TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update አማራ ክልል⬇️

በአማራ ክልል በዚህ ዓመት በትራፊክ አደጋ የ1 ሺህ 1 መቶ ሀምሳ ሁለት(1152) ሰዎች ህይወት ማለፉ ተሰማ፡፡ ባለፈው አመት በክልሉ በታራፊክ አደጋ ምክንያት ህይወታቸው ከጠፋ ሰዎች ቁጥር አንፃር የዘንድሮው በልጦ ተገኝቷል። ባለፈው ዓመት በትራፊክ አደጋ 1 ሺህ ዘጠና ስድስት(1096) ሰዎች ህይወታቸው ያለፈው፡፡

በሌላ በኩል⬇️

▪️በክልሉ በዚህ አመት 8 መቶ 57(857) ተሸከርካሪዎች አደጋ አድርሰዋል። ባለፈው ዓመት ደግሞ 7መቶ 96(796) ተሸከርካሪዎች አደጋ አድርሰዋል፡፡

የችግሩን አሳሳቢነት ለማሳወቅ ፣ ለመጠየቅ እና እውቅና ለመፍጠር ከህጻን እስከ አዋቂ የሚሳተፍበት #ሰልፍ ነገ በዋና ከተማዋ #ባህርዳር መዘጋጀቱን ከአማራ ክልል የመንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር መረጃ📌አዲስ አበባ የሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ነገ፣ መስከረም 9/2018 ዓ.ም. #ዝግ እንደሚሆን አስታውቋል።

ኤምባሲው ለነገ አገልግሎቱን የሚያቋርጠው በከተማዪቱ ውስጥ በሚካሄደው “ግዙፍ ሊሆን ይችላል” ባለው #ሰልፍ ምክንያት የተጠናከረ ጥንቃቄ ለመውሰድ ሲባል መሆኑን ገልጿል።

ቀደም ሲል ተይዘው የነበሩ የቪዛ ቀጠሮዎችና ኤምባሲው ለአሜሪካዊያን ዜጎች ለሚሰጣቸው አገልግሎቶች ለነገ መስከረም 9/2018 ዓ.ም /19 September 2018/ ተቀጥረው የነበሩ ጉዳዮች በሙሉ የተሠረዙ መሆናቸውን አስታውቋል።

አሜሪካዊያን በኤምባሲው ዌብሳይት አማካይነት አዲስ ቀጠሮ እንዲይዙ መክሯል።

ከኢሚግራንት ቪዛ ጠያቂዎች ጋር ተለዋጭ ቀጠሮ ለማድረግ ኤምባሲው በቅርቡ የሚያገኛቸው መሆኑንና ነን-ኢሚግራንት ቪዛ ለማግኘት ያመለከቱ ደግሞ በኤምባሲው ዌብሳይት ላይ አዲስ ቀጠሮ እንዲጠይቁ አሳስቧል።

አጣዳፊ አገልግሎት የሚፈልጉ አሜሪካዊያን ዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ዌብሳይት ላይ ያለውን የአድራሻ/የመገናኛ መረጃ እንዲያዩ መክሯል።

ከኤምባሲው መደበኛ አገልግሎቶች በተጨማሪ አዲስ አበባ ውስጥ የሚገኘው የአሜሪካ ማዕከል እና ዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ውስጥ የሚገኘው ሳችሞ ማዕከልም ነገ ዝግ ሆነው እንደሚውሉ አስታውቋል።

በሰልፉ ላይ #የሚሣተፉ ሁሉ ሃሣቦቻቸውንና ፍላጎቶቻቸውን በሰላማዊ መንገድ መግለፃቸውን እንደሚያበረታታም ኤምባሲው ገልጿል።

©VOA 24(የአማርኛው አገልግሎት)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ፌደራል ፖሊስ⬇️

በአዲስ አበባ #ለዛሬ የተጠራ ምንም ዓይነት #ሰልፍ አለመኖሩን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ።

ኮሚሽኑ ለfbc እንደገለፀው፥ ህብረተሰቡ በመዲናዋ ምንም ዓይነት የተጠራ ሰልፍ አለመኖሩን አውቆ #መደበኛ የእለት ተእለት እንቅስቃሴውን እንዲያከናውን አሳስቧል።

መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተቋማት ለረቡዕ በአዲስ አበባ የተጠራ ሰልፍ አለ በሚል ያወጡት መረጃ ሙሉ በሙሉ #የተሳሳተም ነው ብሏል።

©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአዲስ አበባ ፖሊስ⬇️

በአዲስ አበባ ነገ እውቅና የተሰጠው #ሰልፍ አለመኖሩን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

በከተማው ሕገ ወጥ ሰልፍ የሚደረግ ከሆነ በሕግ አግባብ #እርምጃ እንደሚወሰድም ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡

አንዳንድ ግለሰቦች ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ #መሟለት ያለባቸውን መስፈርቶች ማለትም የሰልፉ አስተባባሪዎች ማንነትና አድራሻ፣ እንዲሁም ሰልፉ ላይ የሚገኝ የሰው ብዛት ሳያሳውቁ መስከረም 10 ቀን 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሰልፍ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡

ለህብረተሰቡ ሰላምና ደህንነት ሲባል አብዛኛው የጸጥታ ኃይል በሌላ የጸጥታ ስራ ላይ በተሰማረበት በአሁኑ ወቅት ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ምቹ ሁኔታ አለመኖሩን ኮሚሽኑ አስታውቆ፣ #ነገ መስከረም 10 ቀን 2011 ዓ.ም ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ መሟለት ያለባቸውን
መስፈርቶች ሳያሟሉ ሰልፍ ለማድረግ የተዘጋጁ አካላት ከሕገ ወጥ ድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባና ይህንን ማሳሰቢያ ተላልፈው በሚወጡ አካላት ላይ ኮሚሽኑ በሕግ አግባብ #እርምጃ ለመውሰድ እንሚገደድ አስታውቋል፡፡

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ቦንጋ⬆️ዛሬም ለተከታታይ ቀን በቦንጋ ከተማ የተቃውሞ #ሰልፍ ሲደረግ ተስተውሏል። በከተማይቱ የንግድ አገልግሎት እንደቆም እንዲሁም የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንደተቋረጠ ነው። የቡና መገኛነታችን ይከበር በሚል ነው ተቃውሞው እየተካሄድ ያለው። ከአንድ የከተማይቱ ነዋሪ ጋር በስልክ ባደረኩት ቆይታ በቡና መገኛነት ዙሪያ የተሰራጨው መረጃ #ስህተት በመሆኑ የሚመለከተው አካል በሚዲያ ወጥቶ በግልፅ #ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባል ብሎኛል። ችግሩ ከዚህ ሳይሰፋም የክልሉም ሆነ የፌደራሉ መንግስት ሊፈቱት ይገባል ሲል አክሏል።

©ESA(TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ለሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች‼️

በማዕበራዊ ሚዲያዎች በተለይም ደግሞ በፌስቡክ በሚሰራጩ #ሀሰተኛ መረጃዎች እንዳትደናገሩ። በዛሬው ዕለት የከተማው አስተዳደር ህጋዊ እውቅና የሰጠው ህዝባዊ #ሰልፍ_የለም

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰላማዊ ሰልፍ አልተጠራም‼️

በአዲስ አበባ ከተማ እሁድ የካቲት 17/2011 ዓ/ም #በመስቀል_አደባባይ ሠላማዊ ሰልፍ ተጠርቷል በሚል በተለያዩ ሶሻል ሚዲያዎች የተላለፈው ዘገባ ሀሰተኛ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በነገው ዕለት ምንም ዓይነት የሠላማዊ ሰልፍ ሆነ ስብሰባ እናድርግ የሚል #ጥያቄ ያልቀረበለት መሆኑን ለኮሚሽኑ የገለፀ ሲሆን ሰልፉ በከተማ አስተዳደሩ ይሁን በፖሊስ ኮሚሽኑ እውቅና የሌለው ነው።
በመሆኑም #ሰልፍ_እንወጣለን በሚል በህብረተሰቡ ላይ የፀጥታ ችግር ለመፍጠር የሚፈልጉ አካላት ከተግባራቸው እንዲታቀቡ ኮሚሽኑ #በጥብቅ አሳስቧል።

ይህን ተላልፎ በሚገኙ አካላት ላይም የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል አስፈላጊውን ህጋዊ #እርምጃ የሚወስድ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል ፡፡

ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጥብቅ ማሳሰቢያ‼️

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር #በነገው ዕለት ምንም ዓይነት የሠላማዊ ሰልፍ ሆነ ስብሰባ እናድርግ የሚል #ጥያቄ አልቀረበለትም።

በመሆኑን በማህበራዊ ሚዲያ ተጠራ የተባለው ሰልፍ በከተማ አስተዳደሩ ይሁን በፖሊስ ኮሚሽኑ እውቅና የሌለው ነው።

ስለሆነም #ሰልፍ_እንወጣለን በሚል በህብረተሰቡ ላይ የፀጥታ ችግር ለመፍጠር የሚፈልጉ አካላት ከተግባራቸው እንዲታቀቡ ኮሚሽኑ #ጥብቅ_ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

ይህን ተላልፎ በሚገኙ አካላት ላይም የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል አስፈላጊውን ህጋዊ #እርምጃ_የሚወስድ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከወሊሶ🔝

"በወሊሶ ከተማ እየተካሄደ ባለው #ሰልፍ ምክንያት መንገድ ተዘግቶ ቆመናል። #ከአዲስ_አበባ እና #ከወልቂጤ ሚመጣ መኪና #ማለፍ አልቻለም።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
መቱ ዩኒቨርስቲ👆

"የመቱ ዩንቨርስቲ መምህራን በዩኒቨርሲቲው የተንሰራፋውን #የመልካም_አስተዳደር እጦት ይታወቅልን በማለት #ሰልፍ ወጥተዋል።"

√Save Mettu University
√ያለ ፕሬዘዳንት እስከ መቼ?
√የመቱ ዩኒቨርሲቲ ቦርድ እና የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ያነጋግሩን
√ፋይናስ አስተዳደር ለስራችን እንቅፋት መሆን አይገባም
√ለመምህራን ማህበር የሚገባው እውቅና ይሰጠው
√የትምህርት ቁሣቁሦች ይሟሉልን
√ወጥ የሆን የክፍያ አሰራር ይኑር

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ👆

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ ሀኪሞች የጠይቅናቸው ጥይቄዎች #በአስቸኳይ ይመለሱልን በሚል #ሰልፍ እያደረጉ ይገኛሉ። በሰልፉ ላይ እያስተላለፏቸው ከሚገኙት #መልዕክቶች መካከል፦

√ስለ ህመምተኛ እንግልት ዝም አንልም
√ታካሚ ካርቶን ላይ እስከመቼ?
√ማከም እንፈልጋለን
√Justice for the patients
√Justice for professionals

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ👆የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሀኪሞች #ሰልፍ እያደረጉ ይገኛሉ። #JimmaUniversity

@tseganwolde @tikvahethiopia
#HAWASSA የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በከተማዋ #ሰልፍ ለማድረግ ከየትኛውም አካል ጥያቄ እንዳልተቀበለ፤ ፍቃድም ተቀብሎ እውቅና እንዳልሰጠ አስታወቀ። ከተማ አስተዳደሩ የከተማው ነዋሪዎች በተራ አሉባልታ ሳይወናበዱ የተለመደውን የእለት ተእለት እንቅስቃሴዎቻቸው ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ ጥሪውን አስተላልፏል።

#TIKVAH_ETHIOPIA

ምንጭ፦ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር
@tsegabwolde @tikvahethiopia