TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አ.ሳ.ቴ.ዩ‼️

የመማር ማስተማሩ ሂደት ተቋርጦ የነበረው የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ ተማሪዎች ተመልሰው ትምህርት እንዲጀምሩ በሴኔት መወሰኑን ዩኒቨርሲቲው አስታወቀ።

የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር #ለሚ_ጉታ ለfbc እንደተናገሩት የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር እና መምህራን ትናንት ከተማሪ ወላጆች ጋር ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ ሴኔቱ ተማሪዎች ወደ ትምህርት እንዲመለሱ ወስኗል ብለዋል።

ከተማሪ ወላጆች ጋር በተደረገ ውይይትም ወላጆች ተማሪዎች ጥያቄ ቢኖራቸውም ትምህርት #ማቋረጣቸው ተቀባይነት የሌለው መሆኑንና የተፈጠረው ችግርም #እንዳሳዘናቸው መናገራቸውን አንስተዋል።

ወላጆች ለተማሪዎቹ ድርጊት #ይቅርታ እንዲደረግ መጠየቃቸውን ተከትሎም ሴኔቱ ያስተላለፈውን የአንድ ሴሚስተር ቅጣት ማንሳቱን ገልጿል።

በዚህ መሰረትም ከፊታችን ሰኞ የካቲት አራት ጀምሮ ተማሪዎች ወደ ተቋሙ የሚገቡ መሆኑ ነው የተገለፀው።

የተቋሙን የመማር ማስተማር ሂደት ሆነ ብለው ሲያውኩ የነበሩ ተማሪዎች ግን የስነ ምግባር ቅጣት እንደሚጠብቃቸው ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል።

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ትምህርት ማቆማቸውን ተከትሎ  ከጥር 12 ቀን  እስከ 14 ቀን 2011 ዓ.ም  ጊቢውን ለቀው እንዲወጡ መደረጋቸው ይታወሳል ።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia