ በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ 1000072131111 መጠቀም እንደሚቻል ተነግሯል፡፡

ከአራት ቀናት በላይ በእግራቸው በመጓዝ ነቀምቴ ከተማ የገቡት ተፈናቃዮች በአሁኑ ሰዓት በመምህራን፣ በቴክኒክና ሙያ፣ በነርሲንግ ኮሌጆችና በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ተጠልለዋል፡፡

#የነቀምቴ ከተማ ነዋሪዎች የምግብና አልባሳት #ድጋፍ እያደረጉላቸው እንደሆነም ተነግሯል፡፡

ምንጭ፦ ሸገር FM 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስቸኳይ መረጃ‼️

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝና ከምስራቅ ወለጋ ዞን አጎራባች ወረዳዎች #የተፈናቀሉ ዜጎችን #በገንዘብ ለመርዳት የምትፈልጉ፦

በኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ
937719

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000259030138

በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ
1000072131111

#ሼር

ምንጭ፦ ኦሮሚያ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስቸኳይ መረጃ‼️

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝና ከምስራቅ ወለጋ ዞን አጎራባች ወረዳዎች #የተፈናቀሉ ዜጎችን #በገንዘብ ለመርዳት የምትፈልጉ፦

በኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ
937719

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000259030138

በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ
1000072131111

#ሼር

ምንጭ፦ ኦሮሚያ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስቸኳይ መረጃ‼️

ከቤኒሻንጉል ጉሙዝና ከምስራቅ ወለጋ ዞን አጎራባች ወረዳዎች #የተፈናቀሉ ዜጎችን #በገንዘብ ለመርዳት የምትፈልጉ፦

በኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ
937719

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000259030138

በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ
1000072131111

#ሼር

ምንጭ፦ ኦሮሚያ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አስቸኳይ መረጃ‼️

ከቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል #የተፈናቀሉ ወገኖቻችን በ03፣ 04 እና 07 ቀበሌ፤ በነቀምት የመምህራን ማሰልጠኛ፣ ዳንዲ ቦሩ ኮሌጅ፣ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም በነቀምት ከተማ አስተዳደር ግቢ ውስጥ ይገኛሉ። እነኚህ ወገኖቻችን ድጋፍ እና እገዛ ያስፈልጋቸዋል። ሁላችንም ከጎናቸው እንሁን!

#ሼር #SHARE
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን⬇️

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከማሺ ዞን እና በደቡብ ክልል ሸካና ከፋ ዞኖች የተከሰቱት #ግጭቶች ከቁጥጥር ውጪ ከመሆናቸው አስቀድሞ መንግስት አስፈላጊውን #እርምጃ እንዲወስድ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጠየቀ።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር አዲሱ ገብረእግዚአብሄር #ከሃዋሳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፥ በእነዚህ ቦታዎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቱ እና ግጭቱ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አስታውቀዋል።

በተለይም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ካማሺ ዞን በሚገኙ አምስት ወረዳዎች ላይ ያለው ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ነው የገለፁት።

በእነዚህ ሶስት ዞኖች የዜጎች የመንቀሳቀስ እና ንብረት የማፍራት #መብት መገደቡን አስታውቀዋል።

ኮሚሽኑ ወደ ሶስቱም አካባቢዎች መርማሪዎችን ቢልክም ምርመራ እንዲያደርጉ የሚያስችል ሁኔታ አለመኖሩን እና መንቀሳቀስ አለመቻላቸውን ነው የተናገሩት።

የፀጥታ አካላትም ግጭቶቹን ለማስቆም ተገቢውን እርምጃ እየወሰዱ አለመሆናቸውን ከአካባቢዎቹ መርማሪዎች ለኮሚሽኑ በስልክ ያደረሱት መረጃ እንደሚጠቁምም ገልፀዋል።

አሁን ላይ በይፋ በግጭቶቹ #የሞቱ እና #የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥርንም በዚህ ምክንያት በአግባቡ ማጣራት አለመቻሉን በማንሳት ይህም የችግሩን ስፋት እንደሚያሳይ ተናግረዋል።

በመሆኑም የሀገር መከላከያ ሰራዊት ችግሩ በተፈጠረባቸው እነዚህ አካባቢዎች ገብቶ የማረጋጋት ፣ ህግ እና ስርዓትን እንዲሁም የዜጎችን መብት የማስከበር ስራ እንዲያከናውን ነው የጠየቁት።

እስካሁን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሽ ዞን ግጭት ካለባቸው አምስት ወረዳዎች መካከል በሁለቱ የሀገር መከላከያ ሰራዊት በመግባቱ የተሻለ ሁኔታ እየታየ መሆኑን ዶክተር አዲሱ አስታውቀዋል።

በእነዚህ መከላከያ በገባባቸው ቦታዎችም ኮሚሽኑ ከነገ ጀምሮ ምርመራ እንደሚጀመር ነው ያስታወቁት። ምርመራውንም በኃላፊነት መንፈስ ያከናውናል ብለዋል።

ዶክተር አዲሱ በመግለጫቸው በተለያዩ አካባቢዎች እየተስተዋሉ ያሉ ችግሮችን መነሻ በማድረግ ችግሮቹ ከመከሰታቸው በፊት አስቀድሞ ለመከላከልና ሲከሰቱም በዘላቂነት ችግሮቹን ለመፍታት የሚያስችል ጥናት ኮሚሽኑ አድርጎ ለመንግስት ማቅረቡን አስታውቀዋል።

ምንጭ ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአማራ ክልል መንግስት‼️

የአማራ ክልል መንግሥት በማዕከላዊና ምዕራብ ጎንደር ዞኖች #የተፈናቀሉ ዜጎችን በሁለት ወራት ውስጥ ወደ ቀያቸው ለመመለሥ እየሠራ መሆኑን የክልሉ መንግሥት የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ #አሰማኸኝ_አስረስ ተናገሩ፡፡

አቶ አሰማኸኝ እንዳሉት በክልሉ ያሉት አጠቃላይ ተፈናቃዮች ቁጥር 90 ሺህ 736 ነው፡፡ ከዚህ ውስጥ 60 ከመቶ አካባቢው ተፈናቃዮች ደግሞ ከማዕከላዊ እና ምዕራብ ጎንደር የተፈናቀሉ ናቸው፡፡

ተፈናቃዮችን በሁለት ወራት ውስጥ መልሶ ለማቋቋም የክልሉ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ እንደሆነም አቶ አሰማኸኝ አስታውቀዋል፡፡

በምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር የተቃጠሉ ቤቶችን ለመገንባት ከሚፈለገው የቤት ክዳን ቆርቆሮ 50 ከመቶውን መንግሥት መግዛቱን ያስታወቁት አቶ አሰማኸኝ ቀሪውን መንግሥት ከለጋሽ አካላት እየጠበቀ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በማዕከላዊ ጎንደር 4 ሺህ 361 ቤቶች እና በምዕራብ ጎንደር 1 ሺህ 500 ቤቶች ተቃጥለዋል፡፡

በመሆኑም የክልሉ መንግሥት 5 ሺህ 861 ቤቶችን ገንብቶና መንደር መሥርቶ ዜጎችን ሊያቋቁም መሆኑን ነው ዋና ዳይሬክተሩ የተናገሩት፡፡

የሚገነቡት ቤቶች እንደ ቤተሰብ ብዛት የሚለያዩ ናቸው፤ አራትና ከዚያ በታች አባላት ላሉት ቤተሰብ ባለ 40 ቆርቆሮ፣ ከአራት በላይ የቤተሰብ አባላት ላሏቸው ደግሞ ባለ 60 ቆርቆሮ ቤት እንደሚገነባ ነው የተናገሩት፡፡

#የመከላከያ_ሠራዊትና የክልሉ የፀጥታ ኃይሎች ኃላፊነቱን ወስደው በዞኖቹ እየሠሩ እንደሆነ አስታውቀው ‹‹ከዚህ በኋላ ወንጀለኞችን ለአንድም ደቂቃ ቢሆን አንታገስም›› ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡
በአማራ ክልል ከሚገኙ 90 ሺህ 736 ተፈናቃዮች 25 ከመቶው በመጠለያ ይገኛሉ፤ ቀሪዎቹ ደግሞ በዘመድ ወዳጅ ተጠግተዋል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ናቸው፡፡

ከቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል #የተፈናቀሉ ወገኖችን ወደ ቀያቸው #ለመመለስም እየተሰራ መሆኑን አቶ አሰማኸኝ አስታውቀዋል፡፡ ለዚህም ከቤኔሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ጋር ውጤታማ #ምክክር እየተደረገ ነው ብለዋል። አፈጻጸሙም የተፈናቀሉት ወገኖች ጋር መግባባት ላይ ከተደረሰ በኋላ የሚተገበር ይሆናል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update መጋቢት 29 በሚጀመረው የህዝብና ቤት ቆጠራ ግጭት ያለባቸው አካባቢዎችና #የተፈናቀሉ ዜጎችን ያማከለ ቆጠራ እንደሚካሄድ የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ ግጭት ያለባቸው አካባቢዎችንና የተፈናቀሉ #ዜጎችን ጉዳይ በተመለከተ እያንዳንዱ ክልል ከለውጡ በኋላ ያለበትን ሁኔታ ለማወቅ ከሁለት ወራት በፊት ስብሰባ ተደርጎ መገምገሙን በኤጀንሲው የህዝብ ግንኙነትና መረጃ አሰባሰብ ዳይሬክተር አቶ ሳፊ ገመዲ ገልጸዋል፡፡ በዚህም ሁሉም ክልል የየራሱን ሪፖርት ካቀረበ በኋላ፣ የቆጠራ ኮሚሽኑ መሰረታዊ ነጥቦች ላይ በሰፊው ውይይት አድርጎ ውሳኔ ማስተላለፉን ኃላፊው አመልክተዋል፡፡ በዚህም ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች የህዝብና ቤት ቆጠራውን ለማካሄድ እንደ አማራጭ ክልሎች በአስቸካይ ተነጋግረው ችግሮችን በፈቱባቸው አካባቢዎች የቆጠራ ካርታ መሰራቱንም ገልጸዋል፡፡ አቶ ሳፊ እንደሚሉት ክልሎች ችግሩን መፍታት ባልቻሉባቸውና የቆጠራ ካርታ ባልተሰራባቸው አካባቢዎች ‘’ልዩ የቆጠራ ቦታ’’ ‘’Special Enumeration area’’ ተብሎ ተይዞ ቆጠራው ይካሄዳል።

Via EBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ተፈናቃዮችን ለማቋቋም ቴሌቶን ተዘጅቷል‼️

በአማራ ክልል እና ከክልሉ ውጭ #የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል፡፡

ነገ መጋቢት 7 ቀን 2011ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል የድጋፍ ማሰባሰቢያ ቴሌቶን ተዘጋጅቷል፡፡

በአማራ ክልል እና ከክልሉ ውጭ የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም ነው 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብሩ የሚያስፈልገው፡፡ የአማራ ክልል መንግሥት ተፈናቃዮቹን ለመርዳት በጊዜያዊነት የሰብዓዊ ዕርዳታዎችን እያደረገ መሆኑንና በዘላቂነት ደግሞ መልሶ ለማቋቋም እየተንቀሳቀሰ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

የሚፈለገውን የገንዘብ መጠን እና የቁሳቁስ ድጋፍ ለመሰብሰብም ነገ መጋቢት 7 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሸራተን አዲስ ሆቴል ቴሌቶን ለማዘጋጀት መርሀ-ግብር ተይዟል፡፡

በዝግጅቱ ዕርዳታ ከመሰብሰብ ባሻገር የአብሮነት እና የአንድነት መልዕክቶች እንደሚተላለፉም ታውቋል፡፡

አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ያለበትን የምጣኔ ሀብት ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት #ከተመረጡ አካላት ብቻ ዕርዳታ የመሰብሰብ ሥራዎችም ተጀምረዋል፡፡ በዚህም ከባለሀብቶች፣ መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች፣ ከዲያስፖራዎች እና ሌሎች አካላት ዕርዳታ ለማግኘት ንዑስ ኮሚቴዎች ተዋቅረው ወደ ተግባር መገባቱንም አልማን ዋቢ አድርጎ አብመድ ዘግቦ ነበር፡፡

የገቢ ማሰባሰቢያ ቴሌቶኑ 90 ሺህ 736 ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመ ነው፡፡ ከቤታቸው ተፈናቅለው ለሚገኙ አርሶ አደሮች የክረምት ጊዜ ከመድረሱ በፊት ለእርሻ የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ማሟላትም ትኩረት ተሰጥቶታል፡፡

ተልዕኮውን ‹‹አግዛለሁ›› የሚል እና ዕርዳታ ለማድረግ የሚፈልግ ማንኛውም ቅን ዜጋ በተለያዩ ባንኮች በተከፈቱ የሒሳብ ቁጥሮች ማስገባት እንዲችልም ቁጥሮቹ ይፋ ተደርገዋል፡፡

በዚህ መሠረት፡-

•ዓባይ ባንክ የሒሳብ ቁጥር፡ 25 62 11 25 41 58 017፣

• አቢሲኒያ ባንክ የሒሳብ ቁጥር፡ 16 24 11 37፣

•የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሒሳብ ቁጥር፡ 10 00 25 82 50 811 ናቸው፡፡

በሸራተን አዲስ ሆቴል በሚኖረው መርሀ-ግብር በቀጥታ ስልክ እየደወሉ ድጋፋቸውን መግለጽ ለሚፈልጉ ሁሉ የተንቀሳቃሽ ስልክ ቁጥሮች አገልግሎት እንደሚሰጡ ተነግሯል፡፡ ቁጥሮቹም፡-

09 08 91 91 91
09 08 92 92 92
09 08 93 93 93
09 08 94 94 94 ናቸው።

Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ: በጌዴኦ ዞን ለሚገኙ #የተፈናቀሉ ዜጎች በናተው በኩል በተሰበሰበ ገንዘብ #ድጋፍ ለማድረግ የተደረገ ጉዞ። #TIKVAH_ETH #ጌዴኦ #ኢትዮጵያ

ዝርዝር መረጃዎች ይኖሩኛል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Oromia

ኦሮሚያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በችግር ላይ ላሉ ወገኖች አስቸኳይ የሰብዓዊ ዕርዳታ እንዲደረግላቸው የጋራ ጥሪ አቅርበዋል።

በአጠቃላይ 12 መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በኦሮሚያ ያለውን ሁኔታ በተመለከተ መግለጫ አውጥተዋል።

በመግለጫቸው፤ በኦሮሚያ እየተከሰተ ያለውን የሰብዓዊ ቀውስ ለመፍታት ሁሉም ባለድርሻ አካላት ትኩረት እንዲሰጡ ጠይቀዋል።

" በድርቅ እና ግጭቶች ከ14 ሚሊዮን በላይ ሰዎች አስቸኳይ ሰብዓዊ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል " ያሉት ድርጅቶቹ " ከነዚህ መካከል በግጭቶች እና በድርቅ ሳቢያ #የተፈናቀሉ 3.4 ሚሊዮን ያህል ሰዎች ይገኙበታል " ሲሉ ገልጸዋል።

የሰብዓዊ ድጋፍ አጋር ድርጅቶች በክልሉ ያለውን ሰብዓዊ ሁኔታ በዝርዝር እንዲገመግሙ እና ለድንገተኛ ሰብዓዊ ቀውስ ምላሽ ለመስጠት ተጨማሪ የሰብዓዊ ድጋፍ ፈንድ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።

" የውስጥ ተፈናቃዮች የመጠለያ፣ የንፅህና አገልግሎት፣ የምግብ፣ የትምህርትና የጤና አገልግሎት ያስፈልጋቸዋል " ያሉት ድርጅቶቹ ፤ በኦሮሚያ በአጠቃላይ ከ3.7 ሚሊዮን በላይ ሰዎች አስቸኳይ የውሃ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው አመላክተዋል።

እነዚሁ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፤ #በቦረና በአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ሳቢያ በአንዳንድ አካባቢዎች ለ5 ተከታታይ የዝናብ ወቅቶች ዝናብ ባለመዝናቡ 46 በመቶ የሚሆኑት የቀንድ ከብቶች እንዲጠፉ ምክንያት እንደሆነና በርካታ አባወራዎች ሁሉንም ያላቸውን ከብቶች እንዳጡ ጠቁመዋል።

ድርጅቶቹ፤ በተለይ በቦረና ዞን ከዚህ ቀደም በታሪክ ታይቶ አይታወቅም ባሉት ድርቅ ምክንያት የህዝቡ ሁኔታ አሁን ላይ ወደ ለህይወት ወደሚያሰጋ ደረጃ ተቀይሯል ሲሉ አሳውቀዋል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

Pic. Jawar Mohammed

@tikvahethiopia