TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ለተማሩና ሐሳብ ላላቸው ዜጎች #የብድር ሥርዓት ሊዘረጋ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አሕመድ ተናገሩ። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስር ዶክተር #ዐብይ_አህመድ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ባለፉት ጊዜያት ትልልቅ ሐሳብ ላላቸው ሳይሆን ትልልቅ ሀብት ላላቸው ብቻ ከፍተኛ የብድር አገልግሎት ስትሰጥ ቆይታለች፤ በዚህም የሚፈለገው ለውጥ ሳይመዘገብ ቀርቷል፡፡

Via አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ🔝

ለተማሩና ሐሳብ ላላቸው ዜጎች #የብድር ሥርዓት ሊዘረጋ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #ዐብይ_አሕመድ ተናግረዋል። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስር ዶክተር ዐብይ አህመድ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ባለፉት ጊዜያት ትልልቅ #ሐሳብ ላላቸው ሳይሆን ትልልቀቅ #ሀብት ላላቸው ብቻ ከፍተኛ የብድር አገልግሎት ስትሰጥ ቆይታለች፤ በዚህም የሚፈለገው ለውጥ ሳይመዘገብ ቀርቷል፡፡ ይህንን ችግር በመረዳትም ለተማሩ ዜጎች ሐሳባቸውን በማዬት ብድር ለመስጠት እንዲቻል ፖሊሲዎች እንደሚመቻቹና አነስተኛና መካከለኛ ባለሀብቶች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል፡፡

በዓለም ባንክ የአገልግሎት አሰጣጥ መለኪያ መሠረት ኢትዮጵያ 159ኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣይ 5 ዓመታት የተቋማትን የአገልግሎት አሰጣጥ ደረጃ #በማሻሻል በመለኪያው ከ100 በታች ለማድረግ በእርሳቸው የሚመሩ 10 ተቋማት ተለይተው ወደ ለውጥ ሥራ መገባቱን አስታውቀዋል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የአሠራር ፖሊሲዎች፣ የሕግ ማዕቀፎች እና የአገልግሎት ሰጭ ተቋማት በተቃርኖ የተሞላ አሠራርን መከተላቸው ኢትዮጵያ በቀላሉ ሥራ (ቢዝነስ) የማይሠራባት ሀገር እንድትሆን ማድረጉንም ገልጸዋል፡፡

ካለፈው ወር ጀምሮ በጠቅላይ ሚኒስትሩ #የሚመራው እና 10 ተቋትን ያካተተው ልዩ ኮሚቴ (ስትሪንግ ኮሚቴ) አገልግሎት አሰጣጥን ለማሳደግ የጀመራቸውን የለውጥ ሥራዎች በየወሩ የውጤት ግምገማ እያደረገ ይገኛል፡፡

ቀጣይነት ያለው ሀገራዊ ዕድገት እንዲመዘገብ ‹‹ያለንን የተፈጥሮ ሀብት #በአግባቡ መጠቀምና ሥራ አጥነትን ለመቅረፍ አዳዲስ ሐሳብ፣ ዕውቀትና ክሕሎትን በተቀናጀ መልኩ አሟጦ መጠቀም ይጠይቃል›› ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡

እስካሁን ያለው አካሄድ በተቃርኖ የተሞላ፣ ዘመናዊ አሠራርን ያልተከተለ፣ ተወዳዳሪነት የሌለውና በአነስተኛ የሥራ ዘርፍ የተሰማሩ ዜጎችን በቀላሉ የማይጠቅም በመሆኑ ውጤት ማምጣት እንዳልቻለም ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያብራሩት፡፡ ለዚህ ደግሞ ውስብስብ የሆነ አካሄድን መጠቀምና የገንዘብ አቅርቦት ችግር ምክንያቶች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

ከችግሩ ለመውጣት የአሠራር ሥርዓትን ማቅለል፣ የፖሊሲና የሕግ ማዕቀፍ ማሻሻያዎችን ማድረግና ምቹ አካባቢን መፍጠር እንደሚገባ ነው ያብራሩት፡፡

ለሥራዎች ገንዘብ የማቅረብ ሂደቱን ቀላል ማድረግ፤ እስካሁን ቋሚ ንብረት ይያዝ የነበረበትን የባንኮች አሠራር በቀጣይ ሐሳብን በማስያዝ ወጣቶች ብድር የሚወስዱበት ሁኔታ እንዲፈጥር ማድረግና የግል ተቋማት ውስጥ በቀላሉ ወደ ሥራ ተገብቶ ውጤታማ የሚሆንበትን መንገድ ማመቻቸት እንደሚገባም ነው የተናገሩት፡፡

‹‹በአዲስ ዕውቀትና ሐሳብ ዕድገታችን ማስቀጠል አለብን፤ ለዚህ መንግሥት ማድረግ የሚገባውን ሁለንተናዊ ድጋፍ ለግል ዘርፍ መስጠት አለበት፡፡ ከዚህ በላይ ደግሞ ቀላልና ሳይንሳዊ የሆነ የአሠራር ሥርዓትን መዘርጋት ይገባል›› ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስት ዶክተር ዐብይ፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ ‹‹አይቻልም›› ወይም ‹‹ሕጉ አይፈቅድም›› የሚሉ አመለካከቶችን በመስበር ሁሉም ተቋማት ለሀገር ሲሉ ቀና አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡ ጅምሮቹ ወደ ውጤት እንዲያድጉ አሁንም ተቋማት በቅንጅት መሥራት እንዳለባቸውም መክረዋል፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ያለፈው አንድ ወር አፈጻጸም ቀርቦ ተገምግሟል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#የብድር_ገደብ

ብሔራዊ ባንክ የጣለው የብድር ገደብ በባንኮች እና ተበዳሪዎች ላይ ተግዳሮት መፍጠሩ ተነግሯል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ / #NBE ከጥቂት ወራት በፊት ያወጣው የገንዘብ ፖሊሲ ወደ ትግበራ ገብቷል፡፡

የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ዋነኛ ዓላማ ያደረገው ይህ ፖሊሲ ፣ የባንኮች የብድር ምጣኔ ካለፈው ዓመት ከ14 በመቶ በላይ እንዳይበልጥ ገደብ የጣለ ነው፡፡

በተለይ ባንኮች የሚሰጡት ብድር በገንዘብ ፖሊሲው ከተጣለባቸው ገደብ ጋር ለማጣጣም በማሰብ ቀደም ብለው የፈቀዷቸውን ብድሮች ጭምር ከመልቀቅ እንዲቆጠቡ ወይም መሰል አሠራርን እንዲከተሉ እያደረጋቸው ስለመሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡ 

ከመመርያው መውጣት ቀደም ብለው የተፈቀዱ ብድሮች ሊለቀቅላቸው እንዳልቻለ የተለያዩ ባለሀብቶችና የንግድ አንቀሳቃሾች ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ገልጸዋል።

በዚህም የተፈቀደላቸውን ብድር ታሳቢ በማድረግ የገቧቸው የቢዝነስ ስምምነቶች እየተፋረሱባቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ቤትና ተሽከርካሪ ግዥ ውሎች ሳይቀሩ በእንጥልጥል እንዲቆዩ ማድረጉንም ከተበዳሪዎች መገንዘብ ተችሏል፡፡ 

ብድር እንዲለቀቅላቸው #ማረጋገጫ አግኝተው የነበሩት ተበዳሪዎች አሁን ላይ ብድሩን ማግኘት ለምን እንዳልቻሉ ለሚያቀርቡት ጥያቄ የሚያገኙት ምላሽ " አዲሱ የገንዘብ ፖሊሲ የጣለው የብድር ዕቀባ " መሆኑን ያስረዳሉ።

አንዳንዶቹም የተፈቀደላቸውን ብድር በትዕግሥት እንዲጠብቁ እንደተነገራቸው ያመለክታሉ፡፡

ቤት ለመግዛት ተዋውለው ከሚገለገሉበት ባንክ የፈቀደላቸውን ብድር እየተጠባበቁ የነበሩ አንድ ተበዳሪ ብድሩ እንደሚያገኙት በተገለጸላቸው ወቅት ሊለቀቅላቸው ባለመቻሉ የቤት ሽያጭ ውላቸው ሊፈርስባቸው እንደሆነ ገልጸዋል። እንዲህ ያለው ችግር በአብዛኛው በግል ባንኮች አካባቢ የሚስተዋል ነው፡፡

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Reporter-Newspaper-10-17

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA #Eurobond ኢትዮጵያ በዓለም ገበያ ለሸጠችው የ1 ቢሊዮን ዶላር ዩሮ ቦንድ ሰኞ ዕለት መክፈል የነበረባትን ወለድ እስካሁን አልከፈለችም። ገንዘብ ሚኒስቴር የክፍያ መጠኑን በአሁኑ የሀገሪቷ አቅም መክፈል እንደሚቻል ገልጿል። ክፍያውን ላለመክፈል የተወሰነው ሁሉንም አበዳሪዎች በፍትሃዊነት እኩል ለማስተናገድ ነው ብሏል። @tikvahethiopia
#ETHIOPIA #Eurobond

ኢትዮጵያ የቦንድ ብድር ወለድ በወቅቱ ያልከፈለችው ለምንድነው ?

ኢትዮጵያ በዓለም ገበያ ለሸጠችው የ1 ቢሊዮን ዶላር ዩሮ ቦንድ ሰኞ ዕለት መክፈል የነበረባትን ወለድ እስካሁን አልከፈለችም።

የ1 ቢሊዮን ዶላር ቦንድ ለሽያጭ የቀረበው ከ9 ዓመት በፊት በ2007 ዓ.ም ነበር።

ኢትዮጵያ ይህንን ቦንድ ሸጣ ከገዢዎች አንድ ቢሊዮን ዶላር ብድር ያገኘች ሲሆን ብድሩ የሚመለሰው በ10 ዓመት ውስጥ ነው።

እስከዚያው ድረስ መንግሥት በዓመት ሁለት / 2 ጊዜ የሚፈጸም የ6.625 በመቶ ዓመታዊ ወለድ ለቦንዱ ገዢዎች ይከፍላል።

ኢትዮጵያ ባለፈው ሰኞ ዕለት 33 ሚሊዮን ዶላር ወለድ መክፈል የነበረባት ቢሆንም ክፍያውን ሳትፈጽም ቀናት አልፈዋል።

" የክፍያ መጡኑን በአሁኑ የሀገሪቷ አቅም መክፈል ይቻላል ፤ ላለመክፈል የተወሰነው ሁሉንም አበዳሪዎች እኩል ለማስተናገድ ነው " - ገንዘብ ሚኒስቴር

የብድር ቦንዱን አስመልክቶ ትላንትና ከቦንድ ገዢዎች ጋር የገንዘብ ሚኒስቴር ዲኤታ ዶክተር ኢዮብ ተካልኝ በነበሩበት ውይይት ተደርጎ ነበር።

ይህን በተመለከተ ገንዘብ ሚኒስቴር ምን አለ ?

- ኢትዮጵያ #የታኅሣሥ_ወርን ወለድ ያላስተላለፈችው ክፍያውን ለማዘግየት ወስና ነው። ይህም ለገዢዎቹ ተገልጿል።

- ኢትዮጵያ #ወለዱን_ለመክፈል የሚያስችል ገንዘብ አላት።

- ክፍያውን የማዘግየት ውሳኔ ላይ የተደረሰው ሁሉንም የውጪ አበዳሪዎች በፍትሐዊነት ለማስተናገድ ሲባል ነው።

- አበዳሪዎች #በፍትሐዊነት ለመመልከት አለመቻል በዕዳ ሽግሽግ ላይ ከሌሎች የውጭ አበዳሪዎች ጋር የሚደረገውን ውይይት አደጋ ላይ ይጥለዋል። ወለዱ ቢከፍል መስተገጓጎል ሊያጋጥም ይችላል።

- በቅርቡ ከኦፊሴላዊ አበዳሪዎች ጋር የብድር ክፍያ ሽግሽግን በተመለከተ ስምምነት ላይ ተደርሷል።

- #የቦንድ_ገዢዎችን ጨምሮ ሌሎች አበዳሪዎችም ተመሳሳይ አይነት የብድር ክፍያ ማስተካከያ ውስጥ እንዲገቡ በማድረግ ከሁሉም አበዳሪዎች ጋር በሚኖር ግንኙነት ላይ #ወጥነት እና #እኩልነትን ለማረጋገጥ ያስፈልጋል።

የብድር እፎይታ ....

* ኢትዮጵያ ላለባት ብድር #የብድር_እፎይታ ለማግኘት በ " ቡድን 20 " የጋራ ማዕቀፍ በኩል የዕዳ ሽግሽግ ለማድረግ ውይይት ስታካሂድ ቆይታ ነበር።

* ባለፈው ኅዳር ወር በቻይናና በፈረንሳይ በሚመራው የፓሪስ ክለብ አማካኝነት የዕዳ ሽግሽግ ስምምነት ላይ ተደርሷል።

* በዚህ ስምምነት መሠረት ኢትዮጵያ ለአበዳሪዎቿ መክፈል የሚጠበቅባትን ብድር እና ወለድ 2 ዓመት ገደማ አትከፍልም።

* ይህ የዕዳ ክፍያ ሽግሽግ በየዓመቱ የሚከፈለውን 1.5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ዕዳ በጊዜያዊነት የሚያስቀር ነው።

ኢትዮጵያ የዚህን አይነቱን ስምምነት የ1 ቢሊዮን ዶላር ቦንዱን ከገዙ የግል ባለሀብቶች ጋርም ለመፈጸም ትፈልጋለች።

የዋናው ብድር የመክፈያ ጊዜ እንዲራዘምና በየዓመቱ የሚከፈለውን የወለድ ምጣኔው ከ6.625 በመቶ ወደ 5.5 በመቶ ዝቅ ማድረግ ሀሳብ አላት።

መንግሥት የብድር አከፋፈሉ ላይ ማስተካከያ ማድረግ የፈለገው ከሌሎች አገራት ጋር በሚያደርገው የብድር ሽግሽግ ላይ አበዳሪዎችን በተመሳሳይ መልኩ ማስተናገድን በተመለከተ ስጋት እንዳይነሳ በማሰብ መሆኑን አሳውቋል።

መንግሥት የብድር አከፋፈል ማስተካከያው ላይ ከቦንዱ ገዢዎች ጋር በተቻለ ፍጥነት ስምምነት ላይ መድረስ ጠንካራ ፍላጎት አለው።

የቦንዱ ገዢዎች ጋር ያለው ስሜት ምንድነው ?

° ኢትዮጵያ የቦንድ ብድር ወለዱን በቀኑ እንደማትከፍል ማስታወቋ በቦንዱ ገዢዎች ዘንድ በመልካም አልተወሰደም።

° የቦንዱ ገዢዎች ኮሚቴ የኢትዮጵያ መንግሥት ውሳኔ አላስፈላጊ እና አሳዛኝ አድርጎ እንደሚመለከተው ገልጿል።

° የኢትዮጵያ መንግሥት ውሳኔውን የማያጥፍም ከሆነ ከፍ ያለ ዳፋ ይኖረዋል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ባለፈው #ሰኞ መክፈል የነበረባትን ወለድ ለቦንድ ገዢዎች ለማስተላለፍ የ14 ቀናት የእፎይታ ጊዜ ተሰጥቷታል።

በእነዚህ በተሰጡ ቀናት ውስጥ ወለዱን የማትከፍል ከሆነ ውልን አለማክበር (#technical_default) እንደሚገጥማት የዘርፉ ባለሞያዎች ተናግረዋል።

" ፊች " የተሰኘው የአገራትን ብድር የመክፈል አቅም ደረጃ የሚያወጣ አሜሪካ ተቋም ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያን የረጅም ጊዜ ዕዳ የመክፈል ደረጃ ከነበረበት " ሲሲ " (CC) ደረጃ ወደ " ሲ " (C) ዝቅ ማድረጉን አስታውቋል።

ተቋሙ ለዚህ ደረጃ ምደባ የጠቀሰው አንዱ ምክንያት ኢትዮጵያ የቦንዱን ወለድ በቀኑ አለመክፈሏል ነው ያለ ሲሆን በ14 ቀናት ውስጥ ክፍያው ካልተፈጸመ ይህንን ደረጃ በድጋሚ ዝቅ እንደሚያደርገው ገልጿል።

Credit - BBC AMAHRIC / REUTERS

@tikvahethiopia