TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ፌደራል ፖሊስ⬇️

ለኦነግ አባላትና አመራር በአዲስ አበባ የተዘጋጀው የአቀባበል ስነስርዓት #ያለአንዳች ችግር መጠናቀቁን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል አስታወቁ።

ኮሚሸነሩ ከfbc ጋር ባደረጉት ቆይታ በአቀባበል ስነስርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ፖሊስ፣ የሀገር መከላከያ፣ የኦሮሚያ ፖሊስ፣ የፌደራል ፖሊስ እና ደህንነት የተጠናከረ ጥበቃ ሲያደርጉ መቆየታቸውንም አንስተዋል።

በአቀባበል ስነስርቱ ላይ ከአራት ሚሊየን (4,000,000) #በላይ ህዝብ የተገኘ ሲሆን፥ የህዝቡን ሰላም በጠበቀ መልኩ #በሰላም መጠናቀቁን ገልጸዋል።

በአቀባበል ስነስርዓቱ ላይ የተገኙ #ወጣቶችም ከፖሊስ ጋር #ትብብር ሲያደርጉ መቆየታቸውን ያነሱት ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ #ጸጥታውን ለማስከበርም በጋር ሲፈትሹ እንደነበረም ጠቅሰዋል።

በዚህም #ቄሮዎችን ያመሰገኑ ሲሆን፥ ለሌሎችም አርአያ የሚሆን ተግባር መፈጸማቸውን ጠቅሰዋል።

የአዲስ አበባ ወጣትም የአቀባበል ስነስርዓቱ መጠናቀቅን ተከትሎ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች የሚመለሱ ወጣቶችን #ምግብና ውሃ በማዘጋጀት ግብዣ ሲያካሂድ እንደነበረ ገልጸዋል።

ኮሚሽነሩ ይህ #አንድነትን ይበልጥ የሚያጠናክርና ለሀገሪቱም ትልቅ #ተስፋ መሆኑን አንስተዋል።

አንዳንድ ቦታዎች ላይ "ወጣት ነን" የሚሉ ግለሰቦች #ድንጋይ የመወርወር አዝማሚያ ማሳየታቸውን የጠቀሱ ሲሆን፥ ፖሊስም #በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸው ተናግረዋል።

በተመሳሳይ በአዲስ አበባ #ዙሪያ በቄሮ ስም #የሚነግዱ ቄሮ ያልሆኑ ከአቀባበል ስነ ስርዓቱ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው ግለሰቦች ዝርፊያና #ግድያ መፈጸማቸውን አንስተዋል።

በዚህም ፌደራል ፖሊስ፣ የኦሮሚያ ፖሊስ እና የሀገር መከላከያ ወደ አካባቢው በመሄድ ግለሰቦቹን በቁጥጥር ስር እያዋለ ይገኛል ብለዋል።

በጥቅሉ አቀባበሉ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት የታየበት ጥሩ መንፈስ የነፈሰበት ህዝቡ እንግዶቹን ተቀብሎ በሰላም እንዲጠናቀቅ ያደረገበት ነው ብለዋል።

የአቀባበል ስነስርዓቱ በሰላም መጠናቀቅ ህዝቡ ላደረገው ትብብር፣ ለቄሮ እና ለአዲስ አበባ ህዝብ ምስጋና አቅርበዋል።

በአቀባበል ስነስርዓቱ ላይ የነበሩ ቄሮዎች ባሳዩት ትብብር ፖሊስ መኩራቱን ገልጸው በቀጣይም ፖሊስ ጋር በመሆን እጅና ጓንት ሆነው እንደሚሰሩ እምነታቸውን ገልፀዋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia