TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን⬇️

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከማሺ ዞን እና በደቡብ ክልል ሸካና ከፋ ዞኖች የተከሰቱት #ግጭቶች ከቁጥጥር ውጪ ከመሆናቸው አስቀድሞ መንግስት አስፈላጊውን #እርምጃ እንዲወስድ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ጠየቀ።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶክተር አዲሱ ገብረእግዚአብሄር #ከሃዋሳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፥ በእነዚህ ቦታዎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቱ እና ግጭቱ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አስታውቀዋል።

በተለይም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ካማሺ ዞን በሚገኙ አምስት ወረዳዎች ላይ ያለው ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ነው የገለፁት።

በእነዚህ ሶስት ዞኖች የዜጎች የመንቀሳቀስ እና ንብረት የማፍራት #መብት መገደቡን አስታውቀዋል።

ኮሚሽኑ ወደ ሶስቱም አካባቢዎች መርማሪዎችን ቢልክም ምርመራ እንዲያደርጉ የሚያስችል ሁኔታ አለመኖሩን እና መንቀሳቀስ አለመቻላቸውን ነው የተናገሩት።

የፀጥታ አካላትም ግጭቶቹን ለማስቆም ተገቢውን እርምጃ እየወሰዱ አለመሆናቸውን ከአካባቢዎቹ መርማሪዎች ለኮሚሽኑ በስልክ ያደረሱት መረጃ እንደሚጠቁምም ገልፀዋል።

አሁን ላይ በይፋ በግጭቶቹ #የሞቱ እና #የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥርንም በዚህ ምክንያት በአግባቡ ማጣራት አለመቻሉን በማንሳት ይህም የችግሩን ስፋት እንደሚያሳይ ተናግረዋል።

በመሆኑም የሀገር መከላከያ ሰራዊት ችግሩ በተፈጠረባቸው እነዚህ አካባቢዎች ገብቶ የማረጋጋት ፣ ህግ እና ስርዓትን እንዲሁም የዜጎችን መብት የማስከበር ስራ እንዲያከናውን ነው የጠየቁት።

እስካሁን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሽ ዞን ግጭት ካለባቸው አምስት ወረዳዎች መካከል በሁለቱ የሀገር መከላከያ ሰራዊት በመግባቱ የተሻለ ሁኔታ እየታየ መሆኑን ዶክተር አዲሱ አስታውቀዋል።

በእነዚህ መከላከያ በገባባቸው ቦታዎችም ኮሚሽኑ ከነገ ጀምሮ ምርመራ እንደሚጀመር ነው ያስታወቁት። ምርመራውንም በኃላፊነት መንፈስ ያከናውናል ብለዋል።

ዶክተር አዲሱ በመግለጫቸው በተለያዩ አካባቢዎች እየተስተዋሉ ያሉ ችግሮችን መነሻ በማድረግ ችግሮቹ ከመከሰታቸው በፊት አስቀድሞ ለመከላከልና ሲከሰቱም በዘላቂነት ችግሮቹን ለመፍታት የሚያስችል ጥናት ኮሚሽኑ አድርጎ ለመንግስት ማቅረቡን አስታውቀዋል።

ምንጭ ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
🕊ሀዋሳ🕊

ሰላም በሌለበት ልማት፣ ዴሞክራሲና የተረጋጋ ሕይወትን ማሰብ እንደማይቻል የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ #የሰላም_ሚኒስቴር አስታወቀ።

ከዘጠኙ ክልሎችና ከሁለት የከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ የሰላም አምባሳደር እናቶች ትላንር #ከሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ጋር ተወያይተዋል።

በውይይቱ ላይም የሰላም ሚኒስቴር ተወካይ የሆኑት ወይዘሮ #አበባ_ተገኝ እንዳሉት በሃገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የተከሰተው የጸጥታ ችግር እንዲቆም መላው ህብረተሰብ በትኩረት ሊሰራ ይገባል።

“ያለ ሰላም ልማት ዴሞክራሲና እድገት አይኖርም” ያሉት ተወካይዋ ሴቶች በሰላም እጦት ምክንያት ዋነኛ ተጎጂዎች በመሆናቸው ለዘላቂ ሰላም መረጋገጥ ሁሉም ህብረተሰብ ከሴቶች ጎን እንዲቆም ጠይቀዋል።

ወጣቱ የሃገር ተረካቢ እንዲሆን ወላጆች ማስተማር ብቻ ሳይሆን በመልካም ስነ-ምግባር በማነጽና በመቆጣጠር ለጸረ-ሰላም ኃይሎች መጠቀሚያ እንዳይሆን ማድረግ እንዳለባቸውም ገልጸዋል።

የሰላም አምባሳደርና የልኡካን ቡድኑ አባል የሃረሪ ክልል ተወካይ ወይዘሮ ገነት አሰፋ በበኩላቸው ሁሉም በየአካባቢው ያሉ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን እንደ ልጆቹ በመጠበቅ በሰላም እጦት እንዳይጎዱ ሊከላከል እንደሚገባ አስረድተዋል።

የሰላም አምባሳደሮቹ በዛሬው እለት የተወያዩባቸውን የሃላባና ሃዋሳ ከተሞች ነዋሪዎችን ጨምሮ በሃገሪቱ የተለያዩ ከተሞች በመዘዋወር ተመሳሳይ ውይይት አድርገዋል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እንኳን ተረፋቹልን...

"ዛሬ 10 ሰዓት አካባቢ #ከሃዋሳ ወደ #አዳማ ይዞን ይጓዝ የነበረ FSR ቅጥቅጥ ባስ ተገልብጦብን 1 ሰው ከባድ ጉዳት ደርሶበታል፤ ሌሎቻችን ምንም አልሆንም"

@tsegabwolde @tikvahethipia